October 16, 2013
3 mins read

በአዲስ አበባ የዳቦ እጥረት ተከሰተ

bread

በአዲስ አበባ ከተማ ዳቦ በበቂ ሁኔታ እየቀረበ እንዳልሆነ ተገለፀ፡፡ የከተማው ነዋሪዎች በየዳቦ ቤቱ ዳቦ ለመግዛት ሲሄዱ ዳቦ አለመኖሩ እየተነገራቸው በተደጋጋሚ እየተመለሱ መሆኑንና ችግሩም እስካሁን እንዳልተቀረፈ ሰንደቅ ጋዜጣ በጥቅምት 6 ቀን 2006 ዓ.ም. እትሙ ዘግቧል፡፡ እንደጋዜጣው ዘገባ ከሆነ አንዳንድ ዳቦ መሸጫ ሱቅ የሥራ ኃላፊዎችና ባለቤቶች በተገኘው መረጃ መሰረት በዳቦ መሸጫ መንግሥት ከተመነው ዋጋ አንፃር ሲታይ
አንድን ዳቦ ለገበያ በማቅረብ የሚገኘው የትርፍ መጠን አነስተኛ በመሆኑ ዘርፉ አበረታች አለመሆኑ ተገልፁዓል፡፡
እጥረቱን በተመለከተ ጋዜጣው ያነጋገራቸው በንግድ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ምክትል ኃላፊ አቶ አብዱራህማን ሰይድ፤ የዳቦ ዋጋ ትርፍን በተመለከተ መንግስት ተመኑን ሲያስቀምጥ ያሉትን ወጪዎች ታሳቢ
አድርጎ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የተፈጠረውንም የዳቦ እጥረት በተመለከተ ስንዴ በእህል ንግድ በኩል ተገዝቶሀገር ውስጥ ሲገባ መንገድ ላይ በተፈጠረው መዘግየት የተፈጠረ መሆኑን ኃላፊው አመለክተዋል፡፡ ያም ሆኖ እህል ንግድ ከመጠባበቂያ ክምችቱ በማውጣት ለአዲስ አበባም ሆነ ለክልል የዱቄት ፋብሪካዎች እንደተቀመጠላቸው ኮታ እንዲያከፋፍል መሆኑንም ጨምረው ገልፀዋል፡፡ መንግስት በሀገሪቱ የተከሰተውን የዋጋ ንረት ለመቆጣጠር በሚል በ 2003 ዓ.ም. በበርካታ የፍጆታ ሸቀጦች ላይ የዋጋ ተመን ከጣለ በኋላ በስተመጨረሻ የሌሎች ተመን ሲነሳ የስኳር፣ የዘይትና የስንዴ ምርቶችን የማከፋፈል ስራ ሙሉ ለሙሉ በመንግስት ቁጥጥር ስር ውሎ እስከ ዛሬም እንደቀጠለ ነው፡፡ይሁን እስካሁን በስርጭቱ ረገድ በስኳር ላይ ተደጋጋሚ ችግር እየታየ ሲሆን አሁን ደግሞ በዳቦ ስንዴ ላይ ችግሩ እየተንፀባረቀ መሆኑን ሰንደቅ ጋዜጣ ዘግቧል፡፡

2 Comments

  1. THe habesha Akatariwoch Ye Amara hizben atetru beselam yenurbet dabo tefa weha tefa eyalachu kemengstachin atatalun eja beselam eyenoren new.Enante Americawin enji Ethiopiawisoch an aydelachum wend kehonachu dabo beltachu Weyane metluten tegafetu lefesfe hula Negere feji.tamaje demo Amaran ayweklem tarikachin atabelashut tamaje ye welkait tigre enji gondere hono ayakem selezi benatachu yeamaran hizb atawezagebu leboch

  2. *መጀመሪያ ይህንን ዳቦ ለኢትዮጵያ ዜና የሰራበት ጋዜጠኛ አሸባሪ ነው ይቀጣል፡ አዲስ አባባ ይህንን የመሰለ ዳቦ ይጋገር ነበረው በዘመነ እንኮዬ ነበር። ዳቦ ድሮ ቀረ አሉ (በድንጋይ ዳቦ ዘመን) አሁን ኮብል እስቶን ሆኗል። በአሁን ወቅት ይህንን ዓይነት ዳቦ የሚበላ ሕዝብ ካለ መካካለኛ ገቢ ካላቸው ሀገሮች ጎን መሰለፍ አደለም ትከሻቸው ላይ ተቀምጠን እንኮኮ አድርገው ዓለም ያዞሩን ነበር።
    *ፎቶ አላግባብ መጠቀም የሚከለክል ሕግ የለም?
    -እኔ የምለው የዳቦው ቁመት ነው ያጠረው? ወይንስ
    -ዳቦ ጠፋ ለማለት ሳቃችሁ መጥቶ?
    -ወይም የሀገሪተን ሥምና ኢህአዴግን ላለማስቀየም? ምን ኢህዴግን ሻቢያን እንበል እንጂ የሚመሩትም የሚያወሩትም፣ የሚገዙትና የሚሸጡትስ እነሱ አደሉምን ? ስብሃት ነጋ ይመስክሩ።
    -አሃ! ዳቦ ያጠረው አዲስ አባባ ብቻ እነጂ ሌላው አካባባ ክልኢለ ወረዳ ቀበሌ ዳቦ እረዝሞ(ጥጋብ)ሆኗል ማለት ነው? -ኢትዮጵያ የምታድገው ስንዴ ከውጭ በመግዛት ነው?
    -ደን ተቃጥሎ ሩዝ ለዓረብ የሚመረትበት ሀገር፤ጫት በሻይ ለህፃናት የሚቀርብብት ሀገር!ጠፋን በእጥረት መሸወድ?
    -የዋጋ ንረት ነው ያሳጠረው? የዋጋ ተመኑ ነው ያጠፋው? የተቀመጠን ዱቄት አውጥቶ መጋገር ሠራተኛው ሰነፈ? — – አሥር ስኳር ፋብሪካ ተመስረቶ ዛሬም ስኳር ቀምሰው የማያውቁ ገበሬዎች አሉ? ለነገሩ ስካር ሚኒስትሩ ሃኢማኖት ጉዳይ ኅላፊ ደርበው መግለጫ ይሰጣሉ ጭራስ የም/ጠ ሚኒስትሩ በሃይማኖት ጉዳይ አደናባሪ ሆነው ተሾሙ፡ በለው!
    የጠ/ሚኒ ቃል አቀባይ አቶ ኀይለማርያም ደስ አላኝ የሚሉት “የስንዴ ምርት ተርፎ ወንዝ ልጨምር ነበር። አይ ኤም ኤፍ፣ ወርልድ ባንክና የነጭ ቅጠረኛውን ግንቦት ፯ እና የአካባቢውን የቀጠናው አተራማሽ የኤርትራን መንግስት ወሬ ጠልተን እነጂ ጎተራው ሞልቶ መንግስት አልባ የሆነችውን ጎረቤት ሀገር ልንረዳ ተጋጅተናል” ሲሉ ነበር። አቤት መቦጠርና መወጣጠር የማይደክማቸው ግለሰብ፣ እንደኋላዊት ታጋይ አዜብና እንደ አቶ ኅይለመለስ ድንፋታና የሙት ረዕይ ሳይሆን እንደባለቤታቸው ቀዳማዊት ሮማን ተስፋየ “ኢትዮጵያ በመጽሐፍ ቅዱስ እንደተጻፈው የተባረከችና የተቀደሰች ምድር ትሁን!” አሜን !!! በቸር ይግጠመን

Comments are closed.

በዛበብ
Previous Story

‹‹ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ መሞታቸው ተነግሮናል›› – (አቶ ስብሃት ነጋ)

አረፋ በዓል
Next Story

የመጅሊስ እና የዑለማዎች ምክር ቤት የይፍረሱ ክስ ለሰበር ሰሚ ችሎት እንደሚቀርብ ተገለፀ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop