የአማራን ዘ ር የማጥፋት እኩይ የወያኔ ሤራ

Amhara Women Cry on Eviction from her home by TPLF policy:See the picture

አማራ ሆኖ መኖር በወያኔ መራሹ መንግሥት ዘንድ ወንጀል ነዉ ዋጋ ያስከፍላል በዚህም መሰረት አማራ ለ21ዓመታት በሀገሩ ላይ  ስደት ሞት ውርደት እንግልት ግርፋት መብት የለሽ ሆኖ በመኖር ዋጋ በመክፈል ላይ ይገኛል ወንጀል የሆነበት ዋናው ምክንያት  በዋናነት ኢትዮጵያን ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር በመሆን ከጠላት  ጠብቆ መኖሩ ነዉ ምክንያቱም አሁን በስልጣን ላይ ያለው የወያኔ አመራር አባላት ሀገር ከድተው በተለይም የጣሊያን የባንዳ ልጆች መሆናቸው ነው በቀልን ጥላቻን ይዘው ሀገርን ሰላም በመንሳት ተግተዉ እየሰሩ ያሉት በዚህም መሰረት እንደየደረጃው በተለያዩ ጎሳዎች ግፍ እየተፈጸመ  ይገኛል በቀዳሚነት አማራና ኦሮሞን መጥቀስ በቂ ብቻ ሳይሆን ከበቂ በላይ ነው በተለይ አማራ ማለት ትምክህተኛ ነፍጠኛ በሚለው የስድብ ቃል ሃያ አራት ሰዓት በወያኔ  የፕሮፓጋንዳ ማሰራጫ ጣቢያዎች ኢቲቪ ሬድዮ ፋና  ኤፍኤም በየቀኑ መስማት የተለመደ ነው

ወያኔ ከደደቢት አዲስአበባ ቤተ መንግሥት የሚደክመውና ተግቶ እየሰራ ያለው አማራን ከኢትዮጵያ  ዘሩን ጨርሶ በአማራ መቃብር ላይ ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር ማጥፋት በኦሮሞ ህዝብ  በጉራጌ ህዝብ በሁሉም ብሄር ብሄረሰቦች ላይም ተመሳሳይ ግፍ እየተፈጸመ ያለው ኢትጵያዊነት ለማጥፋት ካለው አጀንዳ ነው

አቦይ ስብሃት እኔ ግን አቦይ የሚለውን የክብር ስም ሊጠራበት አይገባውም ይልቁንም ዕቡይ ስብሃት ተብሎ ቢጠራየተሻለ ነው እላለሁ ይህ ክፉ መንፈስ ያደረበት ሰው በተደጋጋሚ ሲፎክር እንደሰማነው  አማራና ኦርቶዶክስ ሃይማኖትን አጥፍተናቸዋል  ቦታ የላቸውም የሚል ነበር ነገሩን እንደቀላል ነገር ልናየው እንችላለን ይህ ዘመን የሰጠው  እንደልቡ ተናጋሪ የሆነ ሰው  የተናገረው የሰሩትን እውነታና እየሰሩ ያሉትን ነገር ነው

አዲስአበባ እንደገቡ ያለምንም ጥፋት ብቻ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ምሁራን በሀገራቸው ላይ ስራ እንዳይሰሩ ታግደዋል ከአዲስአበባ ዩኒቨርቲና ከተለያዩ ተቋማት ተባረዋል ይህ ሆን ብሎ የአማራን ተወላጅ ለማጥፋት ካለው መሰረታዊ አጀንዳ የመነጨ ነው በምትካቸው ከሌሎች ሀገሮች ማለትም ከሕንድ፣ከጋና መምህራኖች ቀጥሮ ያመጣው  በዚሁ ምክንያት ነው

በጎንደር በተለይም በወልቃይት ፣በጠገዴ ፣በጠለምት፣በደብረታቦር በጎጃም በሰሜን ሸዋ በደብረብርሃን ይህ ነው የማይባል የዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈጽሟል,በጥናት ላይ የተመሰረተ ከባድ የሆነ የዘርማጥፋት ወንጀል ዛሬም በመፈጸም ላይ ይገኛል

የበደኖ የአርባ ጉጉ ወዘተ ወንጀሎች ሁሉ ወዘተ ተመሳሳይ ወንጀሎች ተፈጽመዋል ሁሉም ጊዜውን ጠብቆ ይወጣል ሰው ሊያውቀዉ በማይችለው ሁኔታ በሕክምና ተቋማት በኩል በክትባት ስም በአማራ ሕፃናት ላይየHIV vires ጨምሮ የተለያዩ ኢሰብአዊ  ድርጊቶች ተፈጽመዋል፣ነገር ግን ለሁሉም ጊዜ አለው እንደተባለው ለጊዜ መተው ይሻላል

አማራነት ካመጣቸው ችግሮች  ትንሾቹን እንይ

ወያኔ ኢህአዴግ አዲስ አበባ እንደገባ በአማራ ላይ የተወሰዱ እርምጃዎች

1ኛ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ ከመንበራቸው ወይም ከሥልጣናቸው እንዲወርዱና እንዲገላቱ በመጨረሻም በሃገራቸው መኖር ባለመቻላቸው እንደሌሎች የአማራ ተወላጆች አማራ በመሆናቸው ብቻ ለስደት ፣ለዕንግልት፣ ተዳርገዋል,

ዛሬ ወያኔ  የራሱን ምልምል ፓትርያርክ በማስቀመጥ ዛሬ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የአንድ የወያኔ  ተቋም ሁና በመስራት ላይ መሆኗን እያየን ነው በዚህም መሰረት በዕቡይ ስብሐት  ንግግር መሰረት የኢትዮጵን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አጥፍተናታል እንዳለው ዛሬ ቤተ ክርስቲያኗ ከመንፈሳዊና ከማኅበራዊ አገልግሎት ውጭ ሁና የሚታየው መሞቷን የሚያረጋግጥልን ጉዳይ ነው

2ኛ ፕሮፌሰር አስራት ወ/ ኢየሱስን ያሳሰረ ያንገላታ ያሰቃየ ለሞትም ያደረሰ ሌላ ወንጀል አይደለም አማራነት ብቻ ነው

ተጨማሪ ያንብቡ:  ያመመን ያለዉ የአድርባይነት እና ጥላቻ  ሰንኮፍ ነዉ ! - ማላጂ

3ኛ አቶ ተስፋየ ማሩን በጠራራ ፀሀይ በጥይት ያስገደለ ወንጀል አማራነት ብቻ ነው

አማራ እንደማንኛውም የሃገሪቱ ዜጎች አፈር ገፍቶ አዳረ ሠራተኛ ታታሪ ሀገሩን የሚወድ ሕዝብ ነው፣ ይህ ህዝብ  ከሌሎች ኢትዮጵያውን ጋር ማለትም ከትግራይ ወገኖቹ ጋርም በሰላምም በችግርም ወቅት አብሮ የኖረ መሆኑ ቀርቶ እንደ ክፉጠላትተቆጥሮ መከራ እየተቀበለ ያለ ህዝብ ነው

አማራ ለችግሩ ደራሽ ወገን አጥቶ 21 ዓመታት የሰው ልጅ ሊሸከመው የማይችል የመከራ ጽዋን እየተጋተ የሚገኝ አሳዛኝ ሕዝብ መሆኑ ግልፅ ነው

አንድ እዉነተኛ ታሪከ ልንገራችሁ የውጭ ሀገር የትምህረት ዕድል  ይገኝና ወደ ዉጭ ሄዶ መማር የሚፈልግ ተማሪ ሁሉ መመዝገብ ይችላል የሚል ማስታወቂያ ይወጣና ሁሉም ተማረ እንደፍላጎቱ  ለመመዝገብ ወደ መመዝገቢያ ቦታው ሲሄዱ አንድ ካድሪ ተኮፍሶ ቁጭ ብሎአል ከዚያም ተመዝጋቢዎችም ቀርበው ስም ሲጠየቁ በመጀመሪያ የትግራይ ልጆች ቀርበው ይመዘገባሉ ሁሉም መመዘኛዉን አለፉ መመዘኛዉም ዕዉቀት መሆኑ ቀርቶ ብሔር በመሆኑ ሌሎችም እየቀረቡ ይመዘገባሉ በመጨረሻ አንድ የዋህ ተማሪ ተራዉ ደርሶ ይቀርባል፣ መዝጋቢዉ ካድሪ ቀና ብሎ ያየዉና ከፊቱ የቆመዉን ተማሪ ብሄር ህ ምንድ ነው  ይለዋል ተማሪዉም በፍርሃት አማራ ይላል ያኔ ካድሪዉ ቆም ብሎ በቁጣ ከአማራ የሆናችሁ ዉጡ ከአማራ ብሄር አንወስድም የምንመዘገበው ከሌሎች ብሔሮች ብቻ ነው ይላል ይህን የሰማ ወላጆቹ አማራ የሆኑ ተማሪ ሌሎች የአማራ ተወላጆች የሆኑ ተማሪዎች ሲወጡ በድፍረት ይቀርና ሰልፉን እንደያዘ ይቆያል ተራው ደርሶት ወደ ካድሪው ቀርቦ ብሄር ይጠየቃል እሱም ኮራ ብሎ ደቡብ ሕዝቦች ይላል ወዲያዉኑ ከአፉ ተቀብሎ ካድሪዉ በብሔርህ አልፈሃል ግን ለሌሎች ብሔሮች ቅድሚያ ስለሚሰጥ ምናልባት ቦታ ካለ ስምህ በማስታወቂያ መለጥፊያ ቦታ በ15 ቀናት ዉስጥ ይወጣል ተከታተል ተብሎ ሲከታተል እንዳጋጣሚ ዕድሉን አግኝቶ ወደ ዉጭ ሃገር መጥቶ ትምህርቱን በመከታተል ይገኛል ከወደ ኋላ መለስ ብሎ በማሰብ ደፋርና ጭስ መዉጫ አያጣም ሆኖ ነዉ እንጂ ያኔ መንዜ መሆኔን ቢያዉቁ በሽርብተኝነት ወንጀል  ዘብጥያ ያወርዱኝ ነበር በማለት በሃዘን ትዝታ ያጫወተኝ

በአማራ ላይ ያልተፈጸመ ኢሰብአዊ ድርጊት የለም ሌላዉ ቀርቶ ብአዴን የሚሉት ድርጅት  አማራዉን እወክላለሁ ብሎ በሕወሐት የሚመራው ፓርቲ ዉስጥ አማራዉን የሚወክል ሰዉ እንደጠፋ ሁሉ ሆን ተብሎ አማራዉን ለማጥፋት ከሚሰራዉ ሕወሐትና ከሌሎች ብሄሮች የተዉጣጡ የጸረ አማራ ስብስብ መሆኑ ግልጽ ነዉ ድርጅቱ መለያ አርማውም ሆነ አመራሮቹ የሕወሐት ሰዎች መሆናቸዉን ለአብነት እንይ ,

እኔ እስከማዉቀዉ ድረስ ዋና ዋናዎቹ የአመራር አባላት

1ኛ ተሰማ  ገ/ሕይወት 2ኛ አቶ ካሣ ተ/ብርሃን 3ኛ አቶ አዲሱ ለገሰ 4ኛ ህላዌ ዮሴፍ ወዘተ የአማራ ተወላጆች ናቸዉ የምትሉ ካላችሁ የዋሆች ናችሁ አማራ ማለት በሕወሐት ዕምነት ጠላት ነዉ ዘፈኑን  እስቲ እናስታዉስ ገረብ ገረብ ትግራይ መቃብር አምሃራይ የትግራይ ሸለቆዎች ተራራዎች የአማራ መቃብር ናቸዉ  ወይም ይሆናሉ እያለ በቅዠትም በህልምም በዉኑ ም ጸረ አማራ ሆኖ የተፈጠረዉ ወያኔ ነዉ ብአዴን ማለት

አማራ መሆን እንዲያሳፍር አንገት እንዲያስቀልስ  እንዲያሸማቅቅ ለ21 ዓመታት ሲሰራ የኖረዉ አማራ ፈሪ ነዉ በሚለዉ በኢያሱ በርሄ ዜማ አማራን እየተከታተለ ዘሩን በማጥፋትና በኢትዮጵያዊነቱ ተከብሮ ሌላዉንም አክብሮ ከሚኖርበት አካባቢ እተፈናቀለ የሚገኘዉ ከደደቢት ጀምሮ አማራን ለማጥፋት በተያዘዉ  ዕቅድ መሰረት እተፈጸመ ያለ ሂደት ነዉ ,

አማራን ከቤንሻንጉል ጉምዝ ማስወጣት ማለት ምን ማለት እንደሆነ ሕሊና ያለዉ ሁሉ ሰዉ በራሱ ዳኝነት ይየዉ

ተጨማሪ ያንብቡ:  ይህ ሁሉ ወንጀል እየተሠራ ያለው በሁለቱም መሪዎቻችን ግፊት ነው! - ምሕረቱ ዘገዬ

አማራን መዉጫ መግቢያ በማሳጣት ከዚያች ሃገር ማጥፋት ነዉ,ከ2 4 ሚሊዮን የአማራ ሕዝብ በወያኔ አረመኒያዊ ተግባር ወንጀል ተፈጽሞበት ጠፍቷል እንዴት ጠፋ ወደፊት ኢትዮጵያዊ መንግስት ሲኖር የሚታይ ይሆናል የአማራ ወንጀል ኢትዮጵያዊነቱ እንደሆነ ግልፅ ነዉ  ይችን ሃገር ከሌሎች ወንድሞቹ ጋር በመሆን ደሙን አፍሶ ከጠላት ጠብቆ መኖሩ ነዉ  ወንጀሉ ሌላ ምንም ወንጀል የለበትም

አሁን ከጉራ ፈርዳ ከቤንሻንጉል ክልሎች የሚፈናቀሉት አማራ ሆኖ መኖር ወንጀል በመሆኑ ብቻ ነዉ ይህም እየሆነ ያለዉ በህወሐት ጨካኝና ጎጠኛ ድርጅት ስለሆነ ሁሉም ኢትዮጵያዊ አንድ ሆኖ ሊጋፈጠዉ ይገባል ይህ ጊዜ ያልፋል በሚያልፍ ጊዜ የማያልፍ ታሪክ ሰርተን ማለፍ  አለብን በሰላማዊ ትግል መታገል አይቻልም በተለይ አማራ ሆኖ የማይታሰብ ጉዳይ ነው ወጣቱ ፖለቲከኛ አንዱዓለም አራጌ በሰላም መታገሉ ወንጀል ሆኖበት ቃሊቲ እንዲወረወር ያደረገዉ አማራ መሆኑ ብቻ ነው

በቤንሻጉል የዘር ማፅዳት ወንጀል ነዉ እየተፈጸመ ያለዉ ዘርን መሰረት አድርጎ ሌሎችን በማነሳሳት የሚፈጸም ወንጀል ነው በዚህ ወንጀል ሌሎች ኢትዮጵያዉያን እጃችሁን ባታስገቡ መልካም ነ ዉ ይህ ነገር ዝም ብሎ

የሚቀር   አይሆነም ዋጋ ያስከፍላል ዐይንና ጆሮ የሌለዉ ህወሃት ዛሬ አማራን ማጥፋቱን እ ንጂ ነገ ሊያመጣ የሚለውዉን  ችግር የሚያይበት ዐይን የለዉም , ምክንያቱም ዕብሪተኛ  ስለሆነ ብቻ ,ሰው በሃገሩ ላይ ከተፈናቀለ ምን ሃገር አለዉ ሊባል  ይችላል ሊባል የሚችለዉ በሀገሩ ላይ ስደተኛ የሆነ ማለት ነዉ ይህ ይህ ደግሞ ለማንም አይበጅም ተጎጂ የሚሆነዉ አማራ ብቻ አይሆንም የሁሉንም  ቤት ያንኳኩል,የትግራይ ተወላጆችስ አማራ ውስጥ የሉም ወይ እንዲያዉም ጎንደር፣ ባህርዳር፣ ደሴ የትግራይ ከተሞች እስኪመስሉ ድረስ የትግራይ ልጆች መኖሪያ መስሪያ ከተሞች ናቸዉ ሌላዉ ቀርቶ የአማራ ቲሺ አንባቢዎች   በነክብሮም ወ/ስላሴ በነ ህሊና መብራቱ የተያዘዉ አማርኛ ዜና አንባቢ ክአማራ ተወላጆች ሰው  ስለጠፋ ሊሆን እንደማይችል ተስፋ አደርጋለሁ ይህን የምለዉ በወያኔ ስሌት እንጂ በእኔ ዕምነት ትግሬዎችም በአማራም ሆነ በሌሎች ቦታዎች ሰርቶ መኖር ኢትዮጵያዊ መብታቸዉ ነው ስለዚህ የትግራይ ልጆች በአማራዉ ወንድማቸዉ እየደረሰ ያለዉን ችግር ከአማራዉ ከኦሮ

ሞዉ ከጉራጌዉ ከአፋሩ ጎን በመቆም ወገናዊነታቸዉን ማሳየት ከምንጊዜዉም በበለጠ ይጠበቅባቸዋል,ወያኔ  ሁሉንም አጋጭቶ ማለፍ ስለሆነ አላማዉ ጥላቻን አስወግደን ወያኔን ልንፋለመዉ ይገባል በአማራ ተወላጅ ላይ በወያኔ የግፍ አገዛዝ ያልሆነ ምንም ነገር የለም በቤት ዉስጥ እንዳሉ በዕሳት ተቃጥለዋል ,በተኙበት ተደብድበዉ ተገለዋል እንደእንስሳ ታርደዋል ተገለዋል ይህ ሁሉ የሆነ አንድ  ጊዜ ወይም ሁለት ጊዜ አይደለም ወያኔ ከጫካ ህይወቱ ጀምሮ እስካሁን በአማራ ሕዝብ ላይ እያደረሰዉ ያለዉ ግፍና መከራ  ነዉ

አንድ በዕድሜዉ ሸምገል ያለ ሰዉ ብሔራዊ ቲያትር አካባቢ ብቻዉን እያወራ ይሄዳል ምን እንደሚል ጠጋ ብዬ ለመስማት ወደ ሰዉዬዉ  ሄድኩ ድምጹን ከፍ አድርጎ ቢገሉህ የማታልቅ ህዝብ ነበር የሚለዉ እዉነትም ቢገሉት የማያልቅ ህዝብ ልክ እንደ አማራ ህዝብ የኦሮሞ ህዝብ በሃገሩ ላይ ተዋርዷል፣ ታስሯል ፣ተገርፏል ፣ተገሏል በሙሉ ኢትዮጵያዉያን  የዜግነት መብታቸዉን ተገፈዋል , በሀገራቸዉ እንደ ሁለተኛ ዜጋ ተቆጥረዋል,ዛሬ በኢትዮጵያ ዉስጥ በየትኛዉም ቦታ ከትግራይ ተወላጆች ውጭ በወያኔ ሥርዓት ተጠቃሚ የሆነ ከአንዳንድ ካድሪዎች ዉጭ አንድም የሌላ የኢትዮጵያ ብሔር ተወላጅ የለም ,ሌላዉ ቀርቶ በዉጭ ያሉ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎችን በየሃገሩ መመልከት ይቻላል በሚያሳፍር ሁኔታ ለትግራይ ልጆች ብቻ አገልግሎት እንዲሰጥ ሁኖ የተዋቀረ መሆኑን ላለፉት 21 ዓመታት ያየነዉ ይህ ደግሞ ለአንድነታችን አደጋኛ ሁኔታ መሆኑን አዉቀዉ እንዲህ ዐይነቱን ሥራ መቃወም የግድ ይላል , በየሀገሩ ኢትዮጵያዉን በኢትዮጵያ ኤምባሲ በር ላይ እንደ እባብ ራስ ራሳቸዉን ተቀጥቅጠዉ ሲሞቱ ማን ደረሰላቸዉ ማንም የደረሰላቸዉ የለም ምክንያቱም የሕወሃት አባል ወይም የትግራይ ተወላጅ እስካልሆኑ ድረስ ኤምባሲዉ እንደማይመለከተዉ ያየነዉ ጉዳይ ነዉ ,አንድ ጊዜ ሀገር ቤት የሆነዉን ማስታወስ የግድ ሆነብኝ በኦሮምያ ክልል ዉስጥ አንድ የትግራይ ተወላጅ በሆነ በተፈጠረ ግጭት ህይወቱ አለፈች , በዚህም ምክንያት አካባቢዉ ቀዉጢ ሆነ በሙሉ ትንሽ ትልቁ ተጋፎ ወደ እስር ቤት ገባ ከዚያ በኋላ በእስር ቤት ዉስጥ የሆነዉን እግዚአብሔር ይወቀዉ ,የሟቹ አስከሬንም በክብር ወደ ትግራይ ሄዶ መስሪያ ቤት ተዘግቶ የሀዘን ቀን ሆኖ ሥርዓተ ቀብሩ ተፈጽሟል,ታዲያ ለሌላዉ ኢትዮጵያዊ ማን ይድረስለት አሁን ያለዉ የወያኔ መንግስት ዘረኛ ስለሆነ ተፈጥሮዉ ኢትዮጵያዊ ስላልሆነ አሁንም ኢትዮጵያን ከማፍረስ ዉጭ ሌላ ነገር መጠበቅ ከዕባብ ዕንቁላል የርግብ ጫጩት እንደመጠበቅ ይቆጠራል,የአማራ፣የኦሮሞ

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሰላማዊ የመብት ጥያቄ በሠለጠነ ውይይት እንጂ በአፈናና ግድያ መቼም ቢሆን አይፈታም!

፣የጋምቤላ፣ የአፋር የጉራጌ ወዘተ ልጆች ግን በየቀኑ ወያኔ ባዘጋጀዉ ወጥመድ ዉስጥ ገብተዉ ምንም የማያዉቁ ሕጻናት በየቀኑ ሕይወታቸዉ በማለፍ ላይ ይገኛል,

በቤንሻጉል በጉራፈርዳ በጋምቤላ አሁንም ግፍ እየተፈጸመ ነዉ ያለዉ አማራዎቹ ወደ መጡበትይመለሱ እንጂ በዚያ ምን ዐይነት ወንጀል እየተፈጸመባቸዉ እንደሆነ የምናዉቀዉ ምንም ነገር የለም ,የምንሰማዉ ነገር ግን ከሚዲያ እንዲርቁ            አድርጎ የዘር ማጥፋቱ ወንጀል በከፋ ሁኔታ እየተፈጸመባቸዉ ነዉ ,አሁን የሞተዉን ህዝብ ታሪክ ማዉራቱ ምንም ፋይዳ የለም ወያኔ በስልጣን ላይ እስካለ ድረስ ሞት፣ ስደት፣  ዉርደት በአማራ ህዝብ ላይ የማይቋረጥ ሂደት ነዉ ,

በአማራ ሰላማዉያን ዜጎች ላይ እየደረሰ ያለዉን አደጋ ወያኔ እንዲያቆም ከተፈለገ ስራ መስራት ያስፈልጋል,አሁን ይህንን ወንጀል የፈጸመዉ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዉንን በማጥፋት ያለዉ ወያኔ ብቻ ሳይሆን ይህ ድርጊት ሲፈጸም ዝም ብለዉ

ያዩ የሃይማኖት መሪዎች፣ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ምሁራን ፣ታዋቂ ግለሰቦች ሁሉ በተባባሪነት ወንጀል ይጠየቃሉ,ሁላችንም ተጠያቂዎች ከመሆን ለመዳን ከጎሳ ፖለቲካ በመዉጣት እጅ ለእጅ ተያይዘን ወያኔን መታገል የግድ ነዉ ,ካሁን በኋላ ከወሬ ያለፈ ሥራ መስራት ካልቻልን የወያኔ የዘር ማጥፋት ወንጀል አያቆምም ምናልባት የሚሆነው ከአማራዉ ወደ ኦሮሞዉ ከኦሮሞዉ ወደ ወላይታዉ በፈረቃ እንደ አዲስአበባ መብራት እየተዘዋወረ ይቀጥላል እንጂ አይቆምም እየሞቱ ከመኖር እየኖሩ መሞት አማራጭ የሌለዉ መፍትሔ ይሆናል,ወያኔ በየጊዜዉ ወንጀል በፈጸመ ቁጥር ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እንዲያዉቀዉ ከማድረጉ ባሻገር ለዘላቂ መፍትሔ የትግል መስመር መቀየስ ያስፈልጋል ,የሰላማዊ ትግል ሁኔታ ሃያ አንድ ዓመታት የታዬ ስለሆነ በሱ ላይ ጊዜ ማጥፋት አያስፈልግም ,የሰላማዊ ትግል ሂደትበሽብርተኛ ስም ጉዞዉ እስከቃሊቲ ድረስ ብቻ ይሆናል,ሁሉም ኢትዮጵያዊ ልዩነቱን አስወግዶ በኣንድነት በመታገል ነጻ ሊወጣ ወይም በጎሳ ተከፋፍሎ

በሀገሩ ላይ ስደተኛ ባሪያ ሁኖ በወያኔ የባርነት ወጥመድ ዉስጥ ለዘለዓም መኖር ይሆናል ,

ወያኔን በጸረ ኢትዮጵያዊነት የሚቀድመዉ እንጅ የሚበልጠዉ የለም እንደዚህ ዐይነት የዉርደት ፣የስቃይ፣ የጥፋት ዘመን በታሪክ ተፈጥሮ አያዉቅም ESAT TVን  በመደገፍ የምናሳየዉ ትብብር ከቀጠለና ለሌላዉም የትግል መስመር እንደዚህ ከተባበርን ወያኔን የማናጠፋበት ምንም ምክንያት አይኖርም

ወያኔን በቃ ብለን እንነሳ በየቀኑ እንደቅጠል ለሚረግፉ ወገኖቻችን እንድረስላቸዉ ወያኔን በሚገባው ቋንቋ እናነጋግረዉ

ሰላም ድል ለኢትዮጵያዉን

 

 

 

ዲያቆን /መምህር/ ፍስሓ ዘዳሞት

3 Comments

  1. Am so puzzled and boared hearing about woyane;s serialized high profile crime of Ethnic cleansing of the Amharas,gambelans and others. Are we serious about it to nip in the bud the woyanes grandeur emanated from inferiority complex driving to committing crimes towards humanity like Hitler who exterminated the jews motivated by wishful thinking to install Aryan supremacy just what the woyane is equally dig in to make the Tigryans a power house of East Africa by way of stealing,decieving the Ethiopian people and looting ,plundring, the resources of the Ethiopian people. But the problem is how can we stop such crimes ? the answer is simple : by united force ? is it easier to get united and challenge woyane as one ? yes it is easier. But hard to make it because there are certain political organizations allying with Shabia and work hand in glove .So how come organizations that have animosity with one of our dead enemy Shabia expected to hook up with these political parties? is it not a political puzzle.?

  2. Diacon Dillu,
    ይህን ሁሉ ዝባዝንኪ ስትጽፍ ላንተ ኣዘንኩኝ ተምረህ እውቀትን ሳትሸምት: በሰለጠነ ኣገር ኖረህ ምንም ሳታውቅ መቅረትህ!!!!

Comments are closed.

Share