በዉጭ ያሉ ተቃዋሚዎችን ለማሰባሰብ የሚረዱ ነጥቦች – ክፍል አንድ

አማኑኤል ዘሰላም
ሚያዚያ 11 ቀን 2005 ዓ.ም
amanuelzeselam@gmail.com

በዉጭ አገር የፖለቲካ ድርጅቶች ነን የሚሉ ፣ የፖለቲካ ድርጅቶች አይደለንም ብለውም በፖለቲካዉ ጨዋታ ድምጻቸውን የሚያሰሙ ጥቂቶች አይደሉም።  የኢሳት ቴሌቭዥን አለ። በርካታ ድህረ ገጾች አሉ። ራዲዮ ጣቢያዎችማ በተለይም በዲሲ በሽበሽ ናቸው። በተለያዩ ጊዜ ፣ በተለያዩ ጉዳዮች የተለያዩ የአቋም መግለጫዎች፣ በተለያዩ ድርጅቶች ይወጣሉ። መግለጫዎቹ በሙሉ «ተቃዋሚዎች በአንድ ላይ መሰባሰብ አለብን፤ በአንድ ድምጽ መናገር መቻል አለብን፤ ከሌሎች ጋር አብሮ ለመስራት ድርጅታችን ያለዉን ቁርጠኝነት ያረጋግጣል» የሚል ይዘት ነበራቸው።

ሰሞኑን ከቤኔሻንጉል በተፈናቀሉ ወገኖቻችን ላይ የተከሰተዉን የዘር ማጥፋት ወንጀል አስመልክቶ፣ እንደለመድነዉ፣ የመግለጫ ናዳዎች ከተለያዩ በዉጭ አገር ካሉ ማእዘናት እያነበብን ነዉ።  ዜጎች፣ ድርጅቶች የተሰማቸዉን ስሜት መግለጻቸው በራሱ ችግር የለዉም። ተገቢም ነዉ። ነገር ግን ዛሬም ትግላችን፣ መግለጫዎች በማውጣት ላይ ብቻ የተወሰነ መሆኑ ግን በጣም ያሳዝናል።

እንግዲህ መግለጫዎች ከማውጣት ያለፈ ሥራ ለመስራት፣ አንዱና ዋናዉ አስፈላጊ ነገር ትብብር ነዉ። በአለም አቀፉ ማህበረሰብ ተሰሚነት እንዲኖረን፣ ዉጭ ያለዉም ሕዝባችን በኛ ላይ ያለዉ ድጋፉ እንዲበዛ፣  በሚያስማሙ ነጥቦች ላይ አብረን መስራት መቻል አለብን። ለዚህም አብረን እንዳንሰራ መሰናክል የሆኑብንን  ችግሮች ማስወገድ ይገባል።

በኢትዮጵያዉያን መካከል መሰባሰብና መስማማት እንዳይኖር ያደረጉ ሶስት ችግሮች አሉ። የመጀመሪያዉ ከሻእቢያ ጋር አብሮ የመስራቱ ሁኔታ ነዉ። «ወያኔን ለመጣል እስከረዳን ድረስ የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነዉ» በሚል የተሳሳተ መርህ፣ ሁለቱም የኦነግ አንጃዎች እና የግንቦት ሰባት ንቅናቄ የመሳሰሉቱ  ከአቶ ኢሳያስ መንግስት ጋር በቅርበት የሚሰሩ ናቸው።

አብዛኞቻችን ሻእቢያን ከኢሕአዴግ ያልተሻለ እንደዉም የባሰ አድርገን ነዉ የምናየዉ።  በኤርትራ በኩል የሚደረገዉንም ትግል አጥብቀን እንቃወማለን።  በዚህም ምክንያት አፍቃሪ ሻእቢያ በሆኑና በተቀረነዉ መካከል ትልቅ ገደል ተፈጥሮ ነበር።

ይሄ እንግዲህ እስከአሁን የነበረው ነዉ። ከሻእቢያ ጋር በመስራቱ ዙሪያ፣  ከአሁን በኋላ መከፋፈል ይኖራል ብዬ ግን አላስብም። ከሻእቢያ ጋር እንስራ የሚሉ ሰዎች እንደተሳሳቱ የተረዱበት ሁኔታ ነዉ ይመስለኛል። በተለይም የአርበኞች ግንባር አመራር አባላት መገደላቸዉና መሰወራቸው፤ የጀነራል ከማል ገልቹና ጀነራል ሃይሎ ጎንፋ መታሰር፣ የግንቦት ሰባት ጥቂት ሰራተኞች አስመራን ለቆ መዉጣት፣ አንጋፋ የተባሉ፣ አፍቃሪ ሻእቢያ የነበሩ፣ የኦነግ መስራቾችና የአመራር አባላት ኦነግን በአዲስ መልክ በአዲስ ስም አዋቅረዉ፣ ከሻእቢያ ጥገኝነት ነጻ የሆነ እንቅስቃሴ መጀመራቸው፣ የተባበሩት መንግስታት በኤርትራ ላይ የዘረጋዉ ማእቀብ፣ በአስመራ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየታየ የመጣዉ የፖለቲካ አለመረጋጋት፣  በኤርትራ በኩል የመታገል ፖለቲካ የማያዋጣ፣ የማያስኬድና እራስን እንደማጥፋት ያህል የሚያስቆጥር መሆኑ የሚያመላክቱ ናቸዉ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ድሮስ ፤  ከእባብ እንቁላል እርግብ ይገኛልን ??? - ሲና ዘ ሙሴ

በመሆኑም «ትግል በኤርትር በኩል ይደረግ አይደረግ» የሚል ክርክር፣  ከአሁን በኋላ ሊነሳ ይችላል ብዬ አላስብም። እንዳንስማማ ያደረገ ይሄ አንዱ ትልቁ መሰናክል ተወገደልን ማለት ነዉ።

ሁለተኛው መሰናክል የትጥቅ ትግል ወይስ ሰላማዊ ትግል የሚለዉ ነዉ። የትጥቅ ትግል ለማድረግ ቤዝ ያስፈልጋል። በርካታ የትጥቅ ትግል እናደርጋለን የሚሉ ቡድኖች አስመራ መጀመሪያዉኑ የተከሉት በዚሁ ምክንያት ነበር። መሳሪያ፣ መድሃኒት፣ ምግብ የሚያቀብላቸው፤ ወታደሮቻቸዉን የሚያሰለጥኑበት ኮሪዶር ያስፈልጋቸዋል። በኤርትር በኩል መስራቱ የማያወጣ በመሆኑ፣ ኤርትራን ካልተጠቀመን ደግሞ ሌላ ሊረዳ የሚችል ጎሮቤት አገር ባለመኖሩ፣ የትጥቅ ትግል ማድረጉ፣ ብንፈልገዉም፣ የማይቻል ነዉ።

«አይ የትጠቅ ትግሉን በአገር ዉስጥ ማካሄድ ይቻላል» የሚል ሃሳብ ሊቀርብ ይችላል። ይሄ ደግሞ በስድሳዎቹ እንደ ኢሕአፓ ያሉ የሞከሩት፣ ብዙ ወጣቶች ያሰጨረሰዉ  አይነት፣ አሁን ደግሞ በሲሪያ እያየን እንዳለነው፣  እንኳን ሊሞከር ሊታሰብ የማይገባ ነዉ።

ስለዚህ የትጥቅ ትግል ማድረጉ ዉጤት ካላመጣና ጠቃሚ ካልሆነ፣ እንቀጥለው እንኳን ብንል መቀጠል የምንችልበት ሁኔታ ከሌላ፣ ጥይት፣ መድሃኒት  የሚያቀርብለን የጎሮቤት አገር  ድጋፍ ካለገኘን፣ የትጥቅ ትግሉን እንደ አንድ አማራጭ መዉሰድ አይቻልም። በመሆኑም «ሰላማዊ ትግል ወይስ የትጥቅ ትግል» የሚል ክርክር ከአሁን በኋላ የሚነሳበት ምክንያት የለም። እንዳንስማማ ያደረገ ሁለተኛዉ ትልቁ መሰናክል በዚህ መልኩ ተወግደልን ማለት ነዉ።

ሌላዉ በዳያስፖራ ያሉ ተቃዋሚዎች እንዳይተባበሩ መሰናክል የሚፈጥረዉ ጉዳይ ቢኖር የአገር ቤቱ ትግል ነዉ። አንዳንዶቻችን በዉጭ ሆነን የአገር ቤት ትግሉን መምራት እንፈልጋለን። ይሄ ትልቅ ስህተት ነዉ። ከዉጭ በሚደረግ ትግል በኢትዮጵያ ለዉጥ ማምጣት አይቻልም። አራት ነጠብ። ዉጭ አገር ያለነዉ ማተኮር ያለብን የአገር ቤቱን ትግል በማገዙና በመርዳቱ ዙሪያ መሆን አለበት።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአማራ የሕልውና ትግል ላማረኛ ቋንቋ የከፈተው ትልቅ ዕድል

ኢሕአዴግ በሃያ አመታት እድሜዉ ለመጀመሪያ  ጊዜ የተነቃነቀዉ በቅንጅት እንቅስቃሴ ነዉ።  ያኔ በዉጭ አገር የሚገኘዉ ኢትዮጵያዊ  በድጋፍ ድርጅቶች በመሰባሰብ፣ የአገር ቤቱን ትግል ይረዳ ነበር። ያኔ በዉጭ ያሉ ተቃዋሚዎቾ በሕብረት ሥር በመሰባሰብ፣  የአገር ቤት ትግሉን ይረዱ ነበር። በዚህም ምክንያት ነዉ፣  ያኔ ያየነዉን ያየነዉ።

 

እርግጥ ነዉ ቅንጅት/ሕብረት መድረስ የነበረባቸው ደረጃ አልደረሱም። ነገር ግን ብዙ መንገድ ተኪዶ ነበር። እንግዲህ የሚያዋጣን በቅንጅት ጊዜ የተሰሩት መልካም ስራዎችን በመድገም ፣ የተሰሩ ስህተቶችን በማረም፣ የአገር ቤቱን ትግልና የዉጭ አገሩን ትግል አቀናጅቶ መቀጠሉ ነዉ እንጂ፣  ከዚህ በፊት በተሰሩ ስህተቶች ተስፋ ቆርጠን፣ ለዉርደት እራሳችንን አሳልፈን መስጠት የለብንም። እርግጥ ነዉ ከዚህ በፊት ወድቀናል፣ ቆስለናል። ገር ግን ከአሁን ለአሁን እንደገና እንወድቃለን ብለን፣  በፍርሃትና በጥርጣሬ ተሞልተን ለመነሳት ካልሞከርን፣ በወደቅንበት በስብሰን  ሞተን ነዉ የምንቀረዉ።

እንግዲህ በሰላማዊ የእምቢተኝነት ትግል የሚያምኑ፣ ከሻእቢያ ጋር ግንኙነት የሌላቸው ወይንም ግንኙነታቸውን በኢፊሴል የበጠሱ፣ የኢትዮጵያን አንድነት የሚያምኑ፣ ትግሉ አገር ቤት እንደሆነ ተረድተዉ፣  አንዳንዶች እንደሚያደርጉት ፣ የአገር ቤት ትግሉን ማሳነስ ሳይሆን፣  የሚደግፉ ኃይላት በሙሉ በአንድ ላይ መሰባሰብ አይቸግራቸውም። አለባቸውምም።

ድነት/መድረክ የድጋፍ ድርጅቶችና በነአቶ ኦባንግ ሜቶ የሚመራዉ የሶሊዳሪት ንቅናቄ፣ በሰላማዊ ትግል የሚንቀሳቀሱ መሆናቸዉ ይታወቃል። በነ ዶር ፍስሃ የሚመራዉ የሽግግር መንግስት ምክር ቤትም በይፋ የትግል ስልቱ ሰላማዊ እምቢተኝነት እንደሆነ አሳዉቋል። በዘጠና ሰባት ወቅት ከነዶር መራር ጉዲና ጋር በቅርበት ይሰሩ የነበሩ ድርጅቶች ያሉበት፣ ሸንጎ፣ በዉስጡ ያሉ ድርጅቶች አንዳንዴ «ሁሉ ገብ» ትግል የሚል ያለፈበት ፈሊጥ ቢኖራቸውም፣  ሸንጎ እንደ ሸንጎ በሰላማዊ ትግል የሚያምን ስብስብ ነዉ። በቀድሞ የኦነግ አመራር አባላት በቅርቡ የተቋቋመዉ፣ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባርም፣ ኦነግ ላለፉት በርካታ አመታት፣ ኦሮሞዎችን ከማስጨረስ ዉጭ በትጥቅ ትግሉ ዘርፍ ያስገኘው ዉጤት እንደሌለ በመረዳት ይመስለኛል፣ ሰላማዊ በሆነ መንገድ፣ ካስፈለገም ከገዢዉ ፓርቲ ጋር በመደራደር ለመንቀሳቀስ ፍላጎት እንዳለው ገልጿል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአማራ ሕዝብ ዐብይ ድክመት - መስፍን አረጋ

እንግዲህ ከላይ የዘረዘርኳቸው አምስት ድርጅቶች ወይም የድርጅት ስብስቦች ሁሉም በሰላማዊ ትግል የሚያምኑ፣ ለኢትዮጵያ አንድነት የቆሙ፣ በሻእቢያ የማይታዘዙ እንደመሆናቸው ፣ በጋራ በሚስማሙበት ነጥቦች ላይ አብረው የሚሰሩበትን መድረክ ለማመቻቸት መሰናክሎች ያጋጥማቸዋል ብዬ አላምንም። በተለይም የዲፕሎማሲና የዉጭ ግንኑነትን በተመለከተ፣  በዳያስፖራ ያለዉን ኢትዮጵያዊ በማስተባበር ዙሪያ፣ የሚስራ አንድ ግብረ ኃይል በቀላሉ ሊያቋቅሙ ይችላሉ። እርግጠኛ ነኝ እንደ ዶር ዲማ ነግዎ፣ አቶ ኦባንግ ሜቶ፣ ዶር ፍስሃ፣ አቶ አክሎግ ልመንህ፣ ዶር አቻሜልህ የመሳሰሉ፣ የበሰሉ፣ ኢትዮጵያዉን የሚወዱ፣ የነዚህ ድርጅቶች አመራር አባላት ብቃቱ፣ ቅንነቱና  ቁርጠኝነቱ አላቸዉ ብዬ አምናለህ።

ይህ ግብረ ኃይል በዉጭ አገር የሚደረገዉን ትግል የሚመራ ይሆናል። ተቃዋሚዎችን ወክሎ ከምእራባዉያን ጋር ይነጋገራል። የተቃዋሚዉ ኃይል ተሰሚነት እንዲኖረው በአንድ ድምጽ ይናገራል። ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎችን ፣ ሰላማዊ ሰልፎችን  ይመራል።  ከገዢው ፓርቲ ጋር መደራደር ካስፈለገ፣ አገር ቤት ካሉ ጋር በመቀናጀት፣ ዳያስፖራዉን ወክሎ ይደራደራል።  እኛም ከተለያዩ ማእዘናት የሚለቀቁ፣ አሰልቺና «እኔም ከማን አንሼ»  መግለጫዎችን ማንበባችን፣  ከተለያዩ ማእዘናትም እየተጎተትን  ግራ መጋባታችን ይቀራል።

ይህ ግብረ ኃይል፣ አገር ቤት የሚደረገዉን ትግል የሚመራ አይሆንም። ነገር ግን አገር ቤት የሚደረገዉን ትግል የሚያግዝ ይሆናል። በኢትዮጵያ የመንግስት ለዉጥ የሚመጣዉ አገር ቤት ያለዉን ሕዝብ ተደራጅቶች ሲንቀሳቀስ ብቻ ነዉ።

በፊታችን ጁላይ «የሽግግር ምንግስት ምክር ቤት»  የተሰኘው ድርጅት ሁሉንም የሚያሰባስብ ኮንፍራስ ጠርቷል። ይሄን አጋጣሚ መጠቀሙ ጥሩ ይመስለኛል። ይሄን በተመለከተ  ወደፊት በስፋት የምመለስበት ይሆናል።

 

እስከዚያዉ ሁላችንም ቸር ይግጠመን !

 

4 Comments

  1. The peacfull struggle is one form of struggle I do not see any body who said it is a problem but it is not enough . What is the problem in armed strugglle from the side of weyane.According to me the armed struggie helps to strengthen the peacful struggle.let them struggle from where ever place they want as far as they have followers .When the peacfull struggle suppressed by weyane ;the armed struggle moves , When armed struggle weakened the peacfull struggle moves. They are interelted .The main point for coming togther is not how to struggle it is in the ultimate goal.many unity founded in the last 40 years but they did not go any where. Unity needs clear aim. do you know that weyane also do not want the armed struggle? that is why is weyane is crying over ginbit 7 as shebertegna daily. According to me for coming togther is to agree only on two points .one is to accept the existence of ethiopia and the second is the gov must be formed by free election i.e after weyane Whether there is many parties and movement in number the difference in ideas can be dicided by free election of the ethiopian people .let us belief on people dision.So my friend the armed struggle is not the problem.let the parties dicide in which form struggle helps to weaken the weyane .let all aim in dismantling weyane not the oppostion forces .assume oppostion forces as they are our parteners.

  2. Hope all is well with you Ato Samuel.

    I have read your article with interest. I find it interesting because it reflects the same attitude we are familiar with. Whenever positive emotions and energies get high we see false prophetess coming with negative energies and emotions to appease them. So far they had been successful during the woyane/shabia invasion against Ethiopians, and in the year of 2005 when the so-called election was rigged. Time and time again woyane used its agents in so called opposition parties to distract the entire movements and managed to marginalize genuine political parties which is why they have been so far successful and continued to remain in power. The time has come Ato Samuel to get rid off false prophetess and move on. Peaceful means of struggle, respecting the current laws and orders of woyane are the things of the past. And you said Hule-Geb Tiggil is backward….. Something is fishy here, sounds like the same mundane affairs from the same false prophetess with negative energies and emotions we are familiar with.

    Back off! Enough is enough!

    Gudu Kassa

  3. It is the usual woyane proposition to side line die hard Ethiopians and Political groups . Mr Amanuel spitting same old divisive points, of woyane’s kind, between all opposition by identifying one from the other by the form of struggle each group pursue .Now Mr Amanuel mission is just to sneak in the opposition camp and foment confusion so as to enable buy more time for woyane to reassert power which is now on the verge of dismantling..I think what is important is to work hard in creating an enviorment where both armed and peaceful oppositions support each other and conduct their struggle meticulously
    with understanding .Because both are meant to fight to end the woyane regime and form Democratic Ethiopia through fair and free election. In my view the woyane has to come under pressure from any direction .so we have to put up all forms of struggle that is what we call- multi dimensional struggle. Thus i do not see any reason why Mr Zelealem want to rule out the armed struggle since the struggle is the people’ s struggle . Go and see for your self how the peasants in Gonder and Gojjam fighting the woyane thugs resolutely on their own land and turf. This has to be encouraged by any Ethiopian and of course not hailed by die hard woyanes like Zelalem. Alluta continua

Comments are closed.

Share