October 21, 2014
1 min read

ደቡብ ጎንደር ደብረታቦር ለሰዓታት በጥይት እሩምታ ስትታመስ ቆየች

(ዘ-ሐበሻ) በደቡብ ጎንደር ደብረታቦር ከተማ ለሰዓታት በጥይት ስትታመስ መቆየቷን ምንጮች ለዘ-ሐበሻ አስታወቁ::

ከግብር ጋር በተያያዘ ተነሳ በተባለው በዚሁ የጥይት ተኩስ ሶስት አርሶ አደሮች መቁሰላቸው የተዘገበ ሲሆን የሞተ ሰው ግን እንደሌለ የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታውቀዋል::

በሌላ በኩል ምኒልክ ሳልሳዊ በደቡብ ጎንደር ደብረታቦር ከተማ ከግብር ጋር በተያያዘ ክፈል ሌላው ቀደም ሲል ከፍያለሁ በሚል በተነሳው ጸብ ፓሊሰ በአሰቃቂ ሁኔታ አርሶአደሩን በመደብደቡ ገበያ ላይ የነበረው ሰው ህግ ፊት አቅርበህ እንዲቀጣ ታደርጋለህ እንጂ አትገድለውም በማለቱ የተነሳ ደብረታቦር ከተማ ለሰዓታት መናወጧንም ዘግቧል::

በዛሬው ዕለት በተነሳው በዚሁ ግጭት የአንድ አርሶ አደር እጅ መቆረጡን የዘገበው ምኒልክ ሌሎች ሶስት አርሶአደሮችም በጽኑ መቁሰላቸውን ዘገቧል:: ተኩስ ያነሳው ፖሊስም ወደ ደበረታቦር ሆስፒታል የተወሰደ መሆኑን የሚናገሩት የአይን እማኞች ሕይወቱ በአስጊ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ ጠቁመዋል::

5 Comments

  1. Betam yigermal beka beyfa abedu malet new? A collection of rock who do not document for further investigation.

  2. ለምን ፖልሱን አልገደላችሁትም? ነው የኔ ጥያቄ ለሌላው ፖሊስ ትምህርት ይሆን ነበር

Comments are closed.

Previous Story

Hiber Radio: ኢትዮጵያ የኢቦላ ተጠርጣሪዎችን ናሙና ወደ ኬኒያ እንደምትልክ አንድ የአገሪቱ ባለስልጣን ገለጹ; * ካራቱሪ በኪሳራ ሳቢያ መሬቱን አሳልፎ እየሸጠ መሆኑ ተጋለጠ

Next Story

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ችሎት ትናንት እና ዛሬ ቀጥሎ ዋለ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop