(ዘ-ሐበሻ) ጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም ደሳለኝ አቶ በረከት ስም ዖንን እና የአዲስ አበባ ከንቲባ የነበሩትን አቶ ኩማ ደመቀሳን የጠቅላይ ሚንስትሩ የፖሊሲ ጥናት እና ምርምር አማካሪ ሚንስትር አድርገው ከሾሙ በኋላ በተጨማሪም ለ11 ተጨማሪ ባለስልጣናትን ሹመት ማስጸደቃቸው ከአዲስ አበባ የመጣው መረጃ አመለከተ። እንደመረጃው ከሆነ ም/ል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን በጣምራ ይዘውት የነበረውን የትምህርት ሚ/ርነት ሥልጣን ተገፈው “የአማራው ሕዝብ ጠላት” በሚል ቅጽል ስም የወጣላቸው አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ስልጣኑን እንዲይዙት ተደርጓል።
በቅርቡ ከስልጣን በተባረሩት የፍትህ ሚ/ሩ ብርሃን ሃይሉ ምትክም አቶ ጌታቸው አምባዬ መሾማቸው ተገልጿል። አዳዲሶቹን ሹመኞች ዝርዝር እነሆ፦
1. አቶ ደመቀ መኮንን – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር
2. አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ወላሳ – የትምህርት ሚኒስትር
3. አቶ ሬድዋን ሁሴን ራህመቶ- የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሚኒስትር
4. አቶ አህመድ አብተው አስፋው – የኢንዱስትሪ ሚኒስትር
5. አቶ ወርቅነህ ገበየሁ ነገዎ – የትራንስፖርት ሚኒስትር
6. ወይዘሮ ሮማን ገብረስላሴ መሸሻ – በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር
7. ወይዘሮ ደሚቱ ሃንቢሳ ቦንሳ – የሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ሚኒስትር
8. አቶ ጌታቸው አምባዬ በለው – የፍትህ ሚኒስትር
9. አቶ በከር ሻሌ ዱሌ – የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር
10. አቶ በለጠ ታፈረ ደስታ – የአካባቢ ጥበቃና የደን ሚኒስትር
11. አቶ መኮንን ማንያዘዋል እንደሻው – የብሄራዊ ፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር