May 8, 2013
5 mins read

ሰማያዊ ፓርቲ በአፍሪካ ሕብረት 50ኛ አመት ክብረ በአል ዕለት በአዲስ አበባ የተቃውሞ ሰልፍ ጠራ

*ሰልፈኞች ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ
በዘሪሁን ሙሉጌታ
(ሰንደቅ ጋዜጣ የዛሬ ዕትም)

ከመጪው ግንቦት 17 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ የሚከበረውን የአፍሪካ ሕብረት 50ኛ አመት የወርቅ እዮቤልዩ በአል ላይ ታላቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ተደረገ።

ሰልፉን ያዘጋጀውና የሚመራው በቅርቡ የተመሰረተው ሰማያዊ ፓርቲ ሲሆን የሰልፉም አላማ ፓርቲው ከዚህ በፊት አስቸኳይ መፍትሄ እንዲፈለግላቸው ለመንግስት ጥሪ አቅርቦ መልስ ያላገኙ አራት ርዕሰ ጉዳዮች ትኩረት እንዲያገኙ ለማድረግ መሆኑን ተገልጿል።

የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ስለሺ ፈይሳ፣ የፓርቲው የሕግ ጉዳይ ኃላፊ ወጣት ይድነቃቸው ከበደ እና የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አሮን ሰይፉ በጋራ በፓርቲው ጽ/ቤት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳመለከቱት የተቃውሞ ሰልፉ የሚደረገው የተለያዩ ሐገራት፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና መሪዎች በሚገኙበት ድምፃችን ለማሰማት ነው ብለዋል።

በዚሁ መሠረት ከግንቦት 15 እስከ 17 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ ጥቁር ልብስ በመልበስና ግንቦት 17 ቀን 2005 ደግሞ በአፍሪካ ህብረት ጽሕፈት ቤት ፊት ለፊት ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ አራቱን ጥያቄዎች እንዲመለሱ ፓርቲው ግፊት እንደሚያደርግ አመራሮቹ በጋራ በሰጡት መግለጫ ላይ አስታውቀዋል።

የፓርቲው አመራሮች መመለስ ይገባቸዋል ያሉዋቸው አራቱ ጥያቄዎች መካከል፣ ለፍትህና ዲሞክራሲያዊ ስርዓት መስፈን የሚታገሉ ጋዜጠኞችን፣ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችንና አባላትን በአሸባሪነት ስም ማሰርና ማሰቃየትን አጥብቀን የምንቃወም መሆኑንና እስረኞችንም እንዲፈቱ የጠየቅን ቢሆንም እስካሁን ምንም መልስ ያልተገኘ በመሆኑ፤ የዜጐችን ሰብዓዊና ሕገ መንግስታዊ መብቶችን በመጣስ ለዘመናት ከኖሩበት ቦታ ኢሰብዓዊ በሆነ ድርጊት በታጠቁ ኃይሎች እንዲፈናቀሉ ማድረግ የዘር ማጥፋት ወንጀል በመሆኑ የድርጊቱ ፈፃሚዎች ለፍርድ እንዲቀርቡና የተፈናቀሉት ዜጎችም በአስቸኳይ ወደየመኖሪያቸው ተመልሰው እንዲቋቋሙ በመንግስትም ሆነ በግብረ ሰናይ ድርጅቶች አስፈላጊው ድጋፍ እንዲደረግላቸው የጠየቅን ቢሆንም አሁንም ገና የሚፈናቀሉ ዜጎችን ስም ዝርዝር በየማስታወቂያ ሰሌዳዎች ላይ ተለጥፎ እያየን በመሆኑ፤ መንግስት በኃይማኖታችን ጣልቃ አይግባ፣ የእምነት ስርዓታችንና የሃይማኖት መሪዎቻችንን እምነታችን በሚፈቅደው ብቻ እናከናውን ያሉ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮችን በአሸባሪነት ወንጀል በመክሰስ በእስር እንዲማቅቁና ሰብዓዊ መብታቸው እንዲጣስ መደረጉ እንዲቆምና ያነሷቸውም የእምነት ነፃነት ጥያቄዎቻቸው እንዲከበር የጠየቅን ቢሆንም እስካሁን የተገኘ መልስ ባለመኖሩ፤ መንግስት የኑሮ ውድነትን፣ የሥራ አጥነትንና በሙስና የተዘፈቁ የመንግስት ሌቦችን የሚቆጣጠርባቸውን መንገዶችና ፖሊሲዎች በማውጣት ሐገራችንን ከቀውስና ዜጎችንም ከሰቆቃ እንዲያወጣ በተደጋጋሚ ያቀረብናቸው ጥያቄዎች ሰሚ አጥተው በመቆየታቸው እነዚህ ችግሮች እንዲፈቱ አሁንም አጥብቀን የምንጠይቅ መሆኑ ለማስገንዘብ ነው ብለዋል።

ከዚህ ቀደም ፓርቲው በጣሊያን ሀገር ለፋሺስት ግራዚያኒ መናፈሻና ሐውልት መቆሙን ተከትሎ በፓርቲውና ከሌሎች የሲቪክ ማህበራት ጋር ሰላማዊ ሰልፍ በመጥራቱ የተወሰኑ የፓርቲው አመራሮችና የሰልፉ አስተባባሪዎች ታስረው መለቀቃቸው አይዘነጋም።n

3 Comments

  1. The STRUGGLE OF THE ETHIOPIAN PEOPLE FOR FREEDOM, DEMOCRACY AND JUSTICE IS DUE TO ENTER A NEW PHASE following the announcement of Blue Party to hold a public demonstration at the AU meeting.

    This is a significant move for the new Blue Party. This is the moment the Ethiopian people have been waiting for. The people are looking for Leaders, to lead them. Unfortunately, the ‘Loyal’ opposition have been unable to do this for the last 20 years.

    In the face of well publicised, documented evidence showing human rights abuse, jailing and torturing, ethnic cleansing, genocide , eviction of civilians , etc …..any party calling itself an opposition cannot remain silent.

    It is now time to act. Join the Blue Party and come out in protest against injustice, abuse, violence and murder on civilians, torturing and jailing of journalists, political party members and supporters, relegious leaders, youth leaders, trade unionists etc….

  2. Despite all crimes committed by woyane , most people scare to steam off their anger .instead want divine to intervene on behalf of them and thus stretch their hands to the invincible one. How long we keep on praying ? and asking God to destroy the woyane knowing that it is our primary obligation ? why we give hard time to god instead of doing our home work our selves?. I believe we have no tangible reason/s other than making God as our greatest hide out for our profound fear of woyane’s. i doubt the call made by SEMYAWE Party for great turn out may fall in ears stuffed with FEAR . Any ways it is a good and bold decision in the right direction . Let the Semyawe party take the lead and the suffering .Because never been heard anything similar call or support from others who supposedly should take the front line in such show down . keep it up semayawi!!!!!!

  3. Remember that Semayawi party is a splinter group of UDJ and organized by extremist Amharas. The TPLF has given them the permission to form a party because they will counter act the UDJ. As UDJ (Andinet) is now gravitating towards the right feudal reminants there uis no distinction between the two. After 21 years of TPLF’s divide and rule the Amhara elites have not yet learned that their struggle alone cannot yield anything meaningful. If their intention is to allow the TPLF to enslave them indefinitely, power to them. The frest of the country has to be smart and bold enough to have a lasting working relationship and action-oriented activity that will force the TPLF to think about their own existence.

Comments are closed.

habtamu
Previous Story

Hiber Radio: “ኢትዮጵያውያንን በአውሮፕላን መርዝ እየረጨ ያስጨረሰው ግራዚያኒ ሐውልት ሲቆምለት እሱ ያስገደላቸው አቡነ ጴጥሮስ ሐውልታቸው መፍረሱ ያሳዝናል” ኪዳኔ ዓለማየሁ

Next Story

ጥንታዊው ባንኮ ዲሮማ ሕንፃ የመደርመስ አደጋ ተጋርጦበታል

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop