Hiber Radio: ዩ.ኤን.ኤች. ሲ.አር ግብጻውያን በአገራቸው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን እንዲጠብቁ ጠየቀ

June 17, 2013

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ
Hiber Radio: ዩ.ኤን.ኤች. ሲ.አር ግብጻውያን በአገራቸው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን እንዲጠብቁ ጠየቀ 1
እንኳን ለአባቶች ቀን አደረሳችሁ

የህብር ሬዲዮ ዕሁድ ሰኔ 9 ቀን 2005 ፕሮግራም

<< አባይን ግብጽም ሆነ በስልጣን ላይ ያለው አገዛዝ ለፖለቲካ ጥቅም ሊያውሉት ይችላሉ። መንግስት በግልጽ ብሄራዊ እርቅ ብሄራዊ መግባባት እንዲኖር ማድረግ አለበት። የሰብዓዊ መብት ጉዳይ መረሳት የለበትም።ይሄ ባለበት ግን ግብፅ እንደፎከረችው ወረራ ከፈጸመች ሁሉም ተቃዋሚ ጦርነቱን መደገፍ አለበት…>> ዶ/ር ሙሉጌታ ካሳሁን የቀድሞው የኢትዮ_ራዕይ ማህበር ሊቀመንበር

<< ዛሬም በኢትዮጵያውያን ላይ ብዙ ችግር ይደርሳል። የተለወጠ ነገር የለም። ችግሮች አሉ።ከዩ.ኤን.ኤች.ሲ.አር ጋር ተወያይተናል። በኣባላት ጥያቄ ሰልፉን ጠርተናል ስጋቶች ግን አሉብን…>>

አቶ አስናቀ ሞላ በግብጽ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ማህበር የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ ዛሬ ስለጠሩት ሰልፍ ተጠይቀው ከሰጡት ማብራሪያ(ሙሉውን ያዳምጡ)

የአባይ ግድብ ለፖለቲካ? እውን ግብጽ እንደምትፈራው የችግር ምንጭ፡ የህወሃት ኩባንያዎች ኪስ ማዳለቢያ? ለብሔራዊ ጥቅም? ዓለም አቀፍ እይታዎችስ ምን ይመስላሉ? ( ወቅታዊ ትንታኔ አለን)

<< ፌዴሬሽኑ የግለሰቦች ሳይሆን የሕዝብ ነው።ፌዴሬሽናችን ሁሉንም በእኩል አይቶ አስታራቂ ሀሳብ አቅርቧል።የቬጋሱ ክለብ የቦርድ አባል አልተቀበሉትም።በተጫዋቾቹ በኩል ያሉት ያቀረብነውን መፍትሔ ተቀብለዋል። ይህን መሰረት አድርገን ቦርዱ ለጉዳዩ መፍትሄ ለመስጠት ወደ ድምጽ ሄዷል።ለመጨረሻ ውሳኔ የቀረን ሁለት ድምጽ ብቻ ነው።አስራ ሰባት ተሰጥቷል።ድምጽ መስጠቱ ቀጥሏል …>>

አቶ ጥላሁን ፍስሀ የሰሞን አሜሪካ የኢጥዮጵያውያን ፌዴሬሽን የቦርድ አባልና የሳንዲያጎ ቴዎድሮስ ክለብ ተወካይ

አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ዋሊያዎቹ ደቡብ አፍሪካን ካሸነፉ በሁዋላ ምን አሉ? (ዘገባውን ይዘናል)

ሌሎች ቃለ መጠይቆችም አሉን

ዜናዎቻችን
የኡጋንዳው ፕ/ት ሙሴቬኒ በአባይ ጉዳይ ግብጽን አስጠነቀቁ

ዩ.ኤን.ኤች. ሲ.አር ግብጻውያን በአገራቸው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን እንዲጠብቁ ጠየቀ

ኢትዮጵያውያኑ የሚደርስባቸውን የመብት ረገጣ በመቃወም ሰልፍ ወጥተዋል

በአዲስ አበባ ታሪካዊ ህንጻ ይፍረስ አይፍረስ ጥያቄ ውዝግን አስነሳ

በአሪዞና ኢትዮጵያውያን ጉባዔ አደረጉ

የክርስትናና የእስልምና የሀይማኖት አባቶች ስርዓቱን በቃ ማለት እንደሚያስፈልግ ገለጹ

በቬጋስ በስራ ማቆም አድማ ላይ የሚገኙ የፍሪያስ አሽከርካሪዎች ገቨርነር ሳንዶቫልን ምላሽ እንዲሰጡ በሰልፍ ጠየቁ

ሌሎችም ዜናዎች አሉን

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop