«ሕወሓት ከአዲስ አበባ ሌላ ጉዳይ የለውም» ጌታቸው ረዳ

በትግራይ ክልል ላይ የተጣሉ ዕቀባዎች ከተነሱ እና የተቋረጡ አገልግሎቶች ከተመለሱ ሕወሓት የተኩስ አቁም ለማድረግ እና ለመደራደር ፍቃደኛ መሆኑን የግንባሩ ቃል አቃባይ ጌታቸው ረዳ ተናገሩ ። ቃል አቃባዩ ዛሬ ከዶይቼ ቬለ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ «ሕወሓት ከአዲስ አበበ ሌላ ጉዳይ የለውም» በትግራይ ክልል ላይ የተጣሉ ዕቀባዎች ከተነሱ እና  የተቋረጡ አገልግሎቶች ከተመለሱ ሕወሓት የተኩስ አቁም ለማድረግ እና ለመደራደር ፍቃደኛ መሆኑን የግንባሩ  ቃል አቃባይ ጌታቸው ረዳ ተናገሩ ። ቃል አቃባዩ ዛሬ ከዶይቼ ቬለ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ «ሕወሓት ከአዲስ አበባ ሌላ ጉዳይ የለውም» ብለዋል።
በአፍሪቃ ቀንድ የአፍሪቃ ሕብረት ልዩ ልዑክ ኦሊሴንጎ ኦባሳንጆ ከሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ጋር ተገናኝተው መነጋገራቸውን ያነሱት አቶ ጌታቸው ፤ የንግግሩ ይዘት  በሂደት ያለ በመሆኑ ዝርዝር ጉዳዮችን ከመግለጽ ተቆጥበዋል።
የሕወሃት ቃል አቃባይ ጌታቸው ረዳ ድርጅታቸዉ ይፈፅማቸዋል ስለተባሉ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች፣ ከሕዝብ ስለሚደርስበት ተቃዉሞ፣ ከዩናይትድ ስቴትስ ይሰጠዋል ስለሚባለዉ ድጋፍ፣ ከሌሎች ስምንት ቡድናት ጋር ስለመሰረተዉ ትብብር እና በተያያዥ ጉዳዮች ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች መልስ ሰጥተዋል።
ነጋሽ መሐመድ አነጋግሯቸዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  "ተገዥነታችን ለሕዝብና ለሕግ እንጅ ለአምባገነኖች ማስፈራሪያ አይደለም" - አንድነት

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share