በለው! ቄንጠኛ ዳንስ በዕንባ ሲደንስ

ሥርጉተ ሥላሴ 13.03.201 (ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ)

ምን አለባቸው አልሞተባቸው፤ ጥቁር አለበሱ፤ የተራበ ወግን የላቸው፤ የታሰረ ሥጋ የላቸው፤ ባለጊዜ እንዲህ በቄንጥ ዳንሱን ያስነኩት፤ ይጨፍሩ! በጣም አምሮባቸዋል! ተዋጥቶላቸዋልም። ሂዶላቸዋልም። ሚሊዮኖች ጉርሻ ፍላጋ ለትራፊ በረድፍ ተሰልፈው ከጠኔ ጋር ተፋጠዋል። ሚሊዮኖች ከቦታ ቦታ ተራ ዜጋ ናችሁ ተብለው ይፈናቀላሉ። ሺዎች „ኢትዮጵያዊ“ እተባሉ በዬአረብ ሀገሩ እዬተነጠሉ ይታረዳሉ፤ ይደፈራሉ፤ ወንዶችም ይሰለባሉ – ይደፈራሉም፤ በፍል ይቀቀላሉ፤ በፎቅ ይፈጠፈጣሉ። በገጀሞ ይከተከታሉ —- ይታረሳሉ፤ ቄንጠኛው ደግሞ ዳንሱን እንዲህ ያስነኩታል ….

አዎን! በሺህ የሚቀጠሩ ዜጎቻችን ዜግነታቸው የትኛው ሊሆን እንደሚችልም መላ አጥተው ዛሬ ይታመሳሉ። የሱዳን ወይንስ የኢትዮጵያ? የሱዳን መንግሥትና የወያኔ የሽፍታ አስተዳደር የሚስጢሩ ድርድር „ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ ሆኗል።“ ቀንደኛው ሄሮድስ መለስ አፈር ሊያጫውቱ ቢሄዱሙም ጨፋሪው አቶ ሃይለማርያም ደግሞ በሙት መንፈስ ፈረስ እየጋለቡ ታሪክ ይቅር የማይለው አርበኝነትን፤ ታሪክን ማንነትን የዳጠ፤ የጠቀጠቀ ተግባር ፈጸሙ፤ ይንንም ሐሤት አድርገው የፍንጥሩን የልባቸውን ሞልተው የለ ምን ሲገዳቸው፤ እንዲህ ፍለቅልቅ ብለው ይደልቃሉ። በችርስ ይዘንጣሉ። ሳቅ በእናት ኢትዮጵያ ምድር ከገጠር እስከ ከተማ በፈለሰበት ዘመን ከሳቸው ቤት የበቀል ፈገግታ በገፍ እንዲህ ይመረታል – ወይ ነዶ! አሁን ዳንስስስስስ! ህም!

ሚሊዮኖች አስፓልትን ተጠልለው ነገን በሞት ይጠባበቃሉ። የኑሮ ዋስትና፤ የጤና ዋስትን፤ የመማር ዋስትና የላቸውም። የዕምነት አዛውንቶች ካለ ባህላቸውና ትውፊታቸው ስደትን የሙጡኝ ብለው እንደከሰሉ ያልፋሉ። ሀገርም ያሉት የጸሎት ቤታቸው በስጋት ተወጥሮ ከሞቱት በላይ ካሉት በታች ሆነው ተሳቀው ይኖራሉ። ዳንሰኛውም ደግሞ ዳንኪራቸውን እንዲህ መሬት አይበቃኝ ብለው መድረኩን ቀውጢ አድርገው ያስነኩታል …. ፍርሰት —

ተጨማሪ ያንብቡ:  ተረግመሻል ይሆን????!!

ለእለት ጥም ጠብታ ማርኪያ የሚማስኑ ዕልፎች ናቸው። እንደተቆለፈባቸው ጧሪና ጠያቂ አጥተው ትውልዱን ረግመው የሚሰናበቱንም እጅግ በርካታ ናቸው። ቄንጠኛው ዳንሰኛ አቶ ሀይለማርያም ደግሞ ሞቅ ብሏቸው፤ ጥጋቡም አላስችል ብሏቸው እንዲህ ይሉታል …. ማላጋጥ … ምልገትም —-

ጠቀራ የለበሱ ቀናት ረሃብን እያወጁ፤ ስጋትን ነጋሪት እዬጎሰሙ፤ በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ጎጆ እንደ ጉድ ይተማሉ። ቅብጠት ያመራቸውና ያልወጣላቸውም ጠቅላይ ሚኒስተር ሃይለማርያም ደሳለኝ ደግሞ ክርስትናውን ባፍ ጢሙ ብለው ይደልቁታል። ሁሉም አይቅርብኝ በማለት ከተቃራኒ ፆታ ጋርም የዐይን ፍሰቱንም ሆነ የእግር ዳንኪራውም እንዲሁም የመንፈስ ኮማውም …. በአንድነት በመደዴ ያስኬዱታል —- እርግማን!

አሁን ያን የሳውዲ ሰቆቃ ያዬ ፍጡር ዳንስ? ፈንጠዝያ?! ውቂ ደብልቂ?! እፍረት ነው። እውነት ለከፈን፤ ለመጠለያ፤ ለጉሮሮ ያልበቃች በብድር የተነከረች ሀገር እዬመሩ እንዲህ ሃላፊነት የጎደለው የአደባባይ ጥቁር ትዕይንት ማሳዬት እጅግ አንገት ያስደፋል ህሊና ላለው ሰው። „ባልወለድ“ ማለት የነበረበችው እርሳቸው ነበሩ ግን … በዬትኛው ህሊና?

ለነገሩ ምን አለባቸው እሳቸው አልጎደለባቸው። ፈሰስ ብለው ይኖራሉ። እልፎች ድምጻቸው ታፍኖ መተንፈስ ሲጀምሩ እዬተለቀሙ ለእግር ብረት ይዳረጋሉ። ልጆች ካለወላጅ፤ ጎጆም ካለ ጉልቻ፤ ትውልድም በነጠፈ ተስፋ 23ዓመት እንደዋዛ … ወገን ደም እንባ እያለቀሰ ታፍኖ፤ ተከዝኖ የሞት ቀናትን ይጠብቃል። ናፍቆት እስክንድርና መሰሎቹ ህጻናት ደግሞ ወላጆቻቸውን ተነጥቀው በሰው ሀገር ናፍቆታቸውን ሰንቀው ባልበሉት እዳ ይታሻሉ። ክልትምትም ይላሉ። አቶ ሃይለማርያም ደግሞ ከመላ ቤተሰባቸው ጋር የልጆቻቸውን ፍቅር ጠዋት ማታ እዬኮመኮሙ ጥጋቡ አላስችል ብሏቸው እንዲህ በመከራ ላይ፤ በግፍ ላይ ይጨፍራሉ ትዝብት ነው ….

ተጨማሪ ያንብቡ:  እውን ውሳኔው ከዘላቂ የነፃነት፣ የፍትህና የሰላም አርበኝነት የመነጨ ነው? - ጠገናው ጎሹ

ክውና — እረኛ ያጣ ህዝብ፤ ሙሴ የሌለው ትውልድ፤ ባላቤት የሌላት ኢትዮጵያ በፈላ እንባ እስከ መቼ ይሆን መቀቀሉን የሚቀጥሉት? ፈጠሪ አምላክስ መቼ ነው ፍርዱን አደላድሎ በቃችሁን የሚያውጅው!?! ….. ለግፍኞች፤ በእንባ ጨፋሪዎችስ ላይ ቅጣቱን አከታትሎ መቼ ነው የዶግ አመድ አድርጎ ብን የሚያደርጋቸው …. ? መቼስ „ተስፋ“ አያልቅ ደግሞ እንደ አመላችን „ተስፋ“ የሚባለውን እንጠብቅ ወይንስ ከእሱ ከራሱ „ተስፋ“ ከሚባለው ልብ አንጠልጣይ ጉድ ጋር ጦርነት እንግጠም ይሆን?

በሉ የኔዎቹ በዚህች ቆራጣ መጣጥፍ ትንፋሽ — የውስጤን ቁስለት በማሳዬት ተብተከትኩ። ለነበርን መልካም ጊዜ አመሰገንኩ – በፍቅር። ደህና ሰንብቱ።

እልፍ ነን። እልፍነታችን በተግባር እልፍ እናድርገው።
እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

5 Comments

  1. wey wey sirgut,

    inde you live in lexury on swizerland while you know all this happening to ethiopian. tuf tuf if i were you i would have gone to out to fight the gov instead of just do demonstration ones in a month to meet up boys and talk 24/7 on paltalk.

    emabressed by you girl.

  2. Minew endi dedeb set honsh anchi photosh lay eyalekesh new ende yaleshiw?mechem englizegna aygebashim beye new bamarigna yemetsefelesh.minew kenash be pm hd. Yegid amara mehon alebet anchi endetamesegngiw? Asafari set nesh melketfu!!! Ayn yaweta fugera atfogri.

    • What makes you stupid rather? She has the right to comment what she felt. You are no body to say someone ”dedeb’ because you don’t have a religious moral and discipline as per your displayed comment. Grow up in all aspects of your life.

Comments are closed.

Share