
ሐሙስ፣ ነሐሴ ፳ ፩ ቀን ፳ ፻ ፲ ፰ ዓ. ም. (8/27/2026)
ታሪክ በሰዎች ፍላጎትና ዕቅድ የተከተበ ሰነድ ሳይሆን፤ በተከናወነ ተግባርና በተከሰተ እውነታ የተመላ መዝገብ ነው። ይሆናል እና ቢሆን ኖሮ ለሚሉት፤ ታሪክ ቦታ የለውም። ዛሬ ማድረግ ያለብንን ለነገ በቀጠሮ ብናስቀምጠው፤ ታሪክ እኛን የምትጠብቅ ተስፈኛ አይደለችም። በኢትዮጵያ ያለው የአክራሪ ኦሮሞ ገዢ ቡድን ሕጋዊነት ሆነ ችሎታ፤ አብቅቶለታል። አሁን ማድረግ ያለብን ግዴታ፤ ይሄንን ስርዓት በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ መጠገን፣ ማስቀጠል ወይንም ማሻሻል ሳይሆን፤ በቃህ ብሎ ማሰናበት ነው። በማንኛውም በዚህ ባበቃለት ስርዓት መዋቅር ውስጥ ያላችሁ ኢትዮጵያዊያን፤ አሁን ሁለት ኃላፊነት አላችሁ። አንደኛው ወገንን እና አገርን ማገልገል ነው፤ ሌላው የራሳችሁን ደህንነት መጠበቅ ነው።
አብይ መራሹ የአክራሪ ኦሮሞዎች ገዢ ቡድን የያዘው፤ የአገር ጉዳይን አሸንቅጥሮ ጥሎ፤ አብይን መጠበቅና በዙሪያው የተኮለኮሉትን ጥቅመኞች መንከባከብ ነው። ወጣቶችን ከመላ አገራችን እያፈሰ ለጦርነት እየማገደ ነው። ጦርነቱም ኢትዮጵያዊያን እርስ በርስ እንዲጨራርሱ የሚያደርግና፣ ታሪክ የማይሽረው፣ በኢትዮጵያዊያን መካከል መከፋፈልን እና ቂምን አስቋጣሪ የሆነ የመጠፋፋት አባዜ ነው። እናንተ በአገሪቱ ተሰማርታችሁ መዋቅሩን የምታንቀሳቅሱ ግለሰቦች አጀንዳችሁ፤ ወገንና አገራችሁን ማገልገል እንጂ፤ አብይ አሕመድን ወይንም የሱን አሽቃባጮች መንከባከብ አይደለም። በዚህ ከቀጠላችሁ፤ ካበቃላት መርከብ ጋር አብራችሁ መስመጣችሁ ነው። ልብ ልትሉት የሚገባው፤ አብይና አሽቃባጮቹ፤ ከዚህም ከዚያም መነጫጭቀው የሰበሰቡትን የአገር ንብረት ይዘው፤ የአገራችንን ህልውና ወደ ሸጡላቸው አገራት ይኮበልላሉ። ያን ጊዜ ምን ይውጣችኋል! የኢትዮጵያ ሕዝብ ይቅር ባይ ነው። ይህ ይቅርታ ግን፤ አውቀውና ዕድሉ ኖሯቸው ላልተጠቀሙበት አይሆንም። እናንተ የመጨረሻው ዕድል እነሆ ቀርቦላችኋል። የአብይ አሕመድ ገዢነት ቀናት የተቆጠሩ ናቸው!
ውድ በጦር ሠራዊት፣ ፖሊስና ሚሊሽያ፤ አገር ለማገልገል የተሰማራችሁ ወታደሮች!
አገር ወጣት ልጆቿን በጦር ሠራዊት አሠልጥናና አዋቅራ፤ ደንበሯን ታስከብራለች፣ ጥቅሟን ታስጠብቃለች፣ ዓለም አቀፍ ቦታዋን ትይዛለች። ይህ የተቋቋመ ሠራዊት፤ አጀንዳው ሕዝብ መጠበቅና አገርን ከጠላት መከላከል ነው። አምባገነኖች ይሄንን አይቀበሉም። በነሱ አረመኔ ጭንቅላት፤ ሠራዊቱ፣ እነሱን ከሕዝቡ ለመከላከል፤ ግደል ሲሉት የሚገድል፣ ተኩስ ሲሉት የሚተኩስ፣ ለደሞዙ ብቻ የሚሠራ የቁጥር ጉዳይ ነው። አሁን ከፊታችሁ የቀረበው፤ እናንተ የሕዝብና የአገር አገልጋዮች ናችሁ? ወይንስ የአብይና የአሽቃባጮቹ? ይሄን የምትመልሱ እናንተ ናችሁ። አንደኛውን መጨበጥ ብቻ አይደለም ከፊታችሁ የቀረበው ምርጫ! ራሳችሁን የማዳንም ጉዳይ ነው። ይህ የአክራሪዎች አምባገነንገዢ ቡድን እናዳበቃለት ልባችሁ ያውቃል! ታዲያ ምን እስኪመጣ ነው የምትጠብቁት! አለቆቻችሁን አልታዘዝም ማለት ያለባችሁ አሁን ነው! ሳይዘገይ! ከሕዝብ ጋር የምትሰለፉበት ሰዓት አሁን ነው! በታሪክና በኛ አገርም እንዳየነው፤ አለቆቻችሁን በቁጥጥር ሥር አውላችሁ፤ አንድም አብረዋችሁ እንዲቆሙ! አለያም ዘብጥያ እንዲገቡ አድርጉ!
ውድ በመንግሥቱ መሥሪያ ቤቶች ተቀጥራችሁ ስርዓቱን የምታገለግሉ ኢትዮጵያዊያን! ዙሪያችሁን ተመለከቱ! ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊያን አሉ ወይ?ራሳችሁን ጠይቁ? ማንን እያገለገላችሁ ነው? ይህ ገዢ ቡድን በየዕለቱ ምን እያደረገ ነው? የሕዝቡን ኑሮ አያሻሻለ ነው ወይንስ እያከፋ! ትናንት እና ከትናንት ወዲያ ከምትኖሩበት ሁኔታ፤ ዛሬ የተሻለ ላይ ነው ያላችሁት? የገንዘቡ ዋጋ ምን እየሆነ ነው? ደሞዛችሁ እያደገና ለኑሯችሁ የተሟላ እየሆነ ነው? ይህ ስርዓት አብቅቶለታል! እናንተ አሁን፤ አንድም ራሳችሁን የማዳን፣ ሌላም በእውነት ሕዝቡን የማገልገል ዕድሉ አላችሁ። ያንን ግን ማድረግ የምትችሉት፤ በዚህ እየፈራረሰ ካለ አብይ መራሽ የአክራሪ ኦሮሞዎች ገዢ ቡድን ጋር ተሰልፋችሁ አይደለም። ረሃብ ጠንቶ እስክትሞቱ አትጠብቁ! ዛሬ ምርጫው በጃችሁ ነው። ነገ ከጃችሁ ወጥቶ የምትወድቁበትን አታውቁም! ራሳችሁን አድኑ! ኢትዮጵያን አድኑ!
ውድ የአገሬ ወጣትና ተማሪ!
ነገ የኢትዮጵያ ባለቤት፤ አንተ እና አንቺ ናችሁ። ዛሬ ያልተደከመበት ነገ፤ የተንኮታኮተና እጅና እግሩ የማይጨበጥ ተስፋ ነው። ወጣት፤ ለወገኑና ለአገሩ ግንባር ቀደም ተሰላፊ ነው። ወጣት የለውጥ ሞተር ነው። ወጣት ለአገሩ የሚቆጭ ትንታግ ደፋር አለኝታ ነው። አንቺ፤ ያ ነው በልብሽ የሚንቶገቶገው! አንተ፤ የነገህ ባለቤት የምትሆነው፤ ዛሬ ተሰልፈህ ስትገኝ ነው። አገር እያፈራረሰ፣ ሕዝብን እያጫረሰ፣ ቂምን እና መከፋፈልን እያነገሠ ያለ ስርዓት፤ ምን ሊያወርሳችሁ
ይችላል! ዛሬ ሁሉን አውድሞ፣ ነጋችሁን አበላሽቶ፣ ከፊታችሁ እያያችሁ፤ ነገን መጠበቁ ከየዋህነትም የከፋ ነው። ዛሬ ለአገራችን ተስፋ የሆኑን፣ የህልውና ትግል የያዙትን አርበኞቻችንን በመቀላቀል፤ የእውነት ነጋችሁን የናንተ አድርጉ! ፋኖን ተቀላቀሉ! ይህ ስርዓት፤ ዛሬን ብቻ ሳይሆን፣ ነገን እያጠፋ ነው!
ውድ እናቶች!
ለጦርነት የሚማገዱት፤ ዘጠኝ ወር በማህፀናችሁ ተሸክማችሁ፣ ለሶስት ዓመታት ብቻ ሳይሆን፣ በልጅነት አጥብታችሁ፣ ሁልጊዜ እንዳይራብ እናንተ ተርባችሁ፣ አብልታችሁ ያሳደጋችኋቸው ልጆቻችሁ ናቸው። በየተገኙበት እየታደኑ ለእርድ እየቀረቡ ነው። እስከመቼ የማህፀናችሁ ፍሬ ለአብይ አሕመድ መራሹ የአክራሪ ኦሮሞዎች ገዢ ቡድን ጭዳ ይሆናል! አዎ! በጃችሁ ጦር የለም! አዎ! አልተደራጃችሁም! ነገር ግን፤ ለልጆቻችሁ ህይወት ባደባባይ ወጥታችሁ ኡ! ኡ! በሉ። ተጠራሩ! በቃን! በሉ! ከጉያዬ አውጥቼ ልጄን አልሠጥም! በሉ።
የብልፅግና አባላት!
ማንኛችንም በአገራችን ስንኖር የምንጠየቀው፤ ለወገን እና ለአገር ባበረከትነው በጎ ተግባር ወይንም በፈጸምነው በደል ነው። አሁን በኢትዮጵያ፤ የብልፅግና አባላት፤ የአብይ መራሹ አክራሪ ኦሮሞች ገዢ ቡድን መሳሪያ ሆናችሁ፤ ኢትዮጵያዊያንን እና ኢትዮጵያን እያጠፋችሁ ነው። ለወገናችሁ እና ለአገራችሁ ሳይሆን፤ ለአገር አጥፊው አብይ እየሰገዳችሁ ነው። ይህ ግለሰብ፤ ማንንም ጄኔራል አያከብርም! ማንንም የሕክምና ሊቅ አይቀበልም! ማንንም የምጣኔ ሀብት ሊቃ አያስተናግድም! ከሃይማኖት አባቶች በላይ ሃይማኖት አዋቂ፣ ከሐኪሞች በላይ በሺታን ተንታኝ፣ ከዘበኛው በላይ ዘበኛ ነኝ! ባይ ነው። ይሄ የአእምሮ በሺታ ያለበት ወይንም በሥልጣን የመስከር እብሪቱ፤ ራሱን ሕግ፣ ራሱን አገር፣ ራሱን ፓርላማ፣ ራሱን ቀን፣ ራሱን ጨለማ፣ ራሱን የጊዜ ሁሉ ባለቤት ያደረገ ቀዋስ፤ በገዢነት በቆዬ ቁጥር፤ አገራችን ተመልሳ እንዳትቋቋም እያፈራረሳት ነው። ራሳችሁን አድኑ! ከታሪክ ልትማሩ ይገባል! እንዲህ ያለ ገዢ ቡድን፤ ዕድሜው አጭር ነው። እናም ዛሬውኑ ከሕዝብ ጋር በመወገን፤ የአገራችሁን ህልውና አስጠብቁ! ከማንም በላይ ለራሳችሁ ስትሉ!