ድምፃዊ ጌድዮን ዳንኤል የጎዳና ተዳዳሪ ሆኗል፤ የሕዝብን እርዳታ ይሻል

/

(ዘ-ሐበሻ) “ላጽናናሽ”፣ “በተራ” እና በሌሎችም በተሰኙት ሙዚቃዎቹ የሚታወቀውና 2 ሙሉ አልበም የሰራው ድምፃዊ ጌድዮን ዳንኤል በአዲስ አበባ የጎዳና ተዳዳሪ ለመሆን እንደተዳረገና እርዳታ እንደሚያስፈልገው አዲስ ጉዳይ መጽሔት ዘገበ።

በአዲስ አበባ ታትሞ የሚሰራጨው አዲስ ጉዳይ መጽሔት ጓደኞቹን ጠቅሶ እንደዘገበው ድምፃዊው የአእምሮ ህመም ምልክቶች ከታዩበት ረዥም ጊዜ ሆኖታል። መጽሔቱ ያነጋገረው የድምጻዊው ጓደኛ “ጌድዮን ካልጠጣ ሰላማዊ ሰው ነው ከጠጣ ግን በጣም ኃይለኛና ሰውን የሚያስቸግር ሰው ነው” ሲል ይገልጸዋል። ሌሎች ደግሞ ድምጻዊው ሊያገኝ የሚገባውን የሳይካትሪስት ህክምና አለማግኘቱ ለዚህ እንዳበቃው ይናገራሉ::

ጌድዮዎን በተለይ 2ኛ አልበሙን ካወጣ በኋላ ብዙም ተቀባይነት አለማግኘቱ ለዚህ የአእምሮ ችግር እንዳበቃው የሚገልጹ የቅርብ ወዳጆቹ አሉ። እንደ አዲስ ጉዳይ መጽሄት ከሆነ ይህ ወጣትና ጥሩ ብቃት ያለውን ድምጻዊ ሕይወት ለማስተካከል የሙያ አጋሮቹ፣ ማንኛውም ተቋም፣ እንዲሁም ግለሰቦች ሊተባበሩት ይገባል።

የጌድዮን 3 ሙዚቃዎችን ያድምጡ።



ተጨማሪ ያንብቡ:  ደኢህዴን በአጼ ምኒልክ ላይ የሰራው ዶክመንተሪ ኢህአዴግ ውስጥ ቅራኔ ፈጠረ * •በርካታ የብአዴን ካድሬዎች በሰንደቅ አላማ በዓል አልተገኙም

1 Comment

  1. I feel sorry to hear this ‘ I am the most listener of His betera tera meet Gedion when I first came to Addis from Asmara while i was catching taxi in Kazanches’ in 19967 he was very impressive person that I ever meet at that time and he was the most neat artist who cares too much on people when he approaches any person’ may God help this kind person

Comments are closed.

Share