የኢፌዴሪ መከላከያ ሴቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሜጀር ጀነራል ጥሩዬ አሠፌ ወሎ ግንባር ከሚገኙ ሴት የሠራዊት አባላት ጋር ተወያዩ

መስከረም 20 ቀን 2014

ውይይቱ በግንባሩ ያሉ ሴቶች በተልዕኮ አፈፃፀም ውስጥ ላሳዩአቸው ጥንካሬዎች እውቅናና ክብር መስጠትን አላማው ያደረገ ነው ።

በመድረኩ የሴቶች እኩልነትና የእንችላለን ስሜት ከቃል ባለፈ በተግባር የህይወት መስዋዕትነትን በሚጠይቀው ውትድርና ውስጥ ጭምር በብቃት እየታየ ስለመሆኑ በተሳታፊ ሴት የሰራዊት አባላቱ ተገልጿል ።

አሸባሪውን የህወሀት ሀይል በመደምሰሡ ረገድ ከመጀመሪያው ጀምሮ ሴቶች ከጠላት ጋር የጨበጣ ውጊያ በመግጠምና ቦንብ ሲጨርሡ በድንጋይ ምሽግ በማስለቀቅ ጭምር ጀግንነታቸውን እንዳሳዩም ነው የተነገረው ።

በግንባር የሚገኙ ሴት የሠራዊት አባላት የአውደ ውጊያ ጥንካሬ በአሁኑ ወቅት ለወንድ የሠራዊት አባላቱም ጭምር የተሻለ መነሳሳትን እየፈጠረ እንዳለም በውይይት መድረኩ ተነስቷል ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሴቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሯ ሜጀር ጀነራል ጥሩዬ አሠፌ በበኩላቸው ፣ ጀግንነት ለኢትዮጵያውያን ሴቶች ቀድሞውንም መገለጫቸው እንደሆነ ጠቁመው ፣

እናንተም የሀገራችሁን ፍቅር በመስዋዕትነት ጭምር እየገለፃችሁና ይህንኑ ጀግንነት እያስቀጠላችሁ በመሆኑ ስራችሁ ምንጊዜም በታሪክ ሲነገር የሚኖር ነው ብለዋል ።

ነፃነት ሸዋንግዛው ( ከግዳጅ ቀጣና )

ፎቶ ግራፍ በሀይሉ ስለሺ

ተጨማሪ ያንብቡ:  ለተፈናቃዮች ሀገራቸው የት ነው?

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share