April 24, 2013
4 mins read

በኢትዮጵያ ፓርላማ ብቸኛው ተቃዋሚ የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ፤ ወደ ሚኒሶታ በመምጣት ቅዳሜ ኤፕሪል 27፣ 2013 ዓ.ም ሕዝባዊ ስብሰባ ይደረጋል

girma filyer Minnesota 1

(ዘ-ሐበሻ) የአንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ የሚኒሶታ የድጋፍ ሰጪ ኮሚቴ ለዘ-ሐበሻ በላከው መግለጫ “በኢትዮጵያ ፓርላማ ብቸኛው ተቃዋሚ የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ፤ ወደ ሚኒሶታ በመምጣት ቅዳሜ ኤፕሪል 27፣ 2013 ዓ.ም ሕዝባዊ ስብሰባ እንደሚያደርጉ” ገለጸ።

የድጋፍ ሰጪ ኮሚቴው ለዘ-ሐበሻ እንደገለጸው “በአሁኑ ወቅት በሃገራችን ያለውን አጠቃላይ የፖለቲካ  የኢኮኖሚና የማህበራዊ ጉዳይ ችግሮችን አስመልክቶ በውጭ ለምንገኝ ኢትዮጵያውያን ሰፊ ማብራሪያ ለመስጠትና በሃገራችን ጉዳይም ከኛ ጋር ለመወያየት፤ እንዲሁም የፍኖተ ነጻነት ጋዜጣን መልሶ ህይወት ለመስጠት የአንድነት ፓርቲ ም/ሊቀ መንበርና በፓርላማው ብቸኛው የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅት አንደበት የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ  ወደ ከተማችን ስለሚመጡ የሚኒሶታ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያን እና ኢትዮጵያን ወዳጆች በነቂስ በመውጣት ድጋፋቸውን እንዲሰጡን እንጠይቃለን” ብሏል።

በተለይ በአሁኑ ወቅት የአማርኛ ተናጋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያን ዜጎች ከሚኖሩበት ቦታ ተፈናቅለው በችግር ላይ እንዲወድቁ መደረጉ ብዙዎችን ባስቆጣበት ወቅት በሚደረገው በዚህ የሚኒሶታ ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ ሕዝቡ በመገኘት አቶ ግርማ የአማርኛ ተናጋሪዎችን ድምጽ በፓርላማው እንዲያሰሙ እንዲጠይቅና እንዲያሳስብ አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ለዘ-ሐበሻ ተናግረዋል። “የኢትዮጵያ መንግስት የአማሮቹን መፈናቀል፣ በጋምቤላ እየደረሰ ያለውን ጭፍጨፋ፣ የአፋር ክልል ውስጥ የገባውን ረሃብ፣ በኦሮሚያ ክልል ያሉ እስካሁን ያልተፈቱና እየቀጠሉ ያሉ ችግሮችን፣ በሚዲያዎቹ ጭምር ባልዘገበበትና ምንም ምላሽ ባልሰጠበት ሁኔታ አቶ ግርማ ወደ ሃገር ቤት ሲመለሱ እዚህ ያለውን ድምጽ ፓርላማ ላይ ገብተው እንዲያሰሙ ለመጠይቅ ይህ አጋጣሚ መልካም ነው” የሚሉት አስተያየት ሰጪዎቹ “በሚኒሶታ የምንገኝ ኢትዮጵያውያንም በዚህ ሰብሰባ አጋጣሚ እየተፈናቀሉና እየተቸገሩ ላሉት ወገኖች ድጋፋችንን የምንሰጥበትን መንገድ እናመቻቻለን” ብለዋል።

አቶ ግርማ ሰይፉ በሰሜን አሜሪካ የተለያዩ ከተሞች እየተዘዋወሩ ከኢትዮጵያውያን ጋር እየተወያዩ ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ ከሚመለሱበት 2 ቀናት አስቀድሞ ይህን ስብሰባ በሚኒሶታ እንደሚያደርጉ ታውቋል። አቶ ግርማ ኤፕሪል 27 የሚያደርጉት ሕዝባዊ ስብሰባ በሚኒሶታ በሰሜን አሜሪካ ከሚገኙት ትላልቅ ወተር ፓርኮች መካከል አንዱ በሆነው Water Park of America (Radisson Hotel by Mall of America – Bloomington) ሲሆን አድራሻውም፡ 1700 American Blvd E Bloomington, MN 55425 እንደሆነ የሚኒሶታ የአንድነት ፓርቲ የድጋፍ ሰጪ ገልጿል። ለበለጠ መረጃም 612-986-0557 መደወል ይቻላል።

አቶ ግርማ ሰይፉ በሚኒሶታ የሚያደርጉት ስብሰባ ፍላየር ደርሶናል፡ የሚከተለው ነው።

3 Comments

  1. To my Oromo friends in Minnesta,

    I thought that this man would be an impartial representative and would talk to the many issues facing Ethiopians at home. But he turned out to be a mouth piece of Woyane government in condemnation of the situation in Ogaden on the Ogaden national movement as well as the incarceration of Oromos as a work of other Oromos. We were dumb founded that this guy does not have any clue or is here to serve the TPLF. He may condemn the Amhara displacement, because that may be what his core belief is. We just want you to know who he is,

  2. why do not you go and fight for oromo instead sitting abroad and shiting on your mouth. you and your friends are the main cause for the suffer of the oromo. you let TPLF enter to the country and left your people fled to abroad. go fight for your people like this guy. there is no such worry by eating your hamburger and writing trash.

  3. Lelisa,

    Where did you steal this name from?.It does not belong to a person of your caliber. Names are some times exposes of what parents think of their child. You are a baffoon who does not understand the internal politics of Ethiopia. This guy is advancing the same propaganda against Oromos that the TPLF is advancing. He is no different. The TPLF put him in the parliament knowing that he will not have any influence but give them a cover as an “opposition” representatitive. As to fighting for Oromos, you have no clue of what is going on. Shut up you stupid.

Comments are closed.

Previous Story

በቤንች ማጂ በተነሳ ግጭት ሶስት ተማሪዎች ቆሰሉ

Asrat Tassie
Next Story

“በሀገሪቱ የተደረገው ምርጫ የቧልትና የቀልድ ምርጫ መሆኑን ለህዝብ አሳውቀናል”

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop