የአሜሪካና ምዕራባውያን ጫናና መፈንቅለ መንግሥት በግርማዊነታቸው መንግሥት ላይ!! – መስፍን ማሞ ተሰማ

/

የአሜሪካና ምዕራባውያን ጫናና መፈንቅለ መንግሥት በግርማዊነታቸው መንግሥት ላይ!! [መስፍን ማሞ ተሰማ]

ንጉሠ ነገሥቱ [ ግርማዊ ቀዳማዊ ሃይለ ሥላሴ ] ርዳታ ለመጠየቅ [ኢትዮጵያን በግብርናና በኢንዱስትሪ ለማልማት] የተለያዩ የአሜሪካንና የአውሮፓ ሀገሮችን ከግንቦት 10 ቀን እስከ ሐምሌ 28 ቀን1946 /ም ከሁለት ወር በላይ ለሆነ ጊዜ ጎብኝተው ለትምህርትና መከላከያ ከሚውሉ ጥቃቅን ርዳታዎች በስተቀር [ ይህንን ነጥብ ልብ ማለት ያስፈልጋል ] ባዷቸውን ተመለሱ። ብዙም ሳይቆዩ ከመስከረም 25 ቀን 1947 /ም አስከ ህዳር 28 ቀን 1947 /ም በዘጠኝ የአውሮፓ ሀገሮች በመዘዋወር የልማት ገንዘብ ፍለጋ ከሁለት ወር በለሠይ ጉብኝት ቢያደርጉም አሁንም ለልማት የሚውል ርዳታ ሳያገኙ ቀሩ።

በእነዚህ ሁለት ጉዞዎች አሜሪካንና አውሮፓን ጎብኝተው ከምዕራቡ ዓለም ምንም ርዳታ በማጣታቸው ወደ ምሥራቅ ሀገሮች ሄደው ርዳታ ለማግኘት ከወዳጃቸው ከዩጎዝላቪያው መሪ ከፕሬዚዳንት ማርሻል ብሮንዝ ቲቶ ጋር ሲመክሩ ቆዩ። በነሐሴ ወር 1951 /ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስሊዎስ የፓትሪያርክ ሹመት ላይ ለመገኘት ወደ ግብፅ እንደሄዱ ሳይታሰብ በዚያው ጉዞ ድንገት ሶቪየት ኅብረት ሞስኮ መግባታቸው ተሰማ። 

ሞስኮ በገቡ በሶስተኛው ቀን ለልማት ሥራዎች ሁሉ የሚያስፈልግ እና በረጅም ጊዜ የሚከፈል አራት መቶ ሚሊዮን ሩብልስ አግኝተው ተመለሱ። [ ይህ የርዳታ ገንዘብ በዚህ ወቅት የምንዛሪ መጠን ከአምስት ሚሊዮን አምስት መቶ ሰማኒያ ሺህ ዪኤስ ዶላር በላይ ሲሆን ዶላሩ ወደ ኢትዮጵያ ብር ሲመነዘር ደግሞ ከሁለት መቶ ስልሳ ስድስት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሺህ ብር በላይ መሆኑን ልብ ይሏል ] ለልማት የሚያውሉትን መጠነ ሰፊ የርዳታ ገንዘብ አግኝተው ነሐሴ 18 ቀን 1951 /ም ኢትዮጵያ እንደተመለሱ በአራተኛው ቀን ነሐሴ 22 ቀን 1951 /ም ማታ እና በ14ኛው ቀን መስከረም 7 ቀን 1952 /ም ከቀኑ በስምንት ሰዓት የኢትዮጵያ ሕዝብ ለልማት ታጥቆ እንዲነሳ በሬዲዮ ሰፊ ንግግር አሰሙ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  እነ ሚሚ ስብሃቱ የሚያጨሱት ምኑን ነው?

ንጉሠ ነገሥቱ ከምዕራቡ ዓለም የተነፈጉትን ለልማት ሥራዎች() ለጭሰኞች መሬት እየሰጡ ለማስፈር  የሚውል የገንዘብ ርዳታ ከምዕራቡ ዓለም ጋር ተቀናቃኝ ከነበረችው ከኮሚኒስቷ ሶቪየት ኅብረት በማግኘታቸው ኢትዮጵያውያን ሁሉ፣ በየዘርፉ በሚገኙ የልማት ሥራዎች ላይ ለሥራ ታጥቀው እንዲነሱ የሚቀሰቅስ ሰፊ ንግግር አደረጉ። ከዚህ ሁኔታ በሁዋላም ከምሥራቅ ሀገሮች ጋር የተደረገው ግንኙነት የምዕራቡን ኃያላን መንግሥታት ስላስቆጣቸው በየአቅጣጫው በኢትዮጵያ ላይ ጫናቸውን ያሳድሩ ጀመር። [እዚህ ላይ በኛ ዘመን ኢትዮጵያ በቀንደኛነት ከአሜሪካ ከእንግሊዝ ከፈረንሳይና ከተመድ የገጠማትን ጫናና ጣልቃ ገብነት ልብ ማለት ያስፈልጋል ] በተለይ በሐረርጌ ጠቅላይ ግዛት ኮሎኔል ፒንክ የኦጋዴን ሶማሌዎችን በታላቋ ሶማሌ የህልም እንጀራ የመመገብ ፕሮፓጋንዳ ኦሮሞዎችንም እንዲጨምር ለማድረግ እንቅስቃሴውን አጠናከረ። በደጋው የሐረርጌ ጠቅላይ ግዛት ለሚኖሩ የኦሮሞ አርሶ አደሮች ኃይለ ሥላሴ ከኮሚኒስቷ ሶቪየት ኅብረት ያመጣው ብድር እናንተን ጭሰኞችን ባለዕዳ ለማድረግ አማራውን ለማበልፀግ እና ከቀድሞውም በበለጠ ለአማራው ባለርስቶች ተገዥ እንድትሆኑ ለማድረግ ነውና ተነሱየሚል ፕሮፓጋንዳ ይነዛ ጀመር። 

ፕሮፓጋንዳው በዚህ መልክ እየተነዛ እያለም ንጉሠ ነገሥቱ በዘመነ መንግሥታቸው ረጅምና ታሪካዊ የሆነውንና የኢትዮጵያ ሕዝብ ልማት ታጥቆ እንዲነሣ በመድረግ ላይ ያተኮረ ንግግር በሬዲዮ አስተላለፉ። ንግግሩ የኢትዮጵያ ሕዝብ ተባብሮ ከሰራ በጓዳው፣ ደጁ፣ ጓሮው፣ ሜዳው ሸለቆው ጋራውና ሸንተረሩየሚገኘው ሀብት ተዝቆ የማያልቅ መሆኑን በመጥቀስ በዋዛ ፈዛዛ ጊዜውን ሳያባክን በተለያዩ የልማት ዘርፎች ላይ ተሰማርቶ የሚቀሰቅስ ነበር። ያ የንጉሠ ነገሥቱ ንግግር ለዚያን ጊዜም ሆነ ለአሁኑ እና ለወደፊቱም ትውልድ ጭምር ኢትዮጰያውያን ከድኅነት ተላቀው በብልፅግና መኖር የሚችሉበትን መንገድ የሚያመላክት ነው። [በምዕራባውያን በተቀነባበረ  ከፍተኛ አሻጥሮችና ሁዋላም በ1953 /ም በአሜሪካውያን ድጋፍ በነግርማሜ ነዋይ የተሞከረውና በርካታ የንጉሠ ነገሥቱን መንግሥት የልማት ውጥን ደጋፊ ከፍተኛ ባለሥልጣናት በወንድማማቾቹ ግርማሜና ጄኔራል መንግሥቱ ነዋይ የተረሸኑበት መፈንቅለ መንግሥት ተደርጎ የልማት ውጥኑም እንዲከሽፍ ተደርጓል።]

ተጨማሪ ያንብቡ:  ምክር ለጠ/ሚኒሰቴር አብይ አህመድና ለሁላችንም - ሰርፀ ደስታ

* ሕይወቴ ለአገሬ ኢትየቀጵያና ለወገኖቼ ኢትዮጵያውያን ዕድገት የነበረኝ የሥራ ጥማት –  ቅፅ አንድ (1917 እስከ 1967 /) ደጃዝማች ወልደ ሰማዕት ገብረ ወልድ ገፅ ብዛት 636 * [ ከላይ ባቀረብኩት ፅሁፍ ውስጥ በቅንፍ የተቀመጡት ከመፅሀፉ በቀጥታ ቃል በቃል የተወሰዱ ሳይሆኑ ነገር ግን የመፅሀፉን መልዕክት የጠበቁ ጭማሮዎች ናቸው መማተ ]

3 Comments

  1. አሜሪካኖች ሰይጣኖች ናቸው። ንጉሱን ከኤርትራ ጋር እንዲላተሙ ያረጉት እነርሱ ነበሩ። በጎን ፓርላማው እንዲታጠፍ ሲቀሰቅሱ በሌላ በኩል ደግሞ ለኤርትራዊያን እንዴት እንዲህ ትሸወዳላችሁ እያሉ ነፍጥ እንዲያነሱ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ድጋፍ ያደርጉ ነበር። የትላንቱና የዛሬው ሴራቸው ጠልቆ ከተረዳው አፍሪቃዊ መሪ ውስጥ የኤርትራው መሪ ኢሳያስ አፈወርቂ ቀዳሚው ነው። ገብቶታል። ለዘመናት እኛን ሲያጫርሱንና ከሩቅና ከቅርብ ሆነው እሳት ሲያቀብሉን የነበሩትና ያሉት እነርሱ መሆናቸውን። ለዚህም ነው በየጊዜው በኤርትራ ጉዳይ ላይ በሚደረገው ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ ጫና ሰበበ ወይ ፍንክች በማለት ምዕራባዊያኖችን አክ እንትፍ ያላቸው። ወያኔን ስልጣን ላይ ለማስወጣት በኮ/መንግስቱ ሃ/ማሪያም ላይ የተከፈተው ዘመቻና ውጤቱ አሁን በዶ/ር አብይ ላይ ከሚደረገው ዘመቻ ጋር በእጅጉ ይመሳሰላል። ግን ጊዜው ተቀይሯል። ስው ነቅቶባቸዋል። ዋና ተግባራቸው ሃገር ማፍረስና መንግስት መገልበጥ ብቻ ሙሉ ስራቸው የሆነው አሜሪካኖች አለምን እያበራዪና እየዘረፉ ኖረዋል። ከብራዚ እስከ ሄቲ ከካይሮ እስከ ሪያድ እጃቸው ያልገባበትና ያላላተሙት ህዝብና መንግስት የለም። የሚገርመው ትንሽ ነቃ ያሉና ለሃገርና ለወገን በማሰብ አይ ለእናንተ አንታዘዝም ያሉትን የአፍሪቃ መሪዎች በየደረጃ አጥፍተዋቸዋል። እጅግ ዘግናኙ ነገር ደግሞ ራሳቸው ገድለው ራሳቸው መርማሪ መሆናቸው ነው። አሁን እንሆ በቅርቡ ሄቲ ውስጥ ቤ/መንግስት ድረስ በመግባት የተገደለው መሪ መርማሪዎቹ እነርሱ ናቸው።
    ታዲያ ይህና ሌላው ግፋቸው መልሶ የሚወስደን አሁን የወያኔ አለቅላቂ መሆናቸው ለምን ይሆን ወደ እሚለው ጥያቄ ነው። ወያኔ የአሜሪካ ጉዳይ አስፈጻሚ ነበር። በእርዳታና በብድር ለሃገሪቱ የሚሰጠውን ገንዘብ መልሶ ለአበዳሪዎቹ የሚያካፍል በስርቆትና በቀጥታ ሌብነት የተካነ ቡድን ነው። ወያኔ እዚህ ሂድ ይህን አርግ ሲሉት የሚላላክላቸው ሃይል ነበር። ባጭሩ ሰርቆ ያበላቸዋል፤ ተልኮ ይላካቸዋል፤ ብዙ በዚህ ላይ ሊገለጡ የማይችሉ የሶስተኛ ሃገር ጉዳይ አስፈጻሚ ሁሉ ሆኖ ሰርቷል። የአሜሪካ የውጭ ፓሊሲ የውሻ ፓለቲካን ይወዳል። መነካከስን። ዲሲ ላይ 9 ታክሲ ነጂዎችን አሰልፎ የአበይ መንግስት የተቃዋሚ ድርጅቶች ብሎ ሲያስተዋውቅ በጎን ደግሞ ፊልትማን አዲስ አበባ ገብቶ መሪዎችን አልቋል ከሃገር ውጡ እኛ መጠለያ እንስጣችሁ እያለ ነበር የሚያታልላቸው። ይህ የአሜሪካ ሴራ ገሃድ ሆኖ የማይታየው ካለ እውር ሰው ብቻ ነው። የኤምባሲ መዝጋቱ ማስፈራራት፤ ሌሎች ያን ተከትለው እንዘጋለን ወይም ዜጎቻቸው ወደዚያ እንዳይሄድ መነገሩ ከዚሁ ከሴራቸው አንድ ክፍል ነው። እልፍ ጊዜ በተመድ የሆነውም ስብሰባ የሴራው አንድ ማሳያ ነው። ግን ወያኔ እንኳን አዲስ አበባ ሊገባ በገባበት ሁሉ ሰው እየተሰባሰበ እየቀበረው ነው። የውጭ ሃገር የዜና ማሰራጫዎች የሚያናፍሱት የፈጠራ ወሬ የዚሁ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ፓሊሲ ቅጥያ እንጂ እንደሚባለው independent and investigative ሥራ ላይ የተመረኮዘ አይደለም። ባጭሩ የአሜሪካ ዲሞክራሲ ልክ እንደሌላው ዓለም ሁሉ ገንዘብ ላለው የሚሰራ ዲሞክራሲ ነው። በድሃና ቆዳቸው በጠቆረ ላይ የሚቀልድ። ዲሞክራት በለው ሪፕብሊካን ክፋታቸው ያው ነው። የእኛ ሃገር ነብይ ሳትቀር ኋት ሃውስ ድረስ መጥታ የጸለየችለት፤ የአሜሪካ ቤ/ክርስቲያናት ሃገር አዳኝ እያሉ የዘመሩለት ትራምፕ በምድሪቱ ከተነሱ መሪዎች መካከል አደገኛና ጥቁር ጠል እንደሆነ አፉ ይናገራል። ዛሬም ጊዜውን የሚፈጀው ሰው ሲሳደብና በልዪ ልዪ ክሶች ተጠላልፎ ፍርድ ቤት ሲቀርብና ጠበቃ ሲያናገር ነው። የሰማይ ቤት አዳሪ ነን የሚሉት ሁሉ ማበዳቸውን ያየሁት እሱን ከፈጣሪ ጋር ለማስተካከል ሲከጅሉ ነው። አታድርስ። በመዝጊያው ከንጉሱ እስከ አሁን ባለን ጥቂት የደስታም ሆነ ብዙ የመከራ ዘመን ም ዕራባዊያንና አረቦች ኢትዮጵያን ለማሽመድመድ ያልሞከሩት ሴራ የለም። እየተንገዳገድንም ቢሆን ይኼው ዳዲ እንላለን። ነገ ምን ይሆናል ስለሚለው የሚያውቅ የለም። ጠብቀን እናያለን። በቃኝ!

  2. ሞስኮ በቅኝ ገዥዎች የተያዙ ሃገራትን ነፃ ለማውጣት እርዳታና ድጋፍ ስታደረግ እንጂ በቅኝ ልግዛ ያለችበት ጊዜ የልም። የምዕራቡ ዓለማት ግን ሃቁ እንዳይታወቅ ያልታከተ ጥረት አድርግዋል፣ ተሳክቶላቸዋልም። መስፍን ማሞ ለማ የሞስኮን እርዳታ አመላክትው እንደገለጹት እርዳታው በሞስኮ (በሶቭየት ሕብረት) ለንጉሠ ነገሠቱ ከተሰጠና ድጋፉም የሚቀጥል መሆኑን ካረጋገጡ በኋላ ይሆናል ሕዝባዊ ኑሮ እድገት (ሚኒስትሪ ኦፍ ኮምዩኒቲ ደቨለፕመንት) የሚባል መሥሪያ ቤት በሚንስተር ደረጃ ያቛቛሙት። የመሥሪያ ቤቱ ዋና ጽሕፈት ቤት አዲስ አበባ ካዛንቺስ ውስጥ ሲሆን ማሰልጠኛ ጣብያው ቀድሞ አዋሳ አሁን ሐዋሳ ከተማ ነበር።
    ወጣቶችም የስልጠና ትኩረታቸው የገጠሩን ሕብረተሰብ ኑሮ ማሻሻል ላይ ነበር፣ የግብርናን ምርት በተሻለ ዘዴ ማሳደግ፣ የመጠጥ ውሃ ማውጫ መሳሪያ እንዲያገኙ ማድረግ፣ በሕብረት ሥራ ምርትን ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚነትን ማሳደግና የመሳሰሉትን በመማር ሕዝባዊ አገልግሎት ነበር። ይህንኑ ለማጠናከርም ሞስኮ ወጣቶችን በመቀበል ሥልጠና በመስጠት ቆይታለች። የሕዝባዊ ኑሮ ዕድገት መሥርያ ቤቱም፣ማሰልጠኛውም እስከነዓላማውና ተግባሩ ከደርግ መንግሥት በኋላ እንዳልቀጠለ ከፈረሱት መንግሥታዊ መዋቅሮችም አንዱ እንደነበር መገንዘብ አያዳግትም።

  3. The so called big country America, state department a higher official but he is doing silly thing in the ground, day and night working to dismantle the unity of Ethiopia and accomplish the vision of Egypt and also bring to power the terrorist group. If anybody or country is against their interest, they vow first to say “Terrorist”, one day you will be liable on International Criminal Court if Truth Prevails. Ever body you see how this bullshit US foreign policy play the game in the world and intervene deliberately in the sovereignty of one country.

    Long live to Ethiopia!!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share