መረጃ ኃይል ነው። ዘ-ሐበሻ ርእስ አንቀጽ ርእስ አንቀጽ March 14, 2022 Facebook X Pinterest Linkedin Whatsapp Reddit Email በብዙ የሰለጠኑ አገራት መረጃን የሚያቀርቡ ሜዲያዎች ከሕግ አውጭው፣ ከሕግ አስከባሪዉና ከሕግ ተርጓሚው የመንግስት ሶስት ቅርንጫፎች በተጨማሪ አራተኛው የ”መንግስት” ቅርንጫፍ ተደርገው የሚቆጠሩ ናቸው። ኢትዮጵያ ግን የሕዝብ ሜዲያዎች የመንግስት ፕሮፖጋንዳ መሳሪያዎች የሆኑበት፣ የግል ሜዲያዎችም ከፍተኛ ጫናና እንግልት የሚደርስባቸው አገር ሆና ነው የቆየችው። ዘ-ሐበሻ፣ ይሄንን ክፍተት በተወሰነ መልኩ ለመምሏት፣ በኢትዮጵያዊያን አቆጣጠር ከ1997 ዓ/ም ጀምሮ፣ ላለፉት አስራ ሰባት አመታት ፣ በኢትዮጵያ ፍትህ፣ ሰላም፣ እድገትና ዴሞክራሲ እንዲኖር፣ ኢትዮጵያዉያን በአገራቸው ጉዳይ ወቅታዊ መረጃዎችን እንዲያገኙ ለማድረግ በመስራት ላይ ያለ ነጻ፣ ገለልተኛ፣ ከገዢዎች ሆነ ከፖለቲካ ድርጅቶች ተጽኖ ውጭ የሆነ ሜዲያ ነው፡፡ Zehabesha.com፣ ዘ-ሐበሻ ትዩብ (Zehabesha Tube) በሚል በዘ-ሐበሻ ስም በመጀመሪያ የተከፈተ የዩቱብ ቻናል አለው። ሆኖም ብዙ በዘሐበሻ ወይም ሃበሻ ስም በርካታ ድህረ ገጾች ፣ዩቱቦች ፣ የፌስቡክ አካውንቶች ተከፍተዋል። ሐበሻ ትዩብ ፣ ዘ-ሐበሻ 1፣ ዘ-ሐበሻ 2፣ ዘ-ሐበሻ 3፣ ዘ-ሐበሻ 4 , Habesha Market and Zehabesha Restaurant የመሳሰሉትን መጥቀስ ይቻላል። በነዚህ ሜዲያዎች የሚቀርቡ ዝግጅቶችና የሚተላለፉ መልእክቶች፣ “ዘ-ሐበሻ ” በሚል ስለሆነ፣ የኛን ሜዲያ ከነዚህ ሜዲያዎች ጋር አንድ አድርጎ የመውሰድ ሁኔታ በአንዳንድ ወገኖች እያየን ነው። በዚህ አጋጣሚ በነዚህ በዘ-ሐበሻ ስም በሚንቀሳቀሱ ሜዲያዎች የሚቀርቡ መረጃዎች ሆነ ዝግጅቶች የ Zehabesha.com፣ እና ዘ-ሐበሻ ትዩብ (Zehabesha Tube) እንዳልሆነ በአክብሮት ለመግለጽ እንወድለን። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያን እያስተዳደረ ያለው፣ በዶር አብይ አህመድ የሚመራው መንግስት አገርን ወደ ከፋ ደረጃ እየወሰደ ነው የሚል እምነት ነው ያለን። በብዙ የአገራችን ክፍሎች እየሞቱ፣ እየተፈናቀሉ፣ ለረሃብ ለጠኔ እየተጋለጡ፣ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት እየተፈጸመባቸው ያሉ ዜጎች ጉዳይ በእጅጉ ያሳስበናል:: መንግስት ነን ብለው በሃላፊነት ላይ የተቀመጡ መሪዎችም፣ ለሕዝብ ሰቆቃ ትኩረት ከመስጠት፣ የሕዝብን ችግር ከመፍታት፣ ጊዜና ጉልበታቸውን፣ የአገርንም ሃብት፣ አላስፈላጊ ድግሶች፣ ፊስቲቫሎች የመሳሰሉት ላይ ማባከናቸው፣ ከነርሱም ብዙዎቹ የሕዝብ ሃብት የመዘበሩና የሚመዘብሩ፣ ለመመዝበርም ሁኔታዎች የሚያመቻቹ ፣ ከተጠያቂነትና ከሕግ የበላይነት ውጭ መሆናቸው በእጅጉ ያሳስበናል። በየጊዜው ለሰላምና ለፍትህ ለዜጎች እኩልነት እየጮኹ ባሉ ጋዜጠኞች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችና የፖለቲካ መሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ወከባ፣ እንግልት፣ እስርና ግድያን አጥብቀን እንቃወማለን። አሁን በስልጣን ላይ ያሉት ገዢዎች፣ ከህወሃት ጋር ይሰሩ የነበሩ ናቸው:፡ ሆኖም ከአራት አመት በፊት በሕዝብ ትግል፣ ተፈናጠው ፣ ከሕወሃት የተለየን ነን ብለው በመቅረባቸው፣ በብዙዎች ዘንድ ታምነው ነበር፡፡ የለውጥ ተስፋም ታይቶ ነበር። ነገር ግን ከተጠበቀው፣ ከታሰበውና ተስፋ ከተደረገው በእጅጉ የተቃረነ ሁኔታ ነው የተፈጠረው። በሕወሃት/ኢሕአዴግ ዘመን ከነበረው እጅግ በባሰ አደገኛ ሁኔታ ላይ ነው ኢትዮጵያ የምትገኘው፡፡ ከአራት አመት በፊት መጣ የተባለውም ለውጥ ሙሉ ለሙሉ ተቀልብሷል ማለት ይቻላል። በመሆኑም እስከአሁን እያደረግን ያለውን በተጠናከረ መንገድ እያደረግን፣ ታማኝነታችን ለኢትዮጵያ ሕዝብ እንደመሆኑ፣ ለሕዝብ ድምጽ መሆናችንን እንቀጥላለን። ሕዝብ እውነትን እንዲያውቅ፣ መረጃዎችን እንዲያገኝ ነጻና ገለለተኛ በሆነ መልኩ እንሰራለን። Zehabesha.com https://zehabesha.com/contact/ Facebook X Pinterest Linkedin Whatsapp Reddit Email Leave a Reply Cancel replyYour email address will not be published. Δ Latest from Blog ህወሃትን ከደሙ ንጹህ ለማድረግ የታቀደ ስብሰባ ወይስ በአብሮ የመኖር ስም አንድን አገዛዝ ብቻ ተጠያቂ ለማድረግ የታቀደ የውይይት መድረክ!! ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር) (ሰኔ 23፣ 2017) June 30, 2025 እ.አ.አ በሰኔ 7፣ 2025 ዓ.ም “የርዕዮት ሚዲያ” ባለቤት የሆነው ቴዎድሮስ ፀጋዬና፣ “የአብሮነት ኢትዮጵያ” አሰባሳቢ መሪ ነኝ የሚለው ልደቱ አያሌው “ታላቅ የተቃውሞ ትዕይንተ-ህዝብ” በሚል፣ ይሁንና ዋናው መሰረተ-ሃሳብ” ጦርነት ይቁም፣ ግፋዊ አገዛዝ ያቁም፣ ዘላቂ ሰላም ይስፈን” በሚሉ ልዩ | ‹ ከቤተመንግስት አልወጣም› ዓብይ | የሽመልስ እና ዝናሽ ግዙፉ ካምፓኒ ልዩ | ‹ ከቤተመንግስት አልወጣም› ዓብይ | የሽመልስ እና ዝናሽ ግዙፉ ካምፓኒ እ.ኤ.አ. በ2024 ብሔራዊ ባንክ 10.5 ቢሊዮን ብር ኪሳራ እንደገጠመው በገለልተኛ ኦዲት ተረጋገጠ በዚሁ ዓመት በነበረ የብር መዳከም 38 ቢሊዮን ብር መክሰሩ ተገልጿል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እ.ኤ.አ. በ2024 በአጠቃላይ የባንክ ሥራው 10.5 ቢሊዮን ብር ኪሳራ እንደገጠመው በገለልተኛ ኦዲት ተረጋገጠ፡፡ ብሔራዊ ባንክ በገለልተኛ የውጭ ኦዲተር ኦዲት 58 የአብይ አህመድ ነጭ ውሸቶች! – ነዓምን ዘለቀ ቆጥራቹህ ስለላካቹህልን እናመሰግናለን! የተረሳ ካለ ጨምሩበት update አደረጋለሁ! 1. ሳናጣራ አናስርም 2.ጊዜ ስለሌለኝ ከኖቬል ሽልማት ፕሮግራም ላይ አልገኝም 3. አንዲት ፈረንሳዊ ላግባህ ብላኝ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ 4. በተከልነው ችግኝ የሀረማያ ሀይቅ ወደነበረበት ኢዜማ ወ ብልጽግና – ቆሎ የመጎራረስ ውል አልባ ጋብቻ ኢዜማ ወ ብልጽግና – ቆሎ የመጎራረስ ውል አልባ ጋብቻ
ህወሃትን ከደሙ ንጹህ ለማድረግ የታቀደ ስብሰባ ወይስ በአብሮ የመኖር ስም አንድን አገዛዝ ብቻ ተጠያቂ ለማድረግ የታቀደ የውይይት መድረክ!! ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር) (ሰኔ 23፣ 2017) June 30, 2025 እ.አ.አ በሰኔ 7፣ 2025 ዓ.ም “የርዕዮት ሚዲያ” ባለቤት የሆነው ቴዎድሮስ ፀጋዬና፣ “የአብሮነት ኢትዮጵያ” አሰባሳቢ መሪ ነኝ የሚለው ልደቱ አያሌው “ታላቅ የተቃውሞ ትዕይንተ-ህዝብ” በሚል፣ ይሁንና ዋናው መሰረተ-ሃሳብ” ጦርነት ይቁም፣ ግፋዊ አገዛዝ ያቁም፣ ዘላቂ ሰላም ይስፈን” በሚሉ
ልዩ | ‹ ከቤተመንግስት አልወጣም› ዓብይ | የሽመልስ እና ዝናሽ ግዙፉ ካምፓኒ ልዩ | ‹ ከቤተመንግስት አልወጣም› ዓብይ | የሽመልስ እና ዝናሽ ግዙፉ ካምፓኒ
እ.ኤ.አ. በ2024 ብሔራዊ ባንክ 10.5 ቢሊዮን ብር ኪሳራ እንደገጠመው በገለልተኛ ኦዲት ተረጋገጠ በዚሁ ዓመት በነበረ የብር መዳከም 38 ቢሊዮን ብር መክሰሩ ተገልጿል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እ.ኤ.አ. በ2024 በአጠቃላይ የባንክ ሥራው 10.5 ቢሊዮን ብር ኪሳራ እንደገጠመው በገለልተኛ ኦዲት ተረጋገጠ፡፡ ብሔራዊ ባንክ በገለልተኛ የውጭ ኦዲተር ኦዲት
58 የአብይ አህመድ ነጭ ውሸቶች! – ነዓምን ዘለቀ ቆጥራቹህ ስለላካቹህልን እናመሰግናለን! የተረሳ ካለ ጨምሩበት update አደረጋለሁ! 1. ሳናጣራ አናስርም 2.ጊዜ ስለሌለኝ ከኖቬል ሽልማት ፕሮግራም ላይ አልገኝም 3. አንዲት ፈረንሳዊ ላግባህ ብላኝ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ 4. በተከልነው ችግኝ የሀረማያ ሀይቅ ወደነበረበት