January 19, 2023
10 mins read

ተዋሕዶን ለማወክ የሚፈጸመው የአቢይ አህመድ መንግሥታዊ ሽብር በደል እስከ መቼ?

በተለይ የአደባባይ በዐላቷን ለማወክ የሚሠራው በደል መቼ የተጀመረ ነው?

(ከአሁንገና ዓለማየሁ)

yelencho let lig abiy ahmed

ይህን ጽሑፍ ለመጻፍ ያነሳሳኝ የጥምቀትን በዐል መቃረብ አስታክኮ ሲፈጸም ያስተዋልኩት  የተለመደው ሕዝብን  የማሸበር እና የ ማስጨነቅ ድርጊት ነው።

ብዙ ሰዎች የተዋሕዶ ክርስትናን የማዋከቡን ሂደት አቢይ አህመድ የጀመረው የሚመስላቸው አሉ። እርግጥ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶን ከግራኝና ከኦሮሞ አባ ዱላዎች ወረራ ዘመን  ኋላ ከፋሺስት  ጣልያንም አገዛዝ ወቅት ወዲህ እንደ አቢይ አህመድ ያሳደደ፣ ያዋረደ ዘመን አልነበረም ለማለት ይቻላል። ይሁንና በቅርቡ ዘመናችን ታሪክ የተዋሕዶ እምነትንየማጥቃት   በተለይም የአደባባይ በዓላቷን የማዳከም ተልእኮ ከሶሻሊስቱ የደርግ ሥርዐት ጀምሮ እየተባባሰ የመጣ እንጂ አቢይ አህመድ የጀመረው አይደለም። በደርግ   ዘመን የአደባባይ በዐላት በድምቀት እንዳይከበሩ የተማሪዎችን የፈተና ቀን በዚሁ በጥምቀት በዐል  ማግሥት እንዲሆን በማድረግ፣ በዐሉን የሥራና የስብሰባ እለት በማድረግ እና በሌሎችም ብዙ ብዙ መንገዶች የማወክ ሥራ ተሠርቷል። ይህም ቀላል ጉዳት ሳያደርስ ያለፈ አይደለም።

የተማሩና ደህና ገቢ አላቸው ከሚባሉ የሰፈራችን ቤተሰቦች የማስታውሰው አንድ ቤተስብ ብቻ ነበር በደርግ ዘመን አባት ልጆቻቸውን አዲስ የባህል ልብሶች አልብሰው ልጆቻቸውን ጥምቀት በዐል ሊያከብሩ የሚወስዷቸው። በስተቀር ልጆች በራሳቸው ሄደው ያከብሩ ካልሆነ የተማረና የተሻለ ገቢ አለው ከሚባለው ቤተሰብ መካከል ራሳቸውም በመሳተፍ ልጆቻቸውንም ይዘው በመሄድ ከአካባቢያችን አንድም ትዝ የሚለኝ ቤተሰብ የለም። በዐሉን አክብሮ ከነቤተሰቡ በመታደም የሚያደምቀው አነስተኛ ገቢ ያለው የሕብረተሰብ ክፍል ነበር ለማለት ይቻላል። ይህ ለውጥ ደግሞ እንደኔ ትዝብት የደርግን መንግሥት ወደ ሥልጣን መምጣት ተከትሎ ከነበረው የሽብር ጊዜ በኋላ የተከሰተ ነበር።

ኢህአዴግ ሥልጣን ከተቆጣጠረ በኋላ ፖሊስ ከአደባባይ በዐላት አስቀድሞ በሚያወጣቸው የተጠኑ የማሸበሪያ መግለጫዎች የተነሳም ይሁን ሌላ የተማረ ወይም መካከለኛ ገቢ ያለው የሕብረተሰብ ክፍል በነዚህ በዐላት ላይ እንደማይታደም ታዝቢያለሁ። የራሴን የእድሜ ባልንጀሮች በምሳሌነት ስወስድ አንዳቸውም ልጆቻቸውን ይዘው በከተራ፣ በደመራ፣ ወይም በጥምቀት በዐላት ላይ ሲገኙ አላየሁም። የአዲስ አበባ ተወላጆቹን ማለቴ ነው።  በጉዳዩ በማዘን ካነጋገርኳቸው ከብዙዎቹ የተረዳሁት ከፍተኛ ፍርሃትና ሥጋት እንዳለባቸው ነው።

የራሴን ቤተሰብ በምሳሌ ብወስድ እኔ በውጭ ሀገር ባለሁበት ወቅት አንድ ወንድሜ (የአጎቴ ልጅ) የኔን ልጅ የመስቀልን በዐል ሊያሳያት እሽኮኮ ብሏት በሄደበት በመስቀል አደባባይ ለከተራ ቀን ከፍተኛ የተኩስ እሩምታ በአግአዚ ጦር ተከፍቶባቸው ከቦታው ለመሸሽ ተገድደው ነበር። በወያኔ የሥልጣን ዘመን። በዚሁ ዘመን መጨረሻ አካባቢ የደመራን በዐል ለማክበር የቤተሰብና የጓደኞቼን ልጆች መስቀል አደባባይ ሄጄ ምእመኑ እንደዚህ ዐይነት ቦታ ድርሽ እንዳይል የሚደረገውን ማዋከብና ማስፈራራት በገዛ ዐይኔ ለመታዘብ ችያለሁ።

ይባስ ብሎ አቢይ አህመድ ሥልጣን ላይ ከወጣ በኋላ በዋለው የመጀመሪያው የመስቀል በዐል ደመራ እለት ከልብሳችን እና ካንገታችን የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ካልፈታን ወደ አደባባዩ መሄድ ተከልክለን ነበር። በፌዴራል ፖሊስ። በአጋጣሚ በእለቱ አብረን የነበርነው (በወያኔ አገላለጽ) አንድ ኦሮሞ፣ አንድ አማራና አንድ ትግሬ ነበርን። ሦስታችንም በአልባሳታችን ላይ ያሉትን ወይም በአካላችን የጠመጠምነውን ሰንደቅ ዓላማ እንድንፈታ ስንገደድ እልህና እንባ ቢተናነቀንም ምንም ልናደርግ አልቻልንም።  በዚህም ወቅት ከበዐሉ አስቀድሞ የሚደረገው የተቀነባበረ የፖሊስ መግለጫና የሚዲያ ማስፈራሪያ ከበፊቱም በከፋ መልኩ ቀጥሎ ነበር። ከዚያም ወዲህ በእያንዳንዱ የተዋሕዶ የአደባባይ በዓል ወቅት እንዲህ ዓይነት የተጠና በመግለጫና በሚዲያ የታገዘ መንግሥታዊ ሽብር እስከዛሬ ቀጥሏል። የየካ ሚካኤል ታቦት ማረፊያ ሕዝቡ ላይ በቀጥታ በተደገኑ የፒክአፕ መትረየሶች የታጀበ ነበር።  እርግጥ በዐሉ ሁል ጊዜም ከወትሮውም ድምቅ ብሎ የተከበረ ይመስላል። እውነትም የሕዝቡ ቁጥር እያደገ በመሄዱና ከገጠር ወደ ከተማ ያለውም ፍልሰት በመጨመሩ አከባበሩ እየተሻለ የመጣ ሊመስለን ይችላል።

ይሁን እንጂ እልፍ እአላፍ በዚህ ሽብር ምክንያት በበዐሉ ሳይታደሙ እየቀሩ ልጆቻቸውም የዚህ ትውፊትና መንፈሳዊ በረከት ተሳታፊ ሳይሆኑ፣ በእድሉ ሳይጠቀሙ እየተጎዱ ነው።   በሽብር  መልእክቶቹ ሳይረቱ በየአደባባዩ በድፍረት የወጡት አእላፍ ምእመናን በፍርሃት ተሸብበው እቤት የዋሉትን እልፍ አእላፍ እንዳይሸፍኑብን።  ይህ መንግሥታዊ የሽብር ድርጊት አስጸያፊ የመብት ድፍጠጣና ጭፍለቃ ስለሆነ ሊወገዝና ሊቆም የሚገባው እጅግ የከፋ የጭቆና ተግባር ነው።

ከእምነተ ቤተክርስትያን አኳያ ስንመለከተው የበዐሉ አከባበር በነዚህ በተጠቀሱት ዘመናት መካከል መንፈሳዊ ይዘቱ እየጎላ መምጣቱ እንዲሁም የወጣቱ ተሳትፎም እጅግ እያደገ መምጣቱ እሙን ነው። ይህ ግን ከመንግሥት ተጽእኖ እና ፍላጎት በተቃራኒ በሕዝቡ ውስጥ በተፈጠረ መነቃቃትና በቤተክርስትያንም ማሕበራት በተደረጉ ሥራዎች የተፈጸመ ነው።

ለማጠቃለል፣ በአቢይ አህመድ ጊዜ በአስከፊ ሁኔታ ቢባባስም፣ በተዋሕዶ ላይ በተለይ በአደባባይ በዐላት ዙሪያ የሚፈጸመው መንግሥታዊ ሽብርና ማዋከብ ከእግዜር የለሹ ደርግ ዘመን ጀምሮ እየተባባሰ የመጣ እንጂ አዲስ ክስተት አይደለም።

ስለዚህም ውጊያው ከወገን ጋር ሳይሆን ከክፉ መንፈስ ጋር ነው የሚባለውን ለማመን እንገደዳለን።

መልካም የከተራና የጥምቀት በዐል!

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

ጥር 2 ቀን 2017 ዓ/ም   January 10, 2025  በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡ ቤተ ሰብ፡ ወዳጅ ዘመዶቻችሁን ያጣችሁ: ልጆቻችሁን የቀበራችሁ፡ አካልችሁን ያጣችሁ፡ የተሰነዘረውን ብትር በመከላከል ላይ ያላችሁ፡ያለፈቃዳችሁ በመንግሥት ተጽእኖ ወደመግደልና

በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛ ተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡

January 10, 2025
Go toTop