13 ባለስልጣናት ተሾሙ

July 4, 2013

(ዘ-ሐበሻ) ጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም ደሳለኝ አቶ በረከት ስም ዖንን እና የአዲስ አበባ ከንቲባ የነበሩትን አቶ ኩማ ደመቀሳን የጠቅላይ ሚንስትሩ የፖሊሲ ጥናት እና ምርምር አማካሪ ሚንስትር አድርገው ከሾሙ በኋላ በተጨማሪም ለ11 ተጨማሪ ባለስልጣናትን ሹመት ማስጸደቃቸው ከአዲስ አበባ የመጣው መረጃ አመለከተ። እንደመረጃው ከሆነ ም/ል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን በጣምራ ይዘውት የነበረውን የትምህርት ሚ/ርነት ሥልጣን ተገፈው “የአማራው ሕዝብ ጠላት” በሚል ቅጽል ስም የወጣላቸው አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ስልጣኑን እንዲይዙት ተደርጓል።

በቅርቡ ከስልጣን በተባረሩት የፍትህ ሚ/ሩ ብርሃን ሃይሉ ምትክም አቶ ጌታቸው አምባዬ መሾማቸው ተገልጿል። አዳዲሶቹን ሹመኞች ዝርዝር እነሆ፦

1. አቶ ደመቀ መኮንን – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር

2. አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ወላሳ – የትምህርት ሚኒስትር

3. አቶ ሬድዋን ሁሴን ራህመቶ- የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሚኒስትር

4. አቶ አህመድ አብተው አስፋው – የኢንዱስትሪ ሚኒስትር

5. አቶ ወርቅነህ ገበየሁ ነገዎ – የትራንስፖርት ሚኒስትር

6. ወይዘሮ ሮማን ገብረስላሴ መሸሻ – በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር

7. ወይዘሮ ደሚቱ ሃንቢሳ ቦንሳ – የሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ሚኒስትር

8. አቶ ጌታቸው አምባዬ በለው – የፍትህ ሚኒስትር

9. አቶ በከር ሻሌ ዱሌ – የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር

10. አቶ በለጠ ታፈረ ደስታ – የአካባቢ ጥበቃና የደን ሚኒስትር

11. አቶ መኮንን ማንያዘዋል እንደሻው – የብሄራዊ ፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop