በአዲስ አበባ በረዶ የተቀላቀለበት ዝናብ ጥሎ በንብረት ላይ ጉዳት አስከተለ

July 10, 2013

(ዘ-ሐበሻ) ዛሬ በአዲስ አበባ እና በአካባቢዋ በረዶ ቀላቅሎ በጣለ ዝናብ በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን ከስፍራው ክለዘ-ሐበሻ የመጡ መረጃዎች አመለከቱ።
በአውቶቡስ ተራ፣ በአፍንጮ በር ድልድይ እና በሌሎችም አካባቢዎች በጣለው ዝናብና በረዶ መኪናዎች እና ሰዎች ለመጓጓዝ ችግር ገጥሟቸው ሲሰተጓጎሉ ውለዋል ያሉት የዘ-ሐበሻ የመረጃ ምንጮች በተለይም የንግድ ቤቶች ውስጥ እየተዝናኑ ያሉ ሰዎችን ሁሉ ውሃው ጉዳት እንዳደረሰባቸው ተናግረዋል። ምንጮቹ አክለውም ውሃው በአንዳንድ የመኖሪያ ቤቶች ውስጥ ሳይቀር በመግባት ጉዳት ያደረሰ ሲሆን ማህበረሰቡም ከቤቱ ውስጥ የገባውን ዝናብ ለማውጣት ሲታገል በአንዳንድ ሰፈሮች ታይቷል።

የዛሬውን ዝናብ ተከትሎ ጋዜጠና ገጣሚ ፋሲል ተካልኝ በፌስቡክ ገጹ የሚከተለውን ከፎቶ ግራፍ ጋር አስፍሯል።
____ወይ ጥጋብ!¡!____
የአፍሪካ መዲና..ውዴ አዲስ አበባ
ከባቡሩ በፊት..አሰኘሽ ወይ ጀልባ?!?
* * *
___ፋሲል ተካልኝ አደሬ___

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop