February 19, 2022
3 mins read

ብ/ጀኔራል ተፈራ ማሞ አዲስ የተመደቡበትን ስራ እንደማይቀበሉት ተገለፀ

274171135 454005153071973 1347107231539728810 nባህርዳር፤ የካቲት 12/2014/
ብ/ጀኔራል ተፈራ ማሞ አዲስ የተመደቡበትን ስራ እንደማይቀበሉት ነዉ የታወቀዉ ከልዩ ሃይሉ አዛዠነት የተነሱበትም ምክንያት ያለቀ ጦርነት የለም የአማራ ህዝብ ተደራጅቶ ራሱን መጠበቅ አለበት ወጣቶች ሰልጥነው ፋኖ መሆን አለባቸው አለበለዚያ የአማራ ልዩሀይልን መቀላቀል አለባቸው በማለተቻዉ እነደሆነ ተናግሯል።
በአማራ ህዝብ ረጅም ታሪክ ውስጥ ለአማራ ህዝብ መከራና ሰቆቃ ከገባቸው በእጣት ከሚቆጠሩ ከፍተኛ አመራሮች መካከል ጀኔራል ተፈራ ማሞ አንዱ ነው የአማራ ልዩ ኃይል ሰራዊት ካደራጁት ጀግኖች መካከል ጀነራል ተፌራ ግንባር ቀደምም ናቸዉ ።
የአማራን ህዝብ ህይወቱን ሁሉ ገብሮ ማገልገል ፍላጎት ያለው ለአማራ ህዝብ ተወልዶ ለአማራ ህዝብ ለመሞት ቃል የገባው ፤ ሸማቂው ኮማንዶ ተፈራ ማሞ ስራን በነጻነት እንዳይሰራ ፣ የሚፈልገውን እና የሚያግዘውን አካል ወደ ፊት እንዳያመጣ ፣ የሚያቀርበውን እቅድ እና የሰው ሀይል ውድቅ ሲያደርጉበት እንደነበርም ለማወቅ ተችሏል ።
ለፈጣንና አዳዲስ መረጃዎች የአይበገሬዎቹ ልሳን:-
አሻራ ሚዲያ
—–
የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አዛዥ የነበሩት የብ/ጄነራል ተፈራ ጠባቂዎች መታሰራቸው ተገለጸ
ከዚህ ቀደም በአማራ ክልል ባለስልጣናት ግድያ ተጠርጥሮ ከታሰሩ በኋላ ክሱ ተነስቶለት የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አዛዥ ተደርጎ ተሹመው ባለፉት ሁለት ዓመታት የአማራ ልዩ ኃይልን እና ፋኖን በማደራጀት በጦርነቱ ቁልፍ ተሳትፎ እንደነበራቸው የሚነገርለት ብ/ጄነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን በፌዴራል መንግስት እና በፋኖ አደረጃጀት መካከል በተፈጠረው አለመግባባት ከሥልጣናቸው ተነስተው የፕሬዚደንቱ የደህንነት አማካሪ ሆኖ እንዲሰሩ ብመደብም አልቀበልም ማለታቸው ይታወቃል።
ትናንትና ምሽት ደግሞ የጄነራሉ ጠባቂዎች የሆኑት ሁለት ልዩ ኃይል አባላት ታፍነው መወሰዳቸው ከባህር ዳር የሚወጡ መረጃዎች አመልክተዋል።
ማለዳ ሚዲያ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

Go toTop