አስገደ ገ/ስላሴ ለህክምና አሜሪካ ገቡ

June 18, 2013
(ፎቶ – ኢትዮሚድያ)
አስገደ ገ/ስላሴ ለህክምና አሜሪካ ገቡ 1

የታቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባል ሆነው በፖለቲካ አቋማቸው ብቻ ሁለቱ ልጆቻቸው ያላንዳች ጥፋት እስርቤት መወርወራቸውን አይተው በቅርቡ ለኢትዮጵያ ህዝብ “ይግባኝ” ያሉት አቶ አስገደ ገ/ስላሴ ታመው ለህክምና አሜሪካ ገብተዋል።
አቶ አስገደ በአሁኑ ጊዜ በጆርጅ ዋሽንግተን ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል እየታከሙ ይገኛሉ። አሕፈሮም አስገደ የተባለው ልጃቸው ደግሞ መቀሌ በሚገኘው ቀዳማይ ወያኔ ፖሊስ ጣብያ ታስሮ ይገኛል። ወጣቱ አሕፈሮም “ዳኛው የሉም” እየተባለ የዋስ መብቱን አስጠብቆ ሊወጣ ባለመቻሉ እዛው ፖሊስ ጣቢያ እንደታሰረ 54 ቀናትን ቆጥሯል።
በእስር ቤት ሲማቅቅ ቆይቶ ያላንዳች ክስ የተለቀቀው የማነ አስገደ ደግሞ እስርቤት ባደረበት ህመም 22 ቀን ሆስፒታል ከተኛ በኋላ በአሁኑ ጊዜ በቤቱ የአልጋ ቁራኛ ሆኖ ይገኛል።
አቶ አስገደ ሆስፒታል መግባታቸውን ያወቁ ኢትዮጵያውያን ገሚሶቹ በአካል፣ ሌሎቹም በኢሜይልና በስልክ በጎ ምኞታቸውን እና የትግል አጋርነታቸውን ገልጸውላቸዋል።

 

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop