January 25, 2023
2 mins read

ከንቱ ሆይ! – በላይነህ አባተ

678888Wአእምሮ አሸክሞ በአምሳሉ ቢፈጥርህ፣
የሆድ ቀፈት ጋርዶህ ልቡና አልቦ የሆንክ፣
እንኳንስ ሰማዩ ላይ ሆኖ የሚያይህ፣
ምድሩም “ጉድ ነው” ብሏል ነገ የሚውጥህ፡፡

በሥራው መዝነው ብትባል ሰባኪን፣
በቀጣፊ እሰተንፋስ እንደ ትቢያ እምትበን፣
ወና ባዶ ቤት ነው መርምረው ገላህን፡፡

አሳልፎ ሰጥቶ እልፍ አእላፍ ሰማእትን፣
ሰላሳ ዓመት ከድቶህ ይሁዳን የምታምን፣
ልብህን ማን ሰልቦት ምን ነክቶት ናላህን?

አገር ስትቃጠል ሲያልቅ ዘር ማንዘርህ፣
ጀሮህን የደፈንክ ልሳንህን የዘጋህ፣
የቆረጥክ ለማለፍ አንደ ቅንቡርስ ውጠህ፣
ታልጋ ውስጥ ቀርቶ መቃበር እንቅልፍ የለህ፣
መለኮት ተሰማይ ታሪክ ተምድር ሲያሽህ፣
እንደ ጥጥ ባዘቶ አንስቶ ሲጥልህ፡፡

የምትሳሳለት ነፍስ ድሎት የሚወደው፣
እርጉዝ ስትታረድ ቅፍፍ እንኳ እማይለው፣
ተእርጅና በሽታ አንዴት ሊያመልጥ ነው፣
ሞትን በምን መስኮት ሾልኮ ሊዘለው ነው?

ሞልቶ አማይመርጉት ሆድ እያንሰፈሰፈህ፣
የማታመልጠው ሞት የሚረሳህ መስሎህ፣
ሕዝብ በእሳት ሲቃጠል ድምጥህን ያጠፋህ፣
እንደ አባ ጨጓሬ በሆድ አየተሳብክ፣
እንኳን አሕዛብን ሳጥናኤልን አስናክ፡፡

በዝምታ ድጋፍ ጭራቅ እየደገፍክ፣
ለአሳራጅ ዲያብሎስ ግብር እያስገባህ፣
ስንቱን የእግዚአብሔር ሰው አንገቱን አስቀላህ፡፡

ከንቱ ሆይ!

ህፃናት ሲሰው ደመ ነፍስ ያልጠራህ፣
ስስት ድሎት ፍርሃት እንደ ውርጭ ቀፍድዶህ፣
መኖር የቀጠልከው እንደ አህያ ታስረህ፣
መኖ እንደ አሳማዎች እየጎሰጎስክ፣
ቅንጣት እንዳትረሳ አንተም ትሞታለህ፣
ትንታ ወይ እድሜ በሽታ ሲው አርጎህ፣
ዘንግቶ እማይቀረው እንኳን ሞት አለልህ፡፡

በላይነህ አባተ ([email protected])
ጥር ሁለት ሺ አስራ አምስት ዓ.ም.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop