ESFNA 2013: የኢትዮጵያ ቀን በሜሪላንድ በደመቀ ስነ ሥርዓት ተከበረ

July 6, 2013

(ዘ-ሐበሻ) ከተጀመረ 6ኛ ቀኑን በያዘው የሰሜን አሜሪካ የስፖርት እና የባህል ፌስቲቫል ዛሬ የኢትዮጵያ ቀንን በደመቀ ሁኔታ በሜሪላንድ አከበረ። በሲልቨርስፑሪንግ በርድ ስታዲየም በ20-30 ሺህዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ተገኝተው ይህን የኢትዮጵያ ቀን አድምቀውታል። በሌላ በኩል በሼህ መሀምድ አላሙዲ ስፖንሰር አድራጊነት በዲሲ እየተደረገ ያለው ስፖርት ዝግጅት በባዶ ስታዲየም መካሄዱን የቀጠለ ሲሆን በአላሙዲ ሰዎች ወጪያቸው ተችሎ ለክብር እንግድነት የመጡ ሰዎች ሳይቀሩ ወደሜሪላንድ በመምጣት ኢትዮጵያውያኑን ተቀላቅለዋል።
ከነዚህም ውስጥ የብሄራዊ ቡድናችን ተጫዋች አዳነ ግርማ የዲሲውን ዝግጅት ጥሎ ወደ ሜሪላንዱ በመምጣት ከሕዝብ ጋር የኢትዮጵያን ቀን አክብሯል።
“ይህ ሕዝብ ገንዘብ አይገዛውም” በሚል መፈክር ያሰማ ሲሆን በመሃሉም የባህል እና የዘመናዊ ሙዚቃዎች በስታዲየሙ የሚገኘውን ሕዝብ አስናንቶታል።
ተጨማሪ መረጃ ይዘን እስከምንመለስ ፎቶዎችን እና ጥቂት ቪድዮዎችን እናቃምሳችሁ፦

http://www.youtube.com/watch?v=8tEAjPJhc6g

http://www.youtube.com/watch?v=b48TWiumJAE

http://www.youtube.com/watch?v=aDMweIj9LrQ

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop