ወያኔና ሽብርተኛነት – መስፍን ወልደ ማርያም

መስፍን ወልደ ማርያም
መጋቢት 1/2007

ወያኔነትና ሽብርተኛነት ትናንት ምን ዓይነት ግንኙነት ነበራቸው? ዛሬ ምን ዓይነት ግንኙነት አላቸው?

ወደዚያ ከመሄዳችን በፊት የአሸባሪነት የተግባር መገለጫው ምንድን ነው? ብለን እንጠይቅ፤ አሸባሪነት፡-
• ያለውን የሥልጣን ሥርዓት የማፍረስ ዓላማ ያለው ነው፤
• ዓላማውን ለማሳካት ጉልበቱን የሚያፈረጥመው ከሥርዓቱ ጠላቶች በሚያገኘው፡–
• የመሣሪያ እርዳታ፣
• የእውቀት ድጋፍና ገንዘብ
• ዓላማውን ለማሳካት
• ሰዎችን ገድላል
• ያስራል፤ ያሰቃያል
• ይዘርፋል፤ ይቀማል፤
• ዓላማውን ለማሳካት
o ሃይማኖቶችንና ባህልን ያዳክማል፤
o የጥንት ታሪክ ማስታወሳዎችንና የቆዩ መጻሕፍትን ያጠፋሉ፤
o የፖሊቲካ እምነትን ያግዳል፤
o የመሰብሰብ ነጻነትን ይከለክላል፤
o የመደራጀት ነጻነትን ይከለክላል፤
o ሀሳብን የመግለጽ ነጻነት ይከለክላል፤
o ጉልበትን ወደሥልጣን ይለውጣል፤

• አንድ ዓላማ፣ አንድ እምነት፣ አንድ ሀሳብ፣ አንድ ዘዴ. አንድ መንገድ በቀር ሌላው ሁሉ ይዘጋል፤ ይህንን ጥርነፋ የሚቃወም ሁሉ አሸባሪ ተብሎ ይታሰራል፤ የሲአይኤ ሰላይ ተብሎ ተሰቃይቶ ይሞታል፤
ከዚህ በላይ የተዘረዘረት በሙሉ የሽብርተኞች ወንጀሎች የሚባሉ ናቸው፤ እነዚህን እንደመመዘኛ አድርገን በአንድ በኩል ወያኔን፣ ከተፈጠረ ጀምሮ እስካሁን የሚያድርገውንና እያደረገ ያለውን በማስታወስ፣ በሌላ በኩል ከዚህ በታች የተዘረዘሩትና በሽብርተኛነት ተከስሰው በእስር ቤት የሚገኙት ሰዎችን

• እስክንድር ነጋ፣ ርእዮት ዓለሙ፣ ተመስገን ደሳለኝ
• የዞን ዘጠኝ በመባል የሚታወቁት ወጣቶች፣ (ማኅሌት ፋንታዬ፣ አጥናፍ ብርሃኔ፣ ኤዶም ካሣዬ፣ አቤል ዋበላ፣ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ፣ ተስፋ ዓለም ወልደየስ፣ ዘለዓለም )
• አንዱዓለም አራጌ፣ አብርሃ ደስታ፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ሀብታሙ
• ሌሎች ከግንቦት ሰባት ጋር ንክኪ አላችሁ ተብለው የታሰሩት
ስናመዛዝን በሽብርተኛነት መመዘኛዎቹ ከብደው የሚታዩት የትኞቹ ናቸው? የአሸባሪነት የተግባር መግለጫ ተብለው በተዘረዘሩት ውስጥ ባሉት ዓላማዎችና መንገዶች የሚንቀሳቀሱት የትኞቹ ናቸው? ወያኔ ነው ወይስ የታሰሩት ሰዎች? ሽብርተኛ ተብለው ከታሰሩት ውስጥ ባንክ ሲዘርፍ የተያዘ አለ? እኔ አስከማውቀው የለም፤ ከወያኔ ውስጥስ ባንክ የዘረፈ አለ? ራሱ መለስ ዜናዊ በኩራት ነግሮናል! በሌሎች ወንጀሎችም ቢሆን ያው ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ይድረስ ለፕሬዚደንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ

ተጨማሪ ማስረጃ የሚሆነው የዓለም የሰብአዊ መብቶች ድርጅቶች ሁሉ በወያኔ በሽብርተኛነት የታሰሩት ሁሉ እንዲፈቱ እየወተወቱ በአንጻሩ የወያኔን የሰብአዊ መብቶችን መጣስ እያወገዙ ነው፤ ስለዚህ ጋዜጠኞችንና የፖሊቲካ ሰዎችን እየለቀሙ በሽብርተኛነት እየወነጀሉ በየእስር ቤቱ መወርወሩ አላዋጣም፤ አዝማሚያው እንደሚያሳየው የወያኔ ጸረ-ሽብርተኛ መምሰል ለሲአይኤም የሚሸጥ ሊሆን የሚችል አይመስልም፡፡

በዚያ ላይ ሽብርተኞች በኢራቅና በአፍጋኒስታን አድርገው የመን ገብተዋል፤ ከየመን ሶማልያ ቅርብ ነው፤ ኬንያን እየፈተሹት ነው፤ የሱዳን ትርምስ ሽብርተኞችን እንደሚጋብዝ ጥርጥር የለም፤ የናይጂርያው ወደሱዳን ሲጠጋ መፈናፈኛ ይጠፋል፤ በሽብርተኛነት የተከሰሰችው ኤርትራ ለመሸሸጊያ ትሆን ይሆን?

ጤናማ ሰው ሆኖ ሽብርተኛነትን የሚደግፍ ያለ አይመስለኝም፤ ዛሬ በኢራቅ የሚደረገውን በየቀኑ ስንመለከት ወደቤታችን አልተጠጋም ብለን ልንዝናና የምንችልበት ሁኔታ ላይ አይደለንም፤ በዋልድባና በበዙ ሌሎች ቦታዎች የኢትዮጵያ ቅርሶች አደጋ ላይ መሆናቸው ይሰማናል፤ ግን በአቅመ-ቢስነት በዝምታ እንመለከታለን፤ ይህንን የአዳፍኔ የፖሊቲካ አቅጣጫ ለመለወጥ የሀሰብ መለዋወጫ መድረክ የሚፈጥሩትን ወጣቶች ሁሉ በእስር ቤቶች እያጎሩ ነው፤ አዲስ የፖሊቲካ መድረክ እንፍጠር ብለው በሰላማዊ መንገድ የፖሊቲካ ትግል የጀመሩትን ሁሉ እያሰሩ ነው፤ በትግራይ ውስጥ አረና በትግራይ ያለውን የፖሊቲካ መሻገት ለማጥራት እንዳይሞክር እየተደረገ ነው፤ ከዚህ በፊት ገብሩ ዓሥራት የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኅብረትን በክፉ የጭካኔ ዘዴ እንዳዳከመ አሁንም አረናን ለማዳከም እየተሞከረ ነው፡፡
መቼ ነው ወያኔዎችና ሎሌዎቻቸው ነገን የማየት ዓይኖች የሚያበቅሉት?

10 Comments

  1. Professor mesfin weldemariam, birq ena wid ye ethiopia mihur,thank you,since i have never seen you.i just admir admire admire you for your wisdom, i really heard you and professor asrat weldeyes have deep love for ethiopians at all,the rest are your student.i want to read more of you topic of tplf.the one you wrote on megabit 1,2007.ec,thank you professor.

  2. ዪሔ ሸማግሌ መቼ ነው በ አንድ አቁዓም የሚቆየው? መልክቱ ሁል ግዜ ዝብርቅርቅ ያለ ነው. you and Adis Zemzen news paper are the same, the only thing u could do is role with the new coming governments. you are a well known feudal. I am so happy I have never been your student!!!

  3. ፕሮፍ መስፊን

    እርሦስ መችሀ ነው ቲግረ ተበደለ እያሉ መችሁን የመያቆሙት ?????

  4. የተከበሩ ፕሮፌሰር መስፍን ሆይ ! አጠር አድርገው በትክክል በመቱት ሚስማር እንደወትሮው ሁሉ ጠንካራ መልክት ማስተላለፎን አደነቅኩ , ሆኖም ለዛች ሀገር ፍትህ ,ሰባዊ ክብርና ህገመንግስታዊ መብት መከበር ከ 97ቱ ፍጹም ጸጥታ በሁዋላ የፊት መስመር ላይ ሆነው የአሸባሪነትን ካባ ተጭነው የስቃይ ትንሽ የለዉም እንጂ ከማንም በላይ የስቃይ መሞከርያ ሆነው በሽብርተኛው ኢህአዴግ ግፍ እየተሰራባቸዉና ከማንኛዉም የፖለቲካም ሆነ የሚድያ ሰው ይልቅ በሃገራችን ታሪክ አቻ ያልተገኘለት የህዝብ ዉክልናን ያገኙትን የሙስሊሙን መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ቅንጣት ወይንም ኢምንት ሆነው አልታይ አለዎት ? እነዚህን የኢትዮጵያ እንቁ አንዳቸዉንም ለምሳሌነት ሊጠቅሱ አልሞከሩም ? ወይንም በደምሳሳው አላመላከቱም? ያስቀመጡት መመዘኛ ስለማይመለከታቸው ይሆን? (አይመስለኝም) ስም መጥራት ባይጀምሩ አንድ ነገር ነበር !
    በመሰረቱ እርሶ የጠቀሷቸው ዉድና የተከበሩ የኢትዮጵያ ጀግኖች ልጆችም ሆኑ በታላቅዋ እስር ቤት በኢትዮጵያ ታጉረው የሚማቅቁ ሁሉ በፍትህ እጦት እንጂ የሰሩት ወንጀል ኖሮ አይደለም ! ግን የተከበሩ ፕ/ር ሆይ ለመሆኑ ወገን ማለት እንዴት ነው የሚመዘነው ?

  5. ፕሮፌሰር እርሶ እንኳን ደህና ሰው ነበሩ; ተራማጅ:: ዛሬ ምን ነክቶዎት ነው በአሸባሪው መንግስት በአሸባሪነት የተከሰሱ የንጽሃን ኢትዮጵያውያንን ሥም አንድ በአንድ ሲጠቅሱ የሰላማዊነት ተምሳሌ የሆኑትን የህዝበ ሙስሊሙን ተወካዮች ያለ ምንም ርህራሄ ተረማመዱባቸው:: የአሸባሪነት መገለጫዎች ብለው ከዘረዘሯቸው መካከል የትኛው ይሆን በእርሶ መዝገብ ከአሸባሪነት ተርታ እንዲሰለፉ ያደረጋቸው:: እንዲያው የኃይማኖት ነገር ሆኖብዎት ካልሆነ በስተቀር የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላቱ እርሶ ከጠቀሷቸው ውድ የሃገራችን ልጆች በበለጠ ሰላማዊነትን, መቻቻልንና የሀገ መንግስትን መከበር የሰበኩ ለዚህም መልካም አርአያነታቸው በአሸባሪው መንግስት ለእስርና እንግልት የተዳረጉ ናቸው:: እኔ መቸም እንዴት ህሊናዎ አስችሎት እነዚህ ብርቅዩ የሃገራችን ፈርጦች በቸልታ እንዳለፏቸው ሊገባኝ አልቻለም, ለምን ቢባል ፕሮፌሰር መስፍን ተራማጅ ሰው ናቸው ብዬ አምን ስለነበረ ነው:: ጉድና ጅራት … ይባል የለ:: ይብላኝ እንጂ ለእርሶ እነርሱ እንደሆነ ለንጽህናቸው በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መስካሪዎች አሏቸውና የሚያስጨንቅ ነገር የለበትም; ይልቅስ የሚያስጨንቀው የሃገራቸን ምሁራዊ ካፒታል ከቀን ወደ ቀን እያሽቆለቆለ መሄዱ ነው:: አረ አንድ በለን አቦ ፈጣሪያችን መንገዳችን ከድጡ ወደ ማጡ ብቻ ሆነ እኮ!

  6. Prof. Mesfin Woldemariam

    ማስተካከያ

    በቅርቡ በፌስቡክ ላይ የለጠፍሁት ጽሑፍ አንድ ሰሕተትና አንድ ጉድለት እንዳለበት ሰዎች ጠቁመውኛል፤ መጀመሪያ ስሕተቱ፤- ጥያቄዎችን በመጠየቃቸው የታሰሩትን እስላሞች በግልጽ ሳላነሣ ቀርቻለሁ፤ ብዙ ሰዎችንም አላነሣሁም፤ አቡበከርንም አላነሣሁም፤ ስለነአቡበከር ብዙ ጊዜ ጽፌአለሁ፤ ለሃይማኖት ነጻነት ብሎ ለቆመለት ዓላማ እኔም አብሬው እቆማለሁ፤ የጻፍሁትን በአጠቃላይና በትክክል ለተረዳው እነአቡበከር በስም አይጠቀሱ እንጂ የቆሙለት ቁም-ነገር የጽሑፉ ዋና ዓላማ ነበር፡፡ በመሀከላችን ጥርጣሬ አይግባ!
    ጉድለቱ ዘለዓለም ክብረትን ከጓደኞቹ ነጥዬ ማስቀረቴ ነው፡፡
    እግዚአብሔር ልባቸውን ይክፈተውና የእስር ቤቱንም በር እንዲከፍቱ ይርዳቸው፤ በዚያውም ለወህኒ ቤት ጠባቂዎቹ፣ ለፖሊሶች፣ ለዓቃብያነ ሕግና ለዳኞች እግዚአብሔር ነገን ያሳያቸው!

  7. Thank you prof.Mesfn … ለቀረበቦት ቅሬታ ፈጣን ማስተካያ መጻፎ በጣም የሚወደስ ነው :: ያውም ርስዎ ተዘናግተው ነው ፥በሀገራችን አሁን ህዝበ ሙስሊሙ ላይ እየደረሰ ላለው ኢህአዴጋዊ ግፍ ዱላ አቀባይ የሆነው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት የሰራው ሳያንሰው ይቅርታ ጠይቁኝ ማለቱን ትቶ ከርሶ መማር ይችል ይሆን ?

  8. የፕሮፌሰር እነአቡበከርን መዘንጋታቸው አስደንግጦኝ ነበር። ነገር ግን ከበለጠ ማብራርያ ጋር ሲመጡ የበለጠ ታላቅነታቸውን አሳየኝ። ውነትም ተራማጅ ነዎት።

  9. What happened to my comment ? i have sent it into this box yesterday morning ? and now it has gone anyway ,I’m a fun of Professor Mesfin , As i said before once again Thank You for this article .

Comments are closed.

Share