Hiber Radio: ግብጽ ኢትዮጵያ በአባይ ጉዳይ ጀርባዋን ሰጠችኝ ስትል ስጋቷን ገለጸች

July 23, 2013

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ
Hiber Radio: ግብጽ ኢትዮጵያ በአባይ ጉዳይ ጀርባዋን ሰጠችኝ ስትል ስጋቷን ገለጸች 1
የህብር ሬዲዮ ዕሁድ ሐምሌ 14 ቀን 2005 ፕሮግራም

<< ...ጆርጅ ዚመርማን ተኩሶ በገደለው የትራይቮን ማርቲን ጉዳይ በተሰጠው ጠቅላላ ውሳኔ ቅሬታ አለኝ …ይሄ ነገር የተገላቢጦሽ ቢሆንና ጥቁር ጎልማሳ መሳሪያ ያልያዘን ምንም ጥፋት ያላጠፋን የ17 ዓመት ነጭ ወጣት ገሎ አይ እኔ ፈርቼ ነው የገደልኩት ቢል ውጤቱ እንዲህ ይሆን ነበር የሚል ጥያቄ ያስነሳል? እኔ በበኩሌ አይመስለኝም። በሕግ አንጻር የተሰጠውን ፍርድ ስንመለከተው ግን ... >>

በአሜሪካን አገር ጠበቃ የሆኑት አቶ ሳህሉ ሚካኤል የ17 ዓመቱን ወጣት

ትራይቮን ማርቲን በጥይት የገደለው ራሱን ለመከላከል ተብሎ ነጻ መባሉን አስመልክቶ ለህብር ከሰጡት ቃለ መጠይቅ የተወሰደ

<< ...እስርና ማስፈራራት የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት ሕዝባዊ ዘመቻ እንደማያስተጓጉለው ደሴና ጎንደር ላይ የሆነው ምስክር ነው።...ሰሞኑን ከሰልፎቹ በሁዋላ የአሜሪካና የአውሮፓ ህብረትና የተለያዩ አገራት ዲፕሎማቶች በአንድነት ጽ/ቤት ከአመራሩ ጋር ተወያይተዋል። የሰሞኑን በህብረቱ በኩል የወጣውን ሪፖርት በአወንታ ነው የምናየው። በእኛ በኩል በዚህ ሁሉ አስቸጋሪ ሁኔታ ትግሉን ወደፊት ለመቀጠል ወስነናል። የፋይናንስ አቅም ችግር ግን አለብን...>>

የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት አስተባባሪ ግብረ ሀይል ም/ል ቃል አቀባይ አቶ ሀብታሙ አያሌው ከሰጡን ወቅታዊ ቃለ ምልልስ (ሙሉውን ያዳምጡ)

ፕ/ት ኦባማ ያለ ወንጀሉ በጥይት የተገደለውን የ17 ዓመቱን ትራይቮን አስመልክቶ በይፋ ተናገሩ <<...ከ35 ዓመት በፊት ትራይቮን ማርቲን እንደኔ ይሆን ነበር ...>> (ከመቶ በላይ የአሜሪካ ከተሞች የተደረገውን የገዳይን ነጻ መባል የተቃውሞ ንቅናቄ በዘገባችን ቃኝተነዋል)

የአውሮፓ ሕብረት የፓርላማ አባላት እና የሰብዓዊ ጥበቃ ኮሚቴ አባላት በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ ተጉዘው በአገዛዙ ሰብዓዊ መብት ላይ ስለሚያደርሰው በደል ጠቅሰው የሰላ ሂስ ሰንዝረዋል ።ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን ጨምሮ ሁሉም የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ ጠይቀዋል

(ሙሉ ዝርዝሩን ከወቅታዊው ዘገባ ያዳምጡ)

ሌሎችም ቃለ መጠይቆች አሉን

ዜናዎቻችን
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ከእስር ቤት ለፕ/ት ኦባማ የሚደርስ ግልጽ ደብዳቤ ጻፈ

አሜሪካ ሰብዓዊ ዕርዳታን የማይነካ የኢኮኖሚ ማዕቀብና በባለ ስልጣናቱ ላይ የበረራ ማዕቀብ እንድትጥል ጠይቋል

መድረክ በመቀሌ የተሳካ ሕዝባዊ ስብሰባ ማካሄዱ ተገለጸ

በአገር ውስጥ በበረራ ላይ የነበረ አውሮፕላን በድንገት አረፈ

ግብጽ ኢትዮጵያ በአባይ ጉዳይ ጀርባዋን ሰጠችኝ ስትል ስጋቷን ገለጸች

አሜሪካ በሟች ጥቁር ወጣት ትራይቮን ማርቲን ገዳይ የፍርድ ቤት ውሳኔ ሳቢያ ከመቶ በላይ ከተሞች ተቃውሞ ተደረገ

ቢዮንሴና ጄዚም ተሳትፈዋል

ፍሪያስ ኩባንያ ያባረራቸውን የስራ ማቆም አድማ ተሳታፊዎችን ወደ ስራ ለመመለስ በተመለከተ ከሽማግሌዎች ጋር ለመወያየት ጥሪ አቀረበ

ሌሎችም ዜናዎች አሉን

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop