ለዶ/ር አብይ አህመድ የቀረበ ጥሪ – ሰርፀ ደስታ

ወቀሳዬን ረዘም ያደረኩት እንዲያስተውሉት ነው፡፡ እኔም ብዙ ተስፋ ካደረጉና ቆይቶ ግን እጅግ ካዘኑ ነኝና፡፡ ለበርካታ ወራትም እንዲህ ያለ ጽሁፍ ጽፌ አላውቅም፡፡ በሁኔታዎች እጅግ ስለተበሳጨሁ፡፡ እርሶ ወደ ስልጣን እንደመጡ ብዙዎች የናፈቁትን ኢትዮጵያዊነት ያገኙ ስለመሰላቸው ስለእርሶም ሆነ አብረዎት ለነበሩ የለውጥ መሪዎች ትልቅ ድጋፍና ብዙ ምስጋናና ዝማሬም ሁሉ ሳይቀር ከሕዝብ ዘንድ ሲቀርብልዎት ነበር፡፡ ሆኖም ይህ ሁኔታ ብዙም አልቆየም፡፡ ምን አልባትም ሶስት የረባ ወራት እንኳን ሳይሆን ነበር በናፍቆት ከጠበቅንለት ኢትዮጵያዊነት ይልቅ በ27 ዓመቱ እንኳን  ወደ አላየንው እጅግ የከፋ የዘረኝነትና የሥርዓተ አልበኝነት ምልክቶችን ማየት የጀመርንው፡፡ በተለይ ደግሞ እርሶና የመሩት ቡድን አሜሪካ መጥቶ ከተመለሰበት ቀን ጀምሮ የሆነው ሁሉ ለማመንም በሚከብድ ሁኔታ እጅግ የከፋ እየሆነ መጥቶ ይሄው አሁን ያለንበት ደርሰናል፡፡

ያኔ መጀመሪያ ላይ በኢትዮጵያዊነት መንፈስ በተናገሩት የመጀመሪያው ንግግርዎና ከዛም በኋላ በተግባርም እስከሶስት ወር ገደማ ያየናቸው የመሰሉን ተስፋዎች ሁሉ ድንገት ክስም አሉ፡፡ በዛች አጭር የመጀመሪያዎቹ የሲመትዎ ቀናት ብዙ መሠረታዊ የነበሩ ጉዳዮች  ተቀይረው የተናፈቀው ማንነታቸውን ያዙ፡፡ ኢትዮጵያዊነትና የኢትዮጵያ ቀደምት መሪዎች በመሪዋ አንደበት በይፋ ሲወደሱ ሰማን፣ ከ20 ዓመት በላይ የዘለቀው የኢትዮ-ኤርትራን የጦርነት ስጋት ቀርቶ ዓለም ሁሉ ተዓምር በሆነበት ሆኔታ እርሶና የኤርትራው መሪ የሁለቱ አገራት የገጠር ቀበሌዎች ሳይቀር በጋራ ተራመዳችሁ፡፡ ለ27ዓመት ተከፍላ የነበረችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን አንድ አደረጉ (በእርሶ ውሳኔ ባይሆን ላለመዋሀድ ችግር እንደነበር እናውቀለን)፣ በተመሳሳይ በሙስሊሙም እምነት ተከታዮች ተፈጥሮ የነበረውን መከፋፈል ወደ አንድ አመጡ፡፡ እነዚህን ሁሉ ነገሮች አስታውሳለሁ፡፡ በእርግጥም ያኔ በነበረዎት በቃልም በተግባርም በተገለጠው የመሪነት ቁርጠኛ የሚመስል አካሄድዎ በእርግጥም በዓመታት እንኳን ሊታሰቡ የማይችሉ ክንውኖችና ድሎች በቀናቶች ሆነዋል፡፡ ለመልካም ነገር ሲነሱ እግዚአብሔርም በብዙ እጥፍ እንደሚያከናውንም በመጽሐፍ ያነበብነው በእውን በአገራችን ሲሆን አይተን ነበር፡፡  ሆኖም ከላይ እንደጠቀስኩት ጥቂት ወራት እንኳን በዛ መቀጠል አልቻለም፡፡ የ27 ዓመቱ የዘረኝነትና ጥላቻን ዘር በገፍ ማጨድ የጀመርንው ወዲያው ነበር፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  አሁንስ ሊመጣ ላለው ዝግጁ ነን?። - ዳዊተ ዳባ።

መጀመሪያ በብዙ ቦታዎች መንገጫገጩን ይረጋጋል ብለን ስንጠብቅ ጭራሽ ኢትዮጵያን በይፋ እናፈርሳለን እያሉ ከራሳችን ከተማ ከአዲስ አበባ የሚፎክሩብን በተግባርም ራሳቸውን ሲያደራጁና ኢትዮጵያዊነትን በፍጥነት ለመደምሰስ ሲዘጋጁ አየን፡፡  እዚህ ውስጥ ነበር የእርሶም ማንነት በብዙዎች ዘንድ ጥያቄ ውስጥ የገባው፡፡ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ነገሩን በእርጋታ ተጠባበቀ፡፡ ምንም የለም፡፡ በግልጽ በ27 ዓመት በኦነጋውያን፣ ኦሮሞ ምሁራ ነን በሚሉና በወያኔ በአንድነት የኦሮሞን ወጣት ከኢትዮጵያዊነት ሙልጭ አድርገው አውጥተው የእነሱ አስተሳሰብ ባሪያ እንዲሆን እንዳደረጉት ታዘብን፡፡ ብዙ ጊዜ ስለዚህ ነገር እኔ አስታውሼ ነበር፡፡ ጥንቃቄ ካልተደረገ አደጋ እንዳለ፡፡ በአይኑ ሲገድሉትና፣ ብዙ ግፍ ሲያደርሱበት የነበሩት ጠላቶቹን ፍጹም እንዳይመለከት ሆኖ ጠላቶቹ በሰበኩት በጥላቻ ትርክት ተጠመቀ፡፡ የኦሮሞን ማህበረሰብ በከፍተኛ የአገሪቱ የታሪክ ማማ ላይ ያስቀመጠውን የሚኒሊክን ሥርዓት ጭራቅ ተመስሎ ተተረከለት፡፡ ይህ ሥርዓት ደግሞ በእርግጥም ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን አፍሪካ በሙሉና የተጨቆኑ የዓለም ሕዝቦች ሁሉ ሳይቀር ቀና ብለው እንዲሄዱ ምልክት የሆነላቸው ነበር፡፡ ኦሮሞ ከታላቁ ጎበና ዳጬ ይልቅ ወሮበላውና ከማንነቱ አውጥቶ ለጠላቶቹ እየገበረ የሚነግድበት ጀዋር ጀግናው ሆነ፡፡ አዝናለሁ!  የሚኒሊክ ታሪክ ምን ዓልባትም ከ80 በመቶ የሚሆነው አመራር የነበረው ከዚሁ ማህበረሰብ ከወጡ አባቶች ነበር፡፡ ይገርማል፡፡ እንግዲህ እነዚህ ታላላቅ አባቶች ደምና አጥንታቸውን ገብረው አገር ሰርተውና ጠብቀው ያስረከቡትን አገር አፈርሳለሁ እያለ መደንፋት ቀጠለ፡፡ ውጤቱ ለወራዳ አስተሳሰብ ባሪያ መሆን ሆነ፡፡  ከዚህ የአእምሮ መታወክ እስካልተፈወሰ ድረስ ይቀጥላል፡፡ ቀጥሎ ይሄው የዛሬው ትውልደ ኦሮሞ ነፍጠኛን (አማራን) መጥላት መሠረታዊ እምነቱ አደረገ፡፡ ውጤቱንም አየነው፡፡

ይሄ በኦሮሞ ልጆች ላይ የተፈጸመው የጥላቻና ዘረኝነት መርዝ ወደሌሎችም በፍጥነት እንዲዘልቅ ተደረገ በዚቸው እረሶ በመሩባት ሁለት ዓመታት፡፡ ከእኛው ከተማ ይሄው ትዕዛዝ ይሰራጭ ጀመር፡፡ በድብቅ ሳይሆን በይፋ፡፡ ይሄ ሁሉ ሲሆን የእርሶ አስተዳደር ነገሮችን ሕግና ሥርዓት ከማስያዝ ይልቅ ለኢትዮጵያ ጠላቶች ከለላ ሰጭ ሆኖ አይተናል፡፡ አዝናለሁ በጥላቻና ዘረኝነት የተመረዘው ኦሮሞነት ከዛም ለዘመነታ ሲሸምቅ የነበረው የእስላማዊ ጸረ-ኢትዮጵያ ኦሮሞነት በኢትዮጵያውያን ሁሉ ላይ ጥላውን አጠላ፡፡ ኦሮሞነትንም በይፋ አዋረደ፡፡ የአባቶቹን ታሪክ ክዶ የወረበሎችን የጥላቻና ዘረኝነት ትርክት ሲጋት የኖረው ትውልድን ለማስነሳት አሳማኝ ጉዳይ ማንሳት አይጠበቅም ነፍጠኛ፣ ሚኒሊክ፣ የመሳሰሉት ማለት ብቻ ነው፡፡ በግልጽ ይሄው አየንው ወጤቱን፡፡ በነገራችን ላይ ሰሞኑን መንግስት የማያውቀው ሳተላይት የተባለው ነገር አሁንም ባይድበሰበስ እላለሁ፡፡ እኔ መንግስት መዋቅር ውስጥ አደለሁም፡፡ ግን ስለዚህ ጉዳይ ቀደም ብሎ አውቅ ነበር፡፡ ያወቅኩትም በይፋ ከወጣ በዛው በአዲስ አበባ በሚኖሩ ዲፖሎማቲክ ጽ/ቤጾች ነው፡፡ የጥቅምቱ ወር 86 ሰዎች (መንግስት ያመነው) ከተጨፈጨፉበት ቀደም ብሎ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የተንቀሳቃሽ ስልክ በሕገወጥ ወደ እነዛ ጭፍጨፋ ወደተደረገባቸው ቦታዎች እንደገባ የአንዳንድ መንግስታት የደህንነት ተቋማት ጠቁመው ነበር፡፡  መረጃውም ወጥቶ የነበረው ከደህንነት ጋር በተያያዘ ነበር፡፡ ይሄን ግን የእርሶ መንግስት አልተናገረም፡፡ ዛሬ ሳተላይት አገኘን ስትሉ እነዛ ሞባይሎችም ከቴሌ ውጭ በሆነ መስመር ሲሰሩ እንደነበር አሁን ነው የገባኝ፡፡ በወቅቱ የደህንነት ስጋት እንዴት ሊሆን እንደቻለና መረጃውን ያወጡት እንደተናገሩ ብዙም ትኩረት አልሰጠሁትም ነበር፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  በኢትዮጲያዊያን ላይ ሰቆቃ የሚፈጽመው የአብይ አህመድ ምንደኞች ይጋለጡ

ከላይ የጻፍኩትን ለማስታወስ ያህል ነው፡፡ በእነዛ ትቂት መልካምና ተስፋ በመሰሉን ወራት ብዙዎቻችን ኢትዮጵያን በአለን አቅም ሁሉ በመረባረብ አገራችን አሁን  ካለችበት የኑሮ ምስቅልቅል አውጥተን ሌሎች የደረሱበት እናደርሳለን የሚል ትልቅ እንቅስቃሴ ጀምረን ነበር፡፡ እርሶ ያሉት ከዲያስፖራ የሚሰበሰብ በቀን አንድ ዶላር ማለቴ ሳይሆን በሚሊየን የሚቆጠር ዶላር በተማሩ ኢትዮጵያውየን ወደ አገራችን ለማስገባት ብዙ ተስፋ አድርገን ነበር፡፡ ሐሳባችንም በተለያየ ዘርፍ ኢትዮጵያን ሊያለሙና በቴክኖሎጂ ሊያበለጽጉ የሚችሉ ትልልቅ ፕሮጀክቶች ላይ ያተኮረ ነበር፡፡

ያ አልፏል አሁን ለሁለተኛ ጊዜ ይሄን አጀንዳ መነጋገር ጀምረናል፡፡ ከብዙ ነገር አንጻር፡፡  ትውልድን፣ ሕዝብን፣ አገርን ወደተሻለ መቀየር እንችላለን፡፡ እንችላለን ስል አዎ እንችላለን! ለዚህ የምንፈልገው የኢትዮጵያ መንግስትን ቁርጠኝነት ብቻ ነው፡፡  በእልህና ቁጭት ነው ብዙዎች የተነሳሱት፡፡ ኢትዮጵያ የኢትዮጵያውያን እንጂ የወሮበሎች መፈንጫ ሆና ማየት አንፈልግም፡፡ ዛሬ እውቀትና ጥበብ የማይፈልግ ነገር ቢሆን ፖለቲካና አክቲቪስትነት ብቻ ነው፡፡ ሁሉም ሌላ ቀርቶ ገበሬው ሳይቀር የፖለቲካ ተንታኝ እየሆነ መጥቷል፡፡ ፖለቲካም ሆነ ሌላ የጥቂቶች እንጂ የ100 ምናምን ሚሊየን ሕዝብ ጉዳይ ሆኖ አገር ከመጥፋት አትድንም፡፡ ያ በአመጽና ሕዝብን ሁሉ ወደ ራሱ ገበያ ለመሳብ በሴራ መርዘኛ ሐሳቦችን ወደሕዝብ እየዘራ እርስ በእርሱ ሲጫረስ የኖረ የ60ዎቹ ትውልድ ያመጣብን ችግር ነው፡፡ ከዚህ በኋላ የምንፈልገው ጥቂት በውዴታቸው እዛው ፖለቲካቸው ላይ ቀርተው ሌላውን ሕዝባችንን ወደ አገሩ መመለስ ነው፡፡ ወደ አገሩ ስል ወደ ኢትዮጵያዊነት፣ በቁጭትና በሚደርስበት ራዕይ ማሰማራት፣ ማዘመን፡፡ ይሄን ለማድረግ ብዙዎች እየተሰባሰብን ነው፡፡ ይሄን የምለው አሁንም ይሰመርበት በስሜት አደለም፡፡ የምናውቀው የሚቻል ነገር ስላለ እንጂ፡፡ በዚህ ሂደት የነበሩ የአስተሳሰብ ጋሬጦች እንቅፋት እንዳይሆኑ ግን መንግስት ቁርጠኝነቱን ያሳይ፡፡ ይሄ ጥሪዬ ከብዙ ወራት በኋላ ነው፡፡ ክብር የሚሆነው ሕዝባችንንና አገራችንን የምንለውጠበት ሥራ ነው፡፡ ኦሮሞነት፣ አማራነት ወይም ሌላ አደለም፡፡ እኔ እነዚህ ቃላቶች የምጠቀመው ሰው በዚህ ስለለመደው እንጂ ዛሬ ኦሮሞ፣ አማራ ወይም ሌላ የተባለውን ሕዝብ ማንነቱን አውቀዋለሁ፡፡  አሁን የምጠይቅዎት የኢትዮጵያውያን (በዋናነት የምሁራን) አገራችንን ለማልማትና የሕዝባችንን ኑሮ ለመቀየር የእርሶ አስተዳደር ቁርጠኝነቱን ሊያሳየን ይችላል? ሐሳብ ሰጥተን ዞሮ ለማለት አደለም በተግባር ራሳችን ሰርተን ለማሰራት እንጂ፡፡ ትውልድንና አገርን ማዳን ግዴታችን ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የመንጌ! ኪሲንግ

አመሰግናለሁ!

ቅዱስ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይባርክ! አሜን!

6 Comments

  1. አሁን ወደገንቢ ፅሁፍህ እየተመለስክ ነው:: የገለፅከው በሙሉ አዎ ሆኗል ከዚህም በበለጠ:: የረሳኸው

    1. ዐቢይ መለኮታዊ ሀይል እንደሌለው:: ሰው ነው አዲስ ነው ሊሳሳትም ይችላል:: ህዝቡም ዲሞክራሲና ነፃነትን ስላልኖረበት አልለመደም

    2. 27 አመታት ዘረኝነትን በአደባባይ ያስፋፋው የህውሀት ድርጅት አልተደመሰሰም ያውም በይበልጥ በዘረፈው ሀበት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በመላው ኢትዮጵያ የላቋረጠ ሽብርና ግጭት እንዲሁም መፈናቅል ሆን ብሎ ማካሄዱ::የግጭቶች ሀላፊነት ተጠያቂው አሸባሪው የህውሀት ድርጅት ነው:: ይህ ይሰመርበት:: ያፈጠጠ ሀቅም ስለሆነ:: እንዳንድ ሰዎች በዐቢይ ዘመን ይህ ሆነ ሲሉ የእውቀት አድማሳቸውን እንድገምት ያስገድደኛል::

    3. የእንተ ቢጢዎችና አክቲቪስቶች እንደ እስክንድር ያሉ ጀብደኞች ዐቢይን ደግፎ እንዲያሸንፍ ከማበረታት የወያኔ መንገድ ጠራጊዎች በመሆን ዐቢይ 100 ኪሎ ጤፍ ጀርባው ላይ ተሸክሞ ማራቶን ሮጦ እንዲያሸንፍ መጠበቃቸው ስራውን አክብዶታል:: በጅምላ ኦሮሞዎን ሁሉ መወንጀል ዐቢይን አይረዳም::

    4. ዛሬ ሁሉም ግልፅ ወጥቷል:: ሁለት መንግስት በኢትዮጵያ ታይቷል:: የትግራይ ረፑብሊክ ልክ እንደ ሰሜን ኮርያ የጦር ሀይሉን እያሳየ ነው:: ዐቢይ ጦርነት አይፈልግም:: የትግራይ ህዝብ ወገናችን ነው:: ህውሀት በመሞቻው ወቅት ኢትዮጵያን አፍርሶ መቀበር ይፈልጋል:: እኛ ኢትዮጵያውያን ልዩነታችንን ወደሗላ አድርገን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጋር የምንቆምበት ወቅት ቢኖር አሁን ነው:: የተጀመረው ህግና ስርአት መሬት ላይ የሚወርደው እኛም እንደ ህዝብ አብረን ስንቆም ብቻ ነው::
    ኢትዮጵያዊነት አሸናፊ ነው!

  2. Sadly your plea is useless. You are barking the wrong tree. It will never happen unless the beneficiary is the oromo. If you want it to work you just need to commit to the oromo and be subservient to the oromo. Literarly you have to be one of them and sacrifuce the Amhara with them to their end. I hope you wouldn’t do that individually or in a group. Wether you believe it or not the so called ethiopian constitution has to be changed and abiy has clearly said he will not change it for his life.

  3. የአስተሳሰብ አድማስህን እንዲህ ባለው ገንቢ መልኩ መቀየርህን ሳስተውል አብዝቶ ደስታ ተሰማኝ።ይህን የምለው ሁላችንም የሚከተለውን ነገር ስላልተረዳን ስላላወቅን እንጂ ክፉዎች ሆነን አይመስለኝም ።
    ወዳጄ ሰርፀ ይህን ጊዜ ቀድመን እንድንገምተው ዕድል ተሰጥቶናልና እጃችን ውስጥ የገባውን በማወቅ ይህንን ለማስፋፋት በህብረት በመከባበር በመተማመን አሻግረን ማየት ይኖርብናል ብዬ አስባለሁ ።
    በሃገራችን ጉዳይ ላይ የሚፅፍ ሰው ሀገሩ በልማት በዕድገት በቴክኖሎጂ ከፍ እንድትል የሚፈልግ ከሆነ ማበረታት ያለበት ብዬ የማምነው በዜጎች መካከል መተማመንን ለማምጣት ነው መስራት ያለበት።
    መተማመን ከመጣ መከባበርና መተባበር ይከተላሉና።
    ያለንን እንወቅበት ነው መልዕክቴ

  4. ጥሩ ብለሃል ፀሐፊዬ ነገሩ ወዲህ ነው እናቴ የእንቁላል ጊዜ ብትቆጭኝ ኖሮ ዛሬ በሬ ባልሰረኩ ነበር የሚል ሆኖብን እንጅ

  5. Wealthy tigarians are arming and sponsoring for overinflated tigray republic on the graveyard of Amaras. Wealthy oromos are busy arming qerros who are exterminating Amaras and other orthodox christians to create overinflated islamic republic. The Army and police forces are used to keep Amaras unarmed and vulnerable. Amaras are massacred in mass everywhere. If i can suggest, these millionaires can help to save the Amaras, Orthodox christians, Ethiopians and Ethiopia. Educated and wealthy, that is what Ethiopia needs right now but not for profit investment though. Saving a country and its people comes before investment and development. Begging does not take anywhere.

  6. ለ27ዓመት የተሠበከን የዘር ጥላቻ ለዶ/.ር አብይ ብቻ ከመሰለን እንደኔ የተሳሳትን ይመስለኛል ፡፡ስለዚህ ከዚህ በፊት የተሠበከዉን
    ኢትዮጵያዊነት ጥላቻን በጋራ ልንከላከል ይገባል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share