ጅቡን ከነሕይወቱ አጥምዶ በአህያ ጋሪ በመጫን በመቂ ከተማ ሲዘዋወር የነበረው ግለሰብ ታሰረ

June 20, 2013

(ዘ-ሐበሻ) “ወይ ጉድ!” ሊያስብል የሚችል ዜና እንደሆነ ይሰማናል። ይህን ዜና ከነምስሉ የበተነው በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ሥር የሚታተመው ‘ፖሊስና እርምጃው” የተሰኘው ጋዜጣ ነው።

“ይህ የምትመለከቱት ፎቶ ሰሞኑን በምሥራቅ ሸዋ ዞን ቱግጃ ወረዳ መቂ ከተማ ውስጥ የተከሰተ ሲሆን በምስሉ ላይ የሚታየው ተከሳሽ ጅቡን አጥምዶ ከነሕይወቱ በመያዝ በአህያ ጋር ጭኖ መቂ ከተማ ውስጥ ከምሽቱ 2 ሰዓት ላይ በመዘዋወር ላይ ሳለ በህብረተሰቡ ጥቆማ መሠረት በቁጥጥር ስር ውሏል። ተከሳሹ በምን ምክንያት እና ለምን ጅቡን እንደያዘው ለፖሊስ ያልገለጸ ሲሆን እንስሳትን በማንገላታት ክስ ተመስርቶበት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ይገኛል” ይላል ሰሞኑን ታትሞ የወጣው የፖሊስ እና እርምጃው ጋዜጣ ዘገባ።
“ሰው የሚያስብ እንስሳ” ነው ሲሉ ተመራማሪዎች ይገልጻሉ። የ እንስሳት መብት አይከበር እያልን ሳይሆን፤ የሚያስበውን ሰው በአሸባሪነት በመክሰስ፣ እንደፈለገው እንዳይንቀሳቀስ በማገድ የሚታወቀው መንግስት ደርሶ ለእንስሳት ተቆርቋሪ መስሎ በሚዲያ መቅረቡ የሚያስገርም ነው። ጅቡን አንገላታ የተባለው “እንስሳትን የማንገላታት አንቀጽ” ተጠቅሶበት ታሰረ፤ እነ እስክንድር ነጋን ጨምሮ ነፃ አሳቢ የፖለቲካና የሃይማኖት መሪዎችን እስር ቤት እያንገላቱ ያሉትስ? ነው ወይስ “መንግስታችን” የቆመው ለማያስቡ እንስሶች ብቻ ነው?

ዘ-ሐበሻ አስተያየትዎን ጨምሩበት ስትል ትጋብዛለች።

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop