May 28, 2022
2 mins read

ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ በፌደራል ፖሊስ አባላት ተያዘች

Meaza Mohamed
Meaza Mohamed“ሮሃ ሚዲያ” የተሰኘው የዩቲዩብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና ባለቤት የሆነችው መዓዛ መሐመድ ዛሬ ጠዋት በፖሊስ ተይዛ መወሰዷን የስራ ባልደረባዋ እና ጓደኛዋ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገረች። የጋዜጠኛዋ እስር በኢትዮጵያ ከሰሞኑ በጸጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር የዋሉ ጋዜጠኞች እና የመገናኛ ብዙኃን ሰራተኞችን ቁጥር 19 አድርሶታል።
ጋዜጠኛ መዓዛ የፌደራል ፖሊስ የደንብ ልብስ በለበሱ ሁለት ፖሊሶች እና የሲቪል ልብስ ባደረጉ ሶስት የጸጥታ ኃይሎች የተያዘችው በአዲስ አበባ ሰሚት ኮንዶሚኒየም ከሚገኝ የእርሷ መኖሪያ ቤት እንደሆነ የ“ሮሃ ሚዲያ” ጋዜጠኛ ምስራቅ ተፈራ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጻለች። የጸጥታ ኃይሎቹ መዓዛን ለ“ጥያቄ እንፈልጋታለን” በሚል ምክንያት ቢይዟትም ወዴት እንደሚወስዷት ለመናገር ፈቃደኛ እንዳልነበሩ ጋዜጠኛዋ አስረድታለች።
መዓዛ እርሷ ቤት ያደረችው ያላጠናቀቁትን ስራ ለመጨረስ እንደነበር የምትናገረው ምስራቅ፤ ጠዋት ሶስት ሰዓት ገደማ የመኖሪያ ቤቷ ሲንኳኳ በከፈተችበት ወቅት ሁለት ፖሊሶችን እና ሌሎቹን የጸጥታ ኃይሎች በበር ላይ ማግኘቷን አስታውቃለች። የፍርድ ቤት መጥሪያ “አልያዙም ነበር” የተባሉት የጸጥታ ኃይሎቹ፤ የመዓዛን አድራሻ እና መታወቂያዋ ላይ ያለውን መረጃዎች ከመዘገቡ በኋላ በያዙት ካሜራ ፎቶ እንዳነሷት ጋዜጠኛ ምስራቅ አብራርታለች።
(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

1 Comment

  1. ክሚገባሽ በላይ ላገርሽ ለህዝብሽ ሰርተሻል ይህንን ታላቅ ስራሽን የሚያደበዝዝ ምንም ነገር ሊመጣ አይችልም አንች ለሌሎች እንደታገልሽ ላንች ያልታሰርነው እንጮሃለን ለሙያሽ ኤቲክሱ በሚፈቅደው ልክ ተዋድቀሻል ለሆድ አደሮች ምሳሌ ሁነሻል ምናልባት ስዩም ተሾመም የሚቆረጥለት ቀለብ ከቆመ እንዳንች ይሞክረው ይሆናል አይሞክረውም መቼም።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Kidnaper Abiy
Previous Story

የጫነው ዲግሪ አይረዳ የደፋነው ቆብ አያስጥል!

281773279 589624645852490 8570690513383339644 n
Next Story

አሸባሪው ሕወሓት በግዳጅ ዜጎችን ለውትድርና በመመልመልና እርዳታን ለእኩይ አላማ በመጠቀም ተግባሩ እንዲጠየቅ ጥሪ ቀረበ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop