በዳላስ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በሳዑዲ አረቢያ ለተጎዱ ወገኖቻቸው መርጃ ግማሽ ሚሊዮን ብር ሰጡ

አቶ ብርሃን መኮንን ከዳላስ ፎርት ወርዝ አካባቢ የተዋጣውን ገንዘብ ለዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት በዋሽንግተን ዲሲ ተገኝተው ሲያስረክቡ

(ዘ-ሐበሻ) በቴክሳስ ግዛት በዳላስና ፎርት ወርዝ አካባቢ ከተማ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በሳዑዲ አረቢያ ባለፈው ኖቬምበር 2013 ዓ.ም ጉዳት ለደረሰባቸውና ወደ ሃገራቸው ለተመለሱ ኢትዮጵያውያን ወንድም እና እህቶቻቸው ማቋቋሚያ የሚውል 31 ሺህ ዶላር ወይም ግማሽ ሚሊዮን ብር አዋጥተው ሰጡ።

ኢትዮጵያውያን በሳዑዲ አረቢያ ጥቃት ከደረሰባቸው በኋላ በዳላስና ፎርት ወርዝ አካባቢ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ቁጣ ሰላማዊ ሰልፍና የሻማ ማብራት ምሽት በማድረግ ቁጣቸውን እና ሃዘናቸውን መግለጻቸው በወቅቱ በዘ-ሐበሻ ድረ ገጽ የተዘገበ ሲሆን የአካባቢው ነዋሪዎች ከማዘን እና ከመቆጣት ባሻገር ገንዘባቸውን በማዋጣት ወደ ሃገር ቤት ለተመለሱት ኢትዮጵያውያን ማቋቋሚያ እንዲውል በሚል ይህን 31 ሺህ ዶላር አሰባስበው ለዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት IOM የአሜሪካ ቅርንጫፍ ሰጥተዋል።

የማህበሩ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ብርሃን መኮንን በዳላስ ፎርት ወርዝ የተሰባሰበውን 31 ሺህ ዶላር (በዛሬው የአዲስ አበባ የዶላር ምንዛሪ ዋጋ 595 ሺህ 150 ብር) ወደ ዋሽንግተን ዲሲ በማምራት ለዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት በቼክ ካስረከቡ በኋላ እርዳታው እንደሚቀጥል ገልጸዋል። በሕዝቡ ቃል ተገብቶ ያልተሰበሰበው ገንዘብም በቀጣይ እንደተሰበሰበ ለIOM እንደሚሰጥ ሊቀመንበሩ ጨምረው ገልጸዋል።

የዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት ከሳዑዲ የተመለሱ ኢትዮጵያውያንን ለማቋቋም በአዲስ አበባ የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን የገለጸ ሲሆን ከ160 ሺህ በላይ የሳዑዲ አረቢያ ተመላሽ ኢትዮጵያውያንን ለማቋቋም ከፍተኛ ሥራ እንደሚጠብቅ፤ ኢትዮጵያውያን በዓለም አቀፍ ወገኖቻቸውን ለመርዳት የሚያደርጉትን ጥረት እንደሚያደንቅ ድርጅቱ በተደጋጋሚ መግለጹ ይታወሳል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የጎንደር ሕብረት ለጎንደር ተፈናቃዮች አንድ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር መመደቡን አስታወቀ

2 Comments

  1. We the Ethiopians in Dallas, TX had made the right way supporting our brother in sister from Saudi arabia to Ethiopia by directly contributing to IOM without getting involve the so called Global effort (G7 ESAT). Tamage (lemage) beyene was tried so hard by calling day and night to divert the fund to his G7 cronnies account. But the Ethiopians in Dallas let him know that we are not intersted to hand over the fund to Global effort (G7’s Esat). The few G7’s supporter got the message there is no more hard earned money will go to their master Dr. Berhanu and Tamage! They had rubbed enough money $ in this city on the name of ESAT or G7!!

Comments are closed.

Share