December 21, 2022
2 mins read

እሥከቀራኒዮ (የመኮንን ሻውል ግጥም)

ውዴ ሆይ ! እስከቀራኒዮ እዘልቃለሁ
ለንፁህ ፍቅርሽ አንገቴን እሰጣለሁ
ውዴ ህይ ! አልከዳሽም
ለሥጋ ተገዝቼ በሆድ አላውጥሽም ።
አመኚኝ ውዴ ሆይ !
እኔ አንቺን ነኝ ፣ አንቺ እኔነሽ
ሥጋዬ፣አጥንት ፣ ደሜ …
መላ ህዋሴ ነሽ
ውዴ ሆይ !
ከቶ ማንም አይለየን ፤ በጅንጉርጉርነታችን
ውበትን በተጎናፀፈው ነብራዊ መልከችን ።
ቢለያይ አፍ የፈታንበት ቋንቋችን
አንድ ነን እኮ በኢትዮጵያዊነታችን ።
የማይበጠሥ እኮ ነው ፤
የአደዋ ማተብአችን ?
ውዴ ሆይ !
በጭራሽ !
አልክድሽም ፤ …
በህይወት እሥካለሁ ።
የወደድሺኝ …ሰው በመሆኔ
የወደድኩሽ …ሰው በመሆንሽ …
እንደሆነ በሚገባ አውቃለሁ ።
ውዴ ሆይ !
የእኔ ብርሃን እኮ ነሽ …
ጨለማን የምትገፊልኝ …
እንዳልሰናከል
ምርኩዝ የምትሆኚኝ …
ሊነጣጥለን ቢቃጣ ፣ ዘረኝነት ገኖ …
ውዴ ሆይ ! …
ለአንቺ ስል እዘልቃለሁ ፤ እሥከቀራኒዮ !
እሥከሚሰቅሉኝም ሥለፍቅርሽ አዜማለሁ
ውዴ ሆይ ! ሥለ ሰውነትሽ እሰዋልሻለሁ ።
ከመሰዋቴ በፊት የማዜምልሽን ዜማ
እሥቲ ለአፍታ አገር ይሥማ ።
” ውዴ ሆይ ! ፈፅሞ አትሥጊ
አየነጣጥለንም ብሽቁ ፕለቲካ
ቋንቋን በሰብዓዊ መብታችን ላይ እየተካ ።
ነገ ተነገ ወዲያ ዜጎች ይነቃሉ
‘ እኛ ሰው ነን !
እኛ ሰው ነን !
ቋንቋ አይደለንም !
ቋንቋ አይደለንም ! ‘
የሚል መፈክር ይዘው
የቋንቋን ጣዎት ለመከስከስ
እስከ ቀራኒዮ ይዘልቃሉ ። ”
ውዴ ! ሆይ !
መሰዋትነት በከንቱ እንደማይቀር አውቃለሁ ።
ውዴ ሆይ !
ለፍቅር ብለሽ ፣
ደጋግመሽ …
መሰቃየትሽን እያየሁ
ዘወትር አነባለሁ ።
ውዴ ! ፍቅሬ ! አካሌ ! …
እጅግ እወድሻለሁ …
አንቺ ከጎኔ ሆነሽ ባታፅናኝኝ …
ባትደግፊኝ …
አጋር ና ሀገር ባትሆኚኝ
እንዴት እንዲህ
ጀግና ኢትዮጵያዊ
ሆኜ እገኛለሁ ።

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ
ታህሳስ 12 / 2015 ዓ/ም ተፃፈ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Ephrem Madebo
Previous Story

አዲስ አበባ ወይስ አዲስ አባባ? – ክፍል ሁለት

Geday Abiy
Next Story

ለዶ/ር አብይና ብልጽግና ፓርቲ እጅግ አሰቸኳይ የዜጎች እልቂት መፍትሄ መልክት

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop