ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር በርዕዮት ጉዳይ ያልተጠየቀውን መለሰ

ከዳዊት ሰለሞን

ዳዊት ሰለሞን

ባሳለፍነው እሁድ ለንባብ የበቃው የአማርኛው ሪፖርተር ጋዜጣ በደብዳቤዎች አምዱ ከማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ተላከ ያለውን ደብዳቤ አስነብቧል፡፡ከተቋሙ ተላከ የተባለው ደብዳቤ ማህተም፣የአስተዳደሩን ፊርማና ወጪ የተደረገበትን ቀን ያላካተተ ቢሆንም ጋዜጣው ሪፖርተር ታማኝ በመሆኑ ከማረሚያ ቤቱ የተላከ ነው ለማለት በግሌ ድምዳሜ ላይ ደርሻለሁ፡፡በሪፖርተር ታማኝ ምንጭነት ዙሪያ ጥያቄ ያላችሁ ሰዎች ደብዳቤውን ሰንደቅና አዲስ ዘመን ገጽ 3 ላይ የሚጽፉ ያዘጋጁት ይሆናል በማለት መጠርጠር መብታችሁ ይመስለኛል፡፡ወደ ደብዳቤው ዝርዝር ስንገባ ያልታረሙ ሰዎች እነርዕዮትን እናርማለን ብለው በአስተዳደርነት መቀመጣቸውን ወለል ብለውላችሁ ትመለከታላችሁ ፡፡ታገሱኝማ

አስተዳደሩ ደብዳቤውን የላከው አለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት(ሲፒጄ)በማረሚያ ቤቱ የምትገኘውን ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙን በማስመልከት መግለጫ ማውጣቱን ተከትሎ የድርጅቱን ክስ ለማስተባበል ነው፡፡ሲፒጄ በመግለጫው ርዕዮት በርቀት ሁለተኛ ድግሪዋን ለማግኘት ከተመዘገበች በኋላ በማረሚያ ቤቱ እንዳትማር መከልከሏንና  ደረጃውን የጠበቀ የህክምና ክትትል እንደማይደረግላት ማተቱ አይዘነጋም፡፡ለወቀሳው ምላሹን በሪፖርተር የሰጠው ማረሚያ ቤቱ

1)‹‹ርዕዮት ለብቻዋ በዝግ ቤት ታስራለች የተባለው ውሸት ነው፡፡እንዲህ በማለት መናገርም አብረዋት የታሰሩና በአንድ ክፍል ውስጥ የሚገኙ እስረኞችን ሰው አይደሉም በማለት እንደመናገር ይቆጠራል፡፡››ብሏል፡፡አስቂኙ ነገር ሲፒጄ በመግለጫው ርዕዮት ለብቻዋ በዝግ ቤት ታስራለች አለማለቱ ነው፡ከዚህ ይልቅ ሲፒጄ ያለው ‹‹ርዕዮት በቀጣይ ለብቻዋ ልትታሰር ትችላለች›› ነው፡፡ያልተጻፈ መግለጫ በማንበብ መልስ መስጠት ምን ሊሰኝ እንደሚችል ለማንም ግልጽ አይመስለኝም፡፡

2)‹‹ርዕዮት የርቀት ትምህርቱን በመከታተል ላይ ትገኛለች፡፡ይህንንም ከቅድስት ማርያም ዮኒቨርስቲ ኮሌጅ በመጠየቅ ማረጋገጥ ይቻላል››ተብሏል፡፡ወዳጆቼ ተቋም ሲዋሽ ምን ይባላል? ጋዜጠኛዋ ቤተሰብ፣ወዳጅ፣አድናቂና በየሳምንቱ እየሄደ የሚጎበኛት ቁጥሩ ቀላል የማይሰኝ አጋር አላት፡፡ማረሚያ ቤቱ ቢያንስ እነዚህ ምን ይሉኛል አይልም? እንዴት ነው እነዚህ ሰዎች የታረሙ ሰዎችን ሊያፈሩ የሚችሉት?እውነቱ ግን እነርሱ እንደሚሉት አይደለም፡፡ለርዕዮት ከህንዱ ዮኒቨርስቲ የመጡ የመማሪያ መጻህፍት ወደ ማረሚያ ቤቱ እንዲገቡ ያልተፈቀደላቸው በመሆኑ የሚገኙት የጋዜጠኛዋ ወኪል ጋር ነው፡፡(እናንተም ተመልክታችሁ ትፈርዱ ዘንድ መፃህፍቱን ፎቶግራፍ አንስቻለሁ)

ተጨማሪ ያንብቡ:  ባዶ ድምር እያስከተለ ያለዉ መዘዝ(ባድ -መዘዝ) ! - ማላጂ

3) ርዕዮት የዲሲፕሊን ችግር አለባት ያለው የማረሚያ ቤቱ ደብዳቤ በስነ ምግባር ጉድለት መከሰሷን በመጥቀስ እንደ አስፈላጊነቱ በቀጣይ በቀረበባት ክስ ቅጣት ሊጣልባት እንደሚችል አስፈራርቷል፡፡ ርዕዮትን የከሰሳትና የሚመሰክርባት ማን ነው?ዳኞቹስ እነማን ናቸው ? (መቼስ በሪፖርተር ላይ የወጣውን ደብዳቤ የጻፉ ከሆኑ መጨረሻው ምን እንደሚሆን ከወዲሁ መገመት አያስቸግርም)ጋዜጠኛዋ በማረሚያ ቤቱ ውስጥ ለቀረበባት ክስ ጠበቆቿን በማማከር ምላሽ መስጠት ትችላለች?ምስክሮችን የማቅረብ መብትስ አላት?ደብዳቤው ስለ እነዚህ መሰረታዊ ጥያቄዎች የሚለው አንዳች ነገር የለውም፡፡

ባሳለፍነው እሁድ ለንባብ የበቃው የአማርኛው ሪፖርተር ጋዜጣ በደብዳቤዎች አምዱ ከማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ተላከ ያለውን ደብዳቤ አስነብቧል፡፡ከተቋሙ ተላከ የተባለው ደብዳቤ ማህተም፣የአስተዳደሩን ፊርማና ወጪ የተደረገበትን ቀን ያላካተተ ቢሆንም ጋዜጣው ሪፖርተር ታማኝ በመሆኑ ከማረሚያ ቤቱ የተላከ ነው ለማለት በግሌ ድምዳሜ ላይ ደርሻለሁ፡፡በሪፖርተር ታማኝ ምንጭነት ዙሪያ ጥያቄ ያላችሁ ሰዎች ደብዳቤውን ሰንደቅና አዲስ ዘመን ገጽ 3 ላይ የሚጽፉ ያዘጋጁት ይሆናል በማለት መጠርጠር መብታችሁ ይመስለኛል፡፡ወደ ደብዳቤው ዝርዝር ስንገባ ያልታረሙ ሰዎች እነርዕዮትን እናርማለን ብለው በአስተዳደርነት መቀመጣቸውን ወለል ብለውላችሁ ትመለከታላችሁ ፡፡ታገሱኝማ

አስተዳደሩ ደብዳቤውን የላከው አለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት(ሲፒጄ)በማረሚያ ቤቱ የምትገኘውን ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙን በማስመልከት መግለጫ ማውጣቱን ተከትሎ የድርጅቱን ክስ ለማስተባበል ነው፡፡ሲፒጄ በመግለጫው ርዕዮት በርቀት ሁለተኛ ድግሪዋን ለማግኘት ከተመዘገበች በኋላ በማረሚያ ቤቱ እንዳትማር መከልከሏንና  ደረጃውን የጠበቀ የህክምና ክትትል እንደማይደረግላት ማተቱ አይዘነጋም፡፡ለወቀሳው ምላሹን በሪፖርተር የሰጠው ማረሚያ ቤቱ

1)‹‹ርዕዮት ለብቻዋ በዝግ ቤት ታስራለች የተባለው ውሸት ነው፡፡እንዲህ በማለት መናገርም አብረዋት የታሰሩና በአንድ ክፍል ውስጥ የሚገኙ እስረኞችን ሰው አይደሉም በማለት እንደመናገር ይቆጠራል፡፡››ብሏል፡፡አስቂኙ ነገር ሲፒጄ በመግለጫው ርዕዮት ለብቻዋ በዝግ ቤት ታስራለች አለማለቱ ነው፡ከዚህ ይልቅ ሲፒጄ ያለው ‹‹ርዕዮት በቀጣይ ለብቻዋ ልትታሰር ትችላለች›› ነው፡፡ያልተጻፈ መግለጫ በማንበብ መልስ መስጠት ምን ሊሰኝ እንደሚችል ለማንም ግልጽ አይመስለኝም፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ኑሮ በአዲስ አበባ (ነፃነት ዘለቀ – ከአዲስ አበባ)

2)‹‹ርዕዮት የርቀት ትምህርቱን በመከታተል ላይ ትገኛለች፡፡ይህንንም ከቅድስት ማርያም ዮኒቨርስቲ ኮሌጅ በመጠየቅ ማረጋገጥ ይቻላል››ተብሏል፡፡ወዳጆቼ ተቋም ሲዋሽ ምን ይባላል? ጋዜጠኛዋ ቤተሰብ፣ወዳጅ፣አድናቂና በየሳምንቱ እየሄደ የሚጎበኛት ቁጥሩ ቀላል የማይሰኝ አጋር አላት፡፡ማረሚያ ቤቱ ቢያንስ እነዚህ ምን ይሉኛል አይልም? እንዴት ነው እነዚህ ሰዎች የታረሙ ሰዎችን ሊያፈሩ የሚችሉት?እውነቱ ግን እነርሱ እንደሚሉት አይደለም፡፡ለርዕዮት ከህንዱ ዮኒቨርስቲ የመጡ የመማሪያ መጻህፍት ወደ ማረሚያ ቤቱ እንዲገቡ ያልተፈቀደላቸው በመሆኑ የሚገኙት የጋዜጠኛዋ ወኪል ጋር ነው፡፡(እናንተም ተመልክታችሁ ትፈርዱ ዘንድ መፃህፍቱን ፎቶግራፍ አንስቻለሁ)

3) ርዕዮት የዲሲፕሊን ችግር አለባት ያለው የማረሚያ ቤቱ ደብዳቤ በስነ ምግባር ጉድለት መከሰሷን በመጥቀስ እንደ አስፈላጊነቱ በቀጣይ በቀረበባት ክስ ቅጣት ሊጣልባት እንደሚችል አስፈራርቷል፡፡ ርዕዮትን የከሰሳትና የሚመሰክርባት ማን ነው?ዳኞቹስ እነማን ናቸው ? (መቼስ በሪፖርተር ላይ የወጣውን ደብዳቤ የጻፉ ከሆኑ መጨረሻው ምን እንደሚሆን ከወዲሁ መገመት አያስቸግርም)ጋዜጠኛዋ በማረሚያ ቤቱ ውስጥ ለቀረበባት ክስ ጠበቆቿን በማማከር ምላሽ መስጠት ትችላለች?ምስክሮችን የማቅረብ መብትስ አላት?ደብዳቤው ስለ እነዚህ መሰረታዊ ጥያቄዎች የሚለው አንዳች ነገር የለውም፡፡

Share