የኢሕአዴግ መንግስት የማኅበረ ቅዱሳንን አመራርና አባላት በአክራሪነት የሚከስ ዶክመንተሪ ሊያዘጋጅ ነው ተባለ

ዶክመንተሪው የ2007 ሀገራዊ ምርጫ ቅድመ ዝግጅት አካል እንደኾነ ተጠቁሟል

‹‹ማስረጃ አቅርቡና እንነጋገርበት›› ለሚለው የማኅበሩ ጥያቄ ምላሽ አልተሰጠም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሲኖዶሱን ይኹንታ አግኝቶ በመላው አገሪቱ የሚንቀሳቀሰውን የማኅበረ ቅዱሳንን አመራርና አባላት በአክራሪነት የሚከስ ነው የተባለ ዶክመንተሪ ፊልም ለማዘጋጀት መታቀዱ ተጠቆመ፡፡

የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ አንዳንድ ሓላፊዎች አቀብለውታል በተባለ መረጃ እንደሚታገዝና በመንግሥት አካል እንደሚሰናዳ የተገለጸው የዶክመንተሪ ዝግጅቱ በማኅበሩ ኻያ አመራሮች እና አባላት ላይ እንዳነጣጠረ ተገልጧል፡፡ መንግሥት በምርጫ – 97 ውጤትና በተከታይ ኹኔታዎቹ ላይ ባካሔደው ግምገማ፣ የማኅበረ ቅዱሳን አባላት ናቸው የሚባሉ ግለሰቦች በተለይ በገጠር ቀበሌዎች ለተቃዋሚዎች ተሰሚነት ማግኘት በምክንያትነት መጥቀሱ በዜና ጥቆማው የተመለከተ ሲኾን ‹‹የአክራሪነትና የጽንፈኛ ፖሊቲከኞች ምሽግ ነው›› በሚል የሚያቀርበው ክሥም ከዚኹ የሚነሣና ለመጪው የ2007 ሀገራዊ ምርጫ የሚደረግ ቅድመ ዝግጅትም አካል እንደኾነ ተነግሯል፡፡

በቅድመ ዝግጅቱ የሚወሰዱ ርምጃዎች የማኅበሩን አቅሞችና እንቅስቃሴዎች በመቆጣጠር በተለይም የማኅበሩ መሠረቶች ናቸው የሚባሉ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ግቢ ጉባኤያትን ‹‹በሴኩላሪዝም መርሖዎች የመግባቢያ ሰነድ›› ጠርንፎ ‹የአገልግሎት ቅኝቱን የማስተካከል› ዓላማ እንዳላቸው የገለጸው የዜና ምንጩ፣ ይህም ካልተሳካ በተከታታይ አስተዳደራዊ ርምጃዎችና የተቃውሞ ቅስቀሳዎች ማኅበሩን በማወከብ ተቋሙን ለዘለቄታው የማፍረስ ውጤት ሊኖረውም እንደሚችል አመልክቷል፡፡’

ከአዲስ አበባ ሀ/ስብከት አብያተ ክርስቲያናት የተጠሩ ናቸው የተባሉ አስተዳዳሪዎችና ሠራተኞች የሚሳተፉበት እንደኾነ የተገለጸና ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ በማኅበሩ አገልግሎት ላይ ቁጥጥሩን እንዲያጠብቅ የሚጠይቅ ስብሰባ በዛሬው ዕለት በቤተ ክህነቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ እንደሚካሔድ የተዘገበ ሲኾን ዓላማውም ‹‹በአክራሪዎችና ጽንፈኛ ፖሊቲከኞች ምሽግነት፣ የቤተ ክህነቱን አሠራር ባለማክበርና ከቤተ ክህነቱ በላይ ገዝፎ በመውጣት›› ማኅበሩ የሚከሰስባቸውን ኹኔታዎች በማጠናከር ለታቀዱት ርምጃዎች የሚያመቻች ነው ተብሏል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  በእነ እስክንድር ነጋ መዝገብ ዐቃቤ ሕግ ምስክር ማሰማት ጀመረ

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ላይ በማተኮር የተማረው ትውልድ ሃይማኖቱን የሚወድ፣ ግብረ ገብነት ያለው፣ ሀገሩንና ቤተ ክርስቲያኑን በዕውቀቱ፣ በሞያውና በገንዘቡ የሚያገለግል ብቁ ዜጋ ይኾን ዘንድ በቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ በተሰጠው መተዳደርያ ደንብ መሠረት በመሥራት ላይ እንዳለ የሚገልጹ የማኅበሩ አባላትና ደጋፊዎቹ፣ ማኅበሩ ለቀረቡበት ክሦች የሚመች አደረጃጀት ይኹን ባሕርይ እንደሌለው በመግለጽ ተጠሪ ከኾነለት ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጋራ በአሠራር ሒደት የሚፈጠር ክፍተትን በማጦዝ የሚሰነዘሩ ውንጀላዎች ተቀባይነት እንደሌላቸው ተናግረዋል፡፡ የተጠቀሱት ክሦች ላቀረቡት አካላት ‹‹የሚነገረውና የሚጻፈው እኛን የሚገልጸን ስላልኾነ ማስረጃ አቅርቡና እንነጋገርበት›› የሚል ጥያቄ ቢቀርብላቸውም ለሠለጠነ ውይይት ፍላጎት እንደሌላቸው አባላቱ አስረድተዋል፤ በምትኩ ‹‹ርምጃ እንወስዳለን›› በማለት በተለያዩ መድረኮች ማኅበሩን ማሳጣትና መክሠሥ እንደሚመርጡም ለፋክት መጽሔት አስታውቀዋል፡፡

ታቅዷል የተባለው የዶኩመንተሪ ዝግጅት እውነት ከኾነም ማኅበሩን ብቻ ሳይኾን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የማዳከም አጠቃላይ ዘመቻ አድርገው እንደሚቆጥሩትና በቀላሉ እንደማይመለከቱት አሳስበዋል፡፡

ምንጭ፡ ፋክት መጽሔት ቅጽ ፪ ቁጥር ፴፰፤ መጋቢት ፳፻፮ ዓ.ም.)

7 Comments

  1. “አይጥ ሞት ሲያምራት የድመት አፍንጫ ታሸታለች” አሉ አበው….

  2. This is the Golden opportinity to strength the opposition party. As far as I know there are 3000,000 members of mahber kidusan. I feel weyane is going down.

  3. Mahbere rekusan is the exact name of this haters and racist groups.open your eyes and see the evidence….government need to destroy this under ground groups.

  4. ፓትሪያሪኩ ከቤ/ክ ይልቅ ዘሬ ይበልጣል ብለው ነው ከስራቸው እነ ንቡረዕድ ኤልያስ እነ ሊቀ ካህናት እንደ መልኩ ውስጡም ጥቁር የመሳሰሉትን አካዳሚክ እውቀት የሌላቸውን በዘራቸው መርጠው ከስራቸው አስቀምጠዋል ስለዚህ ስለ ቤ/ክ ማሰብ አይችሉም አብዮታዊ ዲሞክራሲ ብቻ ነው የሚችሉት እኔ ግን ወያኔ ወድቆ ይህ አስቀያሚ ዘር የዘሩ ሰም ስለ ሚቀፈኝ ነው የት እንደሚገባ እ/ር እዲያሰዪኝ ነው ቤ/ክ የሁሉም ነች የኦሮሞው የአማራው የጉራጌው የወላይታው ወዘተ ነች የናንተ ብቻ አይደለችም

  5. Weyane Banda doesn’t care about anything. They are communist – MLLT (Marxist Leninist League Tigray). The main architect is Abay Tsehaye: one to five; building sugar company by Waldba; he betrayed his friends from Seye group; they have been doing it. Actually, they are targeting The Orthodox Church that’s way they want to test one of The Churches Institution. Let them do it; what do you expect from communist. It is very sad they came from north; the birth place of Atsi Yohannes. As one brother indicated, let do our part; by calling our family, relative, and friends to vote for the opposition, ensure they lose. What else can you do, wait and destroy our institution. No matter what, Mahibre Kidusa is teaching Christianity; do they have errors yes and but they are more helping Yekolo Temari and so on.
    Laikun

  6. To all those who is excited by this drama, I am not sure what your position is. Are you saying Mahebre Erkusan is a good group???? Do you know what sort of corrupt organisation it is. This is an organisation that is the little kid of the big Synod but now it is feeling too big for its boot, it is stepping out of line. I say, let them do what they like to each other. This is a distruction from bigger issues. The rest of us just watch the drama unfolding.

Comments are closed.

Share