ኢ/ር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ከአገር እንዳይወጡ ታገዱ

ሐብታሙ አሰፋ

ኢ/ር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር በሰሜን አሜሪካ የተለያዩ ከተሞች ፓርቲው ሊያደርገው ላቀደው ስብሰባ ለመገኘትና ከኢትዮጵያውያን ጋር ለመወያየት ዛሬ አዲስ አበባ ኤርፖርት ላይ ከአገር እንዳይወጡ ተከልክለው መመለሳቸውን ከፓርቲው ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።

ኢ/ር ይልቃልን ከኤርፖርት የደህነቱ ሰራተኞች ፓስፖርታቸውን ተቀብለው የመለሷቸው ሲሆን ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ከአገር ሊወጡ ሲሉ ፓስፖርታቸውን ቀምተው ከውስጡ ገጽ ቀደው እንደመለሱላቸው ይታወሳል።

የሰማያዊ እና እውነተኛው የአንድነት ፓርቲ የሰሜን አሜሪካ ድጋፍ ሰጪ ማህበራት አማካይነት የተጠራው ስብሰባ በሰሜን አሜሪካ በተለያዩ ከተሞች ይካሄዳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሀን ከነዚህም በዲሲ፣በቺካጎ፣በቦስተን፣በሲያትል፣በቬጋስና በሌሎች የሚጠቀሱ ሲሆን ኢ/ር ይልቃል በነዚህ ስብሰባዎች ላይ ለመገኘት ነበር ከአገር ሊወጡ የነበረው።

ኢ/ር ይልቃል አስፈላጊውን የጉዞ ሰነድ ያሟሉ ቢሆንም የስርኣቱ የደህንነት ሰራተኞች ፓስፖርታቸውን ከተቀበሉ በሁዋላ ኢሚግሬሺን መጥተህ ጠይቅ በማለት መልሰዋቸዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሙሉ ቪዲዮው ተለቀቀ! የፕሪቶሪያው ሚስጥር በተደራዳሪው አንደበት!

2 Comments

  1. Source fugera.com =kkkk=the same funy jok was made for hailu shawel and ledetu ayalew who are friends of weyane =and now the new weyane creation semayawe party leader yelkal is jokking .why he need to come here in the first place while the election is in the next two months.does he finish complaining for his fake party inside Ethiopia .has he been in debreberhanen awasa or welega where the people who vote are there?what a jok .

  2. የሥሥሥሥሥሥሥሥሥሥሥሥሥሥሥ
    yesssssssssssssssssssssssssssss
    ይህ ተላላኪ ……..አስሮ መግረፍ ነበር
    የአዝማሪ ሊጅ

Comments are closed.

Share