የህሊና ቢሶች መጫወቻ መሆን የማያሳፍረውና የማይቆጨው ትውልድ – ጠገናው ጎሹ

February 11, 2023

ጠገናው ጎሹ

“እስከ ዛሬ ስለ ክርስቶስ አስተምሪያለሁ ። ተምሪያለሁ። ዛሬ ግን ራሱን ክርስቶስን አይቸዋለሁ” ይህን የሚነግረን የተሰጠውን የዲያቆንነትና የሙአዘ ጠበብትነት ስያሜ  ለርካሽ የግል ዝና እና ፍላጎት ማርኪያነት ካዋሉት ጨካኝና አደገኛ የዘመናችን አድርባዮች አንዱ የሆነውዳንዔል ክብረት ነው።  

እርግጥ ነው ከዳንኤል አይነት ህሊናውን ከሸጠና ሃይማኖታዊ እምነትን ልክ ለሌለው የግል ፍላጎቱ ማርኪያነት ሽፋን ከሚያውል (ከሚጠቀም) የበግ ለምድ ለባሽ ክፉ ተኩላ እንዲህ አይነቱን እጅግ የለየለት ቅጥፈት  መስማት ወይም ማንበብ የሚጠበቅ እንጅ ከቶ የማይጠበቅ አይደለም። በራሱም ይሁን በሰዎች  (ከተገኙ) አማካኝነት ተገልጦ ለዳንኤልና ለመሰሎቹ  የሚታይ እውነተኛ አምላክ (ክርስቶስ) መኖሩን እንኳን ለማመን ለማሰብም በእጅጉ ይከብዳል ።

ለዘመናት እና በተለይም ከራት ዓመታት ወዲህ ደግሞ በንፁሃን የግፍ ደምና የቁም ሰቆቃ ክፉኛ የተመረዘው የቤተ መንግሥት ፖለቲካ ታማኝ አማካሪ (በሰው አምሳል ቆሞ የሚሄድ ዲያብሎስ ለሆነ ሰው) ሊገለፅ (ሊከሰት) የሚወድ (የሚችል) እውነተኛው ክርስቶስ በፍፁም የለም። ሊኖር የሚችለው በዳንኤልና መሰሎቹ እኩይ ህሊና (አእምሮ) ውስጥ የተቀረፀ ወይም የብልፅግና ወንጌል (የአብይ ነቢያት) እንደሚሉን ከአብይ ጋር በቤተ መንግሥት ተሰይሞ የመከራውንና የውርደቱን ሥርዓተ ፖለቲካ እያራዘመ ያለው እጅግ ክፉ መንፈስ   ነው።

የመፀፀትና ከስህተት የመመለስ ሰብአዊ ባህሪ ላልፈጠረበት እና ይልቁንም ወደ አስከፊው የኢሰብዊ ቁልቁለት ለሚወርድ ፍጡር ሁሉ ጥሩ ማሳያ ከዳንኤል የተሻለ ፈፅሞ የለ። ይህንን ግልፅና ቀጥተኛ አገላለፄን ለግልብ ስሜት በማይጎረብጥ ሁኔታ ብገልፀው ደስ ባለኝ ነበር። ዳንኤል ክብረት አታሎ ፣ መስሎና አስመስሎ የመኖር ባህሪው አብሮት የኖረ (ምናልባትም አብሮት ያደገ) ሊሆን እንደሚችል በርግጠኝነት መናገር ባይቻልም መገመት ግን አያስቸግርም። ይህ ግን የራሱና ምናልባትም በእርሱ ዙሪያ የነበሩና ያሉ ወገኖች ጉዳይ ነውና ለእርሱ/ለእነርሱ የሚተው መሆን እንዳለበት በሚገባ እረዳለሁ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ዮናስ ብሩ፤ የጭራቅ አሕመድ አዛኝ ቅቤ አንጓች

ይህ አይነት እጅግ አደገኛ  ባህሪ አድጎና ጎልብቶ የፖለቲካውን ቤተ መንግሥትና መንበረ ሃይማኖትን እየቀላቀለ አገርንና ወገንን ለአስከፊና ማለቂያ ለሌለው መከራና ውርደት ሲዳርግ እየታዘቡ ማለፍ ግን ለሰማያዊውም ሆነ ለምድራዊ ህይወት ፈፅሞ  ፀር ነውና በግልፅና በቀጥታ መነጋገሩ ነው የሚበጀው። የዳንኤል ክብረትን የቤተ መንግሥት አማካሪነት  ምንነትና እንዴትነት ከመር ለተከታተለና ሚዛናዊ ህሊና ላለው የአገሬ ሰው ይህንኑ መሪር እውነታ ፈፅሞ አይስተውም። እናም ለዚህ ነው አካፋን አካፋ ከማለት ይልቅ ልፍስፍስ ምክንያት እየደረደሩ የተለየ ለውጥ መጠበቅ ወይ ድንቁርና ወይም አድርባይነት ከመሆን የማያልፈው። እንደ ዳንኤል  ክብረት አይነት ተዋርዶ አዋራጆችና ክፉ ሰዎች ቢያንስ  ነውር ነው ለማለት የፖለቲካና የሞራል ወኔው በእጅጉ የሚጎድለው ትውልድ ስለ ግዙፉና ጥልቁ የነፃነትና የፍትህ ሥርዓት ለምንና እንዴት እንደሚደሰኩር (እንደሚያላዝን) ሲያስቡት በእጅጉ ያስጨንቃል።

ታሪካዊና ታላቅ የሚላቸው አገሩና ሃይማኖቱ በዳንኤልና  በመሰሎቹ የርካሽ ፖለቲካ ቁማርና ልክ የሌለው የግልና የቡድን ፍላጎት ምስቅልቅላቸው ሲወጣ ተግባራዊ የነፃነትና ፍትህ  ተጋድሎ ከመታደግ ይልቅ በየአዳዳባባዩ ፣ በየቤተ እምነቱና እና በአገኘው አጋጣሚ ሁሉ ባዶ እየየታና እግዚኦታ እያስተጋባ የሚቀጥል ትውልድ ስለ ዴሞክራሲና ዴሞክራሲያዊት  አገር የሚያስተጋባው ጩኸት በምድርም ይሁን በሰማይ ምናልባትም የሚሰማው እንጅ የሚያዳምጠው ፈፅሞ የለም።
ረቂቅ አእምሮና ብቁ አካል ሰጥቶ በቃል ብቻ ሳይሆን በቃልህና በተግባርህ ኑር ብሎ የፈጠረው እውነተኛው አምላክም እንዲህ አይነቱን ባዶ (ድርጊት አልባ) እየየታና እግዚኦታ ፈፅሞ  አያዳምጥም ከፖለቲካው  ትኩሳት ጋር የሚወጡና የሚወርዱ የሃይማኖት መሪዎችን በአግባቡና  በመልካም የልጅነት (የአማኝነት) መንፈስ ተሳስታችኋልና እንደ አባትነት በእውነት  ስለ እውነት ቆም ብላችሁ አስቡ ማለትን እንደ ድፍረትና እንደ ኩነኔ (ሃጢአት) የሚቆጥር ትውልድ ለዘመናት ከመጣበት የመከራና የውርደት ህይወት (ህይወት ከተባለ) ፈፅሞ መውጫ የለውም።!

አዎ! እንደ ዳንኤል ክብረት አይነት እጅግ አደገኛ አድርባዮች በዲያቆንነትና በሙአዘ ጥበባትነት ስም በአገርና በወገን ላይ እጅግ አስከፊና የማያቋርጥ የመከራና የውርደት ዶፍ ለሚያወርደው የሸፍጠኞችና የአረመኔዎች ሥርዓተ ፖለቲካ ራሳቸውን አሳልፈው የሸጡ ወገኖችን በአግባቡ ለመገሰፅና ለማረም ወኔው የከዳውን የሃይማኖት አባትነት በአግባቡና   በአክብሮት ትክክል አይደለም ማለትን እንደ ሃጢአት ወይም ብልግና  የሚቆጥር ትውልድ ስለ የትኛው የሃይማኖት ነፃነትና የሰብአዊ መብት  መከበር እንደሚናፍቅ  ለመረዳት በእጅጉ ይከብዳል።

የገዛ ራሳችንን ቅጥ ያጣ ውድቀት በአግባቡ ተቀብለን ወደ ትክክለኛው መንገድ መሰባሰብ ያለመቻላችን ክፉ አባዜ ተጠናውቶን እንጅ የገጠመንና እየገጠመን ያለው ግዙፍና መሪር  እውነታ ይኸው ነው። የመከራውንና  የውርደቱን ወይም በንፁሃን ደምና የቁም ሰቆቃ የተመረዘውን ሥርዓት (ቤተ መንግሥት)  እንደማነኛውም ሸቀጥ ህሊናቸውን   ሸጠው  የሚያገግሉትን እንደ ዳንኤል ክብረት አይነት ግለሰቦች ነውር ነው ከማለት ይልቅ ታላቁ ዲያቆን (ሙአዘ ጥበባት) እያለ ራሱን የሚያዋርድ ትውልድ የሸፍጠኞችንና የጨካኞችን የባርነት ቀንበር ተሸካሚ ሆኖ ቢቀጥል ከቶ ሊገርመን አይገባም!

የትናንቱና የዛሬው ለመግለፅ  የሚያስቸግር አጠቃላይ ውድቀታችን  መሪር ትምህርት ሆኖን የተሻለ ነገንና ከነገ  ወዲያን  ለመፍጠር  እንደምንችል ተስፋ  እያደረሁ አበቃሁ!

ተጨማሪ ያንብቡ:  ይቅርታ እና ይቅር ባይነት - በዲያቆን ዳንኤል ክብረት

 

5 Comments

  1. ወንድማችን ዲያቆን ክብረትም የቄሳርን ለቄሳር አስረክቦ በንስሃ እንደገና ተጠምቆ ወደ ቤተ ክርስቲያን ይመጣል የሚል እምነት አለ፡፡ የእስላሞቹ መጽሃፍ ምረቃ ላይ የዘላበደውን ግን እንዴት እንደሚያርመው ማወቅ ግን ይቸግራል፡፡

    • “የ እስላሞቹ” ስትል ውስጥህ በምን ያህል ጥላቻ እንደተሞላ ያሳያል ወዳጄ ፍቅርን ስበክ በ እስላሞች መሀል መኖርህን አትርሳ

      • ግግ ምን ነካህ ጥላቻን ምን አመጣው እዚህ? እኔስ ምን መሆኔን አውቀህ ነው ?የተቀባበለ መሳሪያ አትሁን እንጅ አደብ ጥሩ ነው ጥርስም አውጣ ሁል ጊዜ ልጅ አትሁን

  2. ዳኒ ችግር ሳይገጥመው አልቀረም በጣም ከስቷል ዶ/ር አብይም ያለውን ሁሉ አድርጎበታል ጭዱን እያሳየ ያልሆነ ቦታ ሳይለቀው አልቀረም፡፡ ዳኒ ኑሮ ወደ ሚዲያ ከመጣ ከሚቀጥለው ምርጫ አንድ ወር ቀደም ብሎ ነው እስከዛ ስንት ጉድ አለ፡፡ እንደ ዮናታን አክሊሉ ትምቢት ከሆነ ጥሩ ነገር አይታይም መቼም ዮናታን አክሊሉ፤እዩ ጩፋ፤እስራኤል ዳንሳ ትምቢት አብረው ነው የሚያዩት ጫት ካለ ምን ችግር አለ ሌላም ይቻላል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share