September 21, 2022
2 mins read

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሚያካሄደው ሕዝበ ውሳኔ የ541 ሚሊዮን ብር የበጀት ጥያቄ አቀረበ

308362382 425060986398163 583442255749157231 n
308362382 425060986398163 583442255749157231 n
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ውስጥ ለሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ ማስፈጸሚያ የሚያስፈልገውን የአምስት መቶ አርባ አንድ ሚልዮን ሁለት መቶ ሰባ ሺህ አንድ መቶ አራት ብር ከሰማንያ ሁለት ሳንቲም (የ541,270,104.82) በጀት ያቀረበው ለኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው።
ቦርዱ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር የሚገኙ ስድስት ዞኖች ማለትም የጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ጌዲዮ፣ ኮንሶና፣ ደቡብ ኦሞ ዞኖች እንዲሁም አምስት ልዩ ወረዳዎችን እነዚሁም የቡርጂ፣ አማሮ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ ልዩ ልዩ ወረዳዎች ላይ ሕዝበ ውሳኔ እንደሚያካሄድ ይታወቃል።
ቦርዱ በተጠቀሱት ዞኖችና ልዪ ወረዳዎች ላይ ሕዝበ ውሣኔ በማደራጀት ውጤቱን እንዲያሳወቅ በፌዴሬሽን ምክር ቤት የተጠየቀው ነሐሴ 12 ቀን 2014 ዓ.ም. በተጻፈ ደብዳቤ ሲሆን፤ በዚህም መሠረት ቦርዱ የሕዝብ ውሣኔውን ለማከናወን የሚያስፈልጉ ዝርዝር ተግባራትን በማካተት የድርጊት መርኅ ግብር አዘጋጅቶ አቅርቧል።
በሕዝበ ውሣኔው የድርጊት መርኅ ግብሩ ላይ የተጠቀሱትን አጠቃላይ ተግባራት ተፈጻሚ ለማድረግም የሚያስፈልገውን በጀት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Fano
Previous Story

እኔዎች (እኔያት) – በላቸው ገላሁን

307109249 636179791369674 2307424408475762334 n
Next Story

በኢትዮጵያ ተፋላሚ ኃይሎች መካከል ይደረጋል ተብሎ ስለሚጠበቀው ድርድር የአሜሪካ ልዩ ልዑክ ማይክ ሐመር ምን አሉ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop