May 12, 2015
4 mins read

ተስፋ ሳይኖር ተስፋ መቁረጥ: የተስፋ ቢሶች ተስፋ ( ሄኖክ የሺጥላ )

Henok Yeshitila
Henok Yeshitila
Henok Yeshitila
ተስፋ ሳይኖር ተስፋ መቁረጥ: የተስፋ ቢሶች ተስፋ ( ሄኖክ የሺጥላ ) 1

ካንዳንድ ወዳጆቼ ጋ ሳወራ ፣ ” ግን ሄኖክ በትግሉ ተስፋ ቆርጠሃል ማለት ነው ? ” የሚል ጥያቄ ይጠይቁኛል ። እኔ ሲጀመር መቼ ተስፋ አድርጌ አውቃለሁ ? “ያለውን ትግል ከማዳፈን አብሮ ሆኖ ስህተቱን ማረም ነው የሚሻለው” የሚል መልካም አስተያየቶችም ደርስውኛል ። እርግጥ ያ ቢሆን ማን ይጠላል ? ሳይማር ያስተማሩን ገበሬ አባቶቻችን ፣ ሳይሰሙ ስሙን የሚሉ ልጆች ወለዱ ። ሳይታገሉ ፣ የሚያታግሉ ወንዶች ልጆች አባቶች ሆኑ ። የነሱ ስቃይ በምን እና በማን ይገለጽ ? አፈር ፈጭተው ሰው ያደረጉን እኛ የነሱ ልጆች ፣ ወሬ ፈጭተን ፣ ሰው ልናደርጋቸው አሰብን ። እኛ ያባቶቻችን ልጆች ነን ? ።

ሄኖክ ተስፋ አትቁረጥ ይሉኛል ። ተስፋ የሚያስቆርጥ ምን አዲስ ነገር ? ተስፋ የሚሰጥስ ነገር አለን ? እኛ ስለ ተስፋ እናውቃለን ? ተስፋ ያለው ሕዝብ እኮ ቢያንስ እምነት አለው ? ቢያንስ ተስፋ ያለው ሕዝብ ጽናት አለው ። ተስፋ ለመቁረጥም ሆነ ተስፈኛ ለመሆን ምን አዲስ ነገር አለና ።
ስለ እውነት እኛ ኢትዮጵያኖች ተስፋን አልረሳነውምን ? እስራዔላውያኖች ከግብጽ ወደ ከነዓን ሲጏዙ ተስፋ የሆናቸው መጏዛቸው እኮ አይደለም ፣ ተስፋ የሆናቸው ሀገር እንዳላቸው ማወቃቸው ነው ። ስንቶቻችን ነን ሀገር እንዳለን ትዝ የሚለን ? የምናውቀው ? አንድ ቀን እንገባለን ብለን የምናስበው ? እኛ ተስፋን ረስተነዋል ፣ ምክንያቱም ተስፋ እኛን ስለረሳን ።

አንዳንዴ መከራችን ሲደራረብ ፣ ሃዘናችን ሲበረታ ፣ ፊታችንን ወደ እግዚአብሔር እናዞራለን ፣ ጥሩ ነገር ነበር ግን እሱን እንኳ ለይስሙላ ( ለፋሽን ) የምናደርግ ሰዎች ነን ። በእውነት እምነት እኛን ያውቀናል ? እኛ ክርስቲያኖ ነን እንዴ ? እስላሞች ነን እንዴ ? ነን የምትሉ የክርስቲያን ወይም የሙስሊም ባህርይ ምን መምሰል እንዳለበት መጽሐፍ ቅዱሱንና ቁርዓኑን አገላብጡ ። ከዚህ አንጻር እኛን እግዜሩ አያወቅንም ማለት እችላለሁ ።

ድረስ አምላክ ፣ አረ የት ነህ
ብንማጸን ብንለምንም
አትሳሳቱ ሰዎች እግዜር እኛን አያውቀንም !
የገዳማት ሀገር እኛ
የግዮን ወንዝ መገኛ
የማህሌት መዝሙር ምንጭ
የበገና አውታሮች እጅ
ብለን እልፍ ብናወራ
ወሬያችን ምንም ላይሰራ
እግዜር እኛን አያውቀንም

የሚመስለኝ ይሄ ነው ። እና በትግሉ ተስፋ ቆረጥክ ለምትሉ ፣ ተስፋ አርጋችሁ ነበር እንዴ ? ሳያዩ የሚያምኑ ብጹአን ናቸው ፣ ያዩትን ማገናዘብ እና ራሳቸውን መጠየቅ ያልቻሉ ግን ፣ በአሁኑ አጠራር ( ወይም አገላለጽ ) ተስፈኞች ናቸው ማለት ነው ። የ ካልሃሪ በርሃ ላይ ዝናብ ይዘንባል ብሎ ተስፋ ማድረግ ስህተት አይደልም ፣ ግን እንዲህ አይነት ተስፋ ጥቅሙ ምንድን ነው ?

Source: Henok Yeshitela fb

2 Comments

  1. አይ ሄኖክ ወንድሜን!

    ሳይሞቅ የፈላ ሰው መጨረሻው ይሄ ነው:: ያላቅምህ ገምጠህ ሳያንቅህ ትግሉን ተፋሃው:: ያው ብዙ ምክንያት ደረደርክ:: ለመሸወድ ማለት ነው:: ከመራራው ትግል የማምለጫ ቀዳዳህን ለመቆፈር የባጡን የቆጡን ቀባጠርክ:: በሰበብ የገዛ ግጥሞችህን ከድተህ ከመራራው ትግል ሸሸህ:: ጀግና መስለህ ፍርሃትህን ደብቀህ ከረምክ::

    ጥሩ ግጥም ገጥሞ በአደባባይ ማዥጎድጎድና መሬት ወርዶ የመረረ ትግል አሃሂዶ መስዋእትነትን መክፈል ልዩነቱን በአጭር ጊዜ ውስጥ አየህው:: ስለ አንዳርጋቸው ጽጌ ግጥም ማውረድና ከእሱ ጋር የተነሳሃውን ፎቶግራፍ በፌስ ቡክ በመለጠፍና አንዳርጋቸውን እራሱን መሆን ልዩነቱን በአጭር ጊዜ ውስጥ እንድታይ ተገደድክ::

    አምላክ ያለው ትዝ ይልሃል? ስለ እኔ ማወቅ ብቻ ሳይሆን እኔን እወቁ (ሁኑ) ነው ያለው:: ስለ አንዳርጋቸው ታውቃለህ :: የማያልቅም ግጥም ትደረድራለህ:: ግን አንዳርጋቸውን እንኳን ለመሆን ትንሽም መምሰል አልቻልክም:: እንዲሁ ባዶ ፉከራ ብቻ ነበር ያ ሁሉ መውተርተር::

    የገጠምካቸው ግጥሞች ለገዛ ራስህ ባዳ ሆነዋል:: እርግጠኛ ነኝ ከአእምሮህ እንጂ ከልብህ አልፈለቁም:: ከአንገት በላይ ነበሩ ማለት ነው:: ከአንተ ይልቅ እኛ በግጥምህ ተጽናንንተንና ጸንተን እንገኛለን:: ግጥሞችህ ለአንተ ባዳ ቢሆኑም እኛን ግን ከተስፋ መቁረጥና ከሃዘን አላቅቀውናል:: አንተና ልጆቿን የካደች ርጉም እናት አንድ ናችሁ:: አንተ ተስፋ ቆርጠህ ወልደህ የካድካቸውን ግጥሞች እኛ ተረክበንና በልባችን አኑረን በዚህ በጨለማ ሰዓት ብርሃን እየሆኑን ነው::

    ምንም አያስደንቀንም:: መከዳት የመጀመሪያችን አይደለም:: በየአይነቱ አይተናል:: እንዳንተ ያዙኝ ልቀቁኝ እያሉ ከርመው ግን በነጋታው የሌለ ምክንያት ፈጥረው ከሚሸሹን ጀምሮ ሰው በላውን ወያኔ የተቀላቀሉ ጥቂት አይደሉም::

    ሄኖክ መሸሽ መብትህ ነው:: ግን ያልሆነ ምክንያት እየሰጠህ ፍርሃትህንና ወኔ ቢስነትህን አትደብቅ:: በተለይ ለፍርሃትህ መደበቂያ የሌሎችን ስብእናና የረጅም የትግል ታሪክ አታንቋሽ:: እንዳንተ ዓይነት ፈሪዎች በበዙብት በአሁኑ ሰዓት ሁሉን ተቋቁመው ትግሉን ለብቻቸው ተሸክመው የሚታገሉትን ቆራጥ የኢትዮጵያ ልጆች ለሽሽትህ እንድምክንያት አትጠቀምባቸው:: የሚችሉትን መስዋእትነት እየከፈሉ ትግሉን ሳያክርፉና ሳይነጫነጩ ተሸክመዋል::

Comments are closed.

Previous Story

Hiber Radio: ቻይና ለኢትዮጵያው አገዛዝ የጦር መሳሪያ ማስታጠቋን የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር ደርሼበታለሁ አለ *የመን ያሉ ኢትዮጵያውያን አገዛዙ ዜጎችን ከመመለስ ይልቅ የውስጥ የቪዛ ንግድ ላይ አተኩሯል ይላሉ * የኢትዮጵያና የደቡብ ሱዳን ባለስልጣናት ተቃዋሚዎቻቸውን ላለማስታጠቅ ለመስማማት ስብሰባ ተቀምጠው እንደነበር ተዘገበ * የኢትዮጵያ መንግስት በእስራኤል መብታቸው የተነካ ኢትዮጵያውያን ቤተ እስራኤሎች ጉዳይ ያሳስበኛል ማለቱን ብዙዎች አጣጣሉት * ኢትዮጵያዊው የታሪክ ተራኪ ኤድዋርዶ ባይሮኖ የሰጠው ቃለምምልስ እና ሌሎችም..

Next Story

ሳሞራ የኑስ በዋሽንግተን ዲሲ እጅግ ተዋረዱ * ተቃውሞው ቀጥሏል

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop