Hiber Radio: በኑሮ ውድነቱ ሳቢያ የዓመት በዓል ገበያው ቀዝቅዟል

/

የህብር ሬዲዮ ዕሁድ ጳጉሜ 3 ቀን 2005 ፕሮግራም

እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሰዎ

በዓሉ የሰላምና የጤና እንዲሆን መልካም ምኞታችን ነው !

<... ሎስ አንጀለስ ሊትል ኢትዮጵያ ተብሎ በስሙ በውጭ አገር መንገድ የተሰየመለት ብቸኛ ቦታ ነው። በዚህ ተሰባስበን ኢትዮጵያውያን የአዲስ ዓመት በዓልን እናከብራለን።ይሄ በሎስ አንጀለስ ብቻ ሳይሆን በርካታ ኢትዮጵያውያን ባሉባቸው ቦታዎች መጠሪያችንን ማኖር ይቻላል...>

በሎስ አንጀለስ ዕንቁጣጣሽን አስመልክቶ የተከበረውን ዓመታዊ ፌስቲቫል አስመልክቶ ሊትል ኢትዮጵያ እንዲሰየም ጥረት ካደረጉት አምስት ሴቶች አንዱዋ ሜሮን አሀዱ ለህብር ከሰጠችው ቃለ መጠይቅ የተወሰደ

<<...በናዝሬት/አዳማ ሰልፉ ከመደረጉ በፊትና በሰልፉም ወቅት የተለያዩ ተጽኖዎች ነበሩ። እነዛን ተቋቁመን ከ15 ሺህ በላይ የከተማዋ ነዋሪ አደባባይ ወጥቶ ሶስት ኪሎ ሜትር ያህል በከተማዋ መንገዶች ተዘዋውሮ ተቃውሞውን አሰምቷል።...ሕዝቡ የራሱን መፈክር ያሰማና ብሶቱን ይገልጽ ነበር...ይህ እንቅስቃሴ ነጻነት እስኪገኝ ድረስ የሚቀጥል ነው...>>

አቶ ዳንኤል ተፈራ የአንድነት የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ የሃዝሬት/አዳማውን ሰልፍ አስመልክቶ ለህብር ከሰጡት ቃለ መጠይቅ የተወሰደ።ለዲያስፖራው የአዲስ ዓመት መልክታቸውም ተካቷል።

ልዩ የበዓል መሰናዶ አካተናል

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ
<<...ይሄ መንግስት እኮ በህክምና ቋንቋ ሞቷል። የቀረው ቀብሩ እንዴት ነው የሚፈጸመው የሚለው ነው...>> አባ መላ በቬጋስ የአዲስ ድምጽ አገራዊ ጉባዔ ላይ ተገኝቶ ከሰጠው ማብራሪያ (የተወሰነውን አካተነዋል)

<<...የበዓል አመጋገባችን በተለይ ቅባት የበዛበት ነገር ማብዛቱ ለጤና ጉዳት አለው። በእነዚህ ላይ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል...በተለይ ለአዲሱ ዓመት አምስት ምክሮች አሉኝ እነዚህም...>>

ዶ/ር ኤፍሬም መኮንን ከአትላንታ የበዓል አመጋገባችን መሰረት አድርገን አነጋግረናቸው ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት)

(ሌሎችም ቃለ መጠይቆች አሉን)

ዜናዎቻችን

በኑሮ ውድነቱ ሳቢያ የበዓል ገበያው ቀዝቅዟል

ዶሮ 180 ብር፣በግ መካከለኛ 1500 ብር፣ በሬ ከ10 ሺህ እስከ 15 ሺህ ብር አንድ ዕንቁላል 2 ብር ከ70ሳንቲም ተሽጧል

አሜሪካ ሶሪያን ማጥቃቱዋ በኢትዮጵያ ንግድ ላይ ተጽዕኖ ይፈጥራል ተባለ

የኢንጂነር ሀይሉ ሻውል <<ሕይወቴና የፖለቲካ እርምጃዬ>> የተሰኘው መጽሐፍ ነገ ለንባብ ይበቃል

የኢራን ዲፕሎማት ኦባማ ሲሪያን ካጠቁ አንዱዋን ልጃቸው ትታፈናለች ሲሉ አስጠነቀቁ

የኢትዮጵአው ዋልያ በሰሞኑ ድል የብራዚል ጉዞውን እያመቻቸ ነው

ሌሎችም ዜናዎች አሉን

ተጨማሪ ያንብቡ:  የግእዝ ቁጥሮች በአኀዝና በፊደል
Share