August 3, 2014
2 mins read

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የፍ/ቤት ቀጠሮው ለመጪው ዓመት ተቀጠረ

 

ተመስገን ደሳለኝ)
የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የፍ/ቤት ቀጠሮው ለመጪው ዓመት ተቀጠረ 1

በቀድሞው የ“ፍትህ” ጋዜጣ ላይ ዋና አዘጋጅ ሆኖ ሲሰራ ሶስት ክሶች የቀረቡበት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ በተደጋጋሚ ቀጠሮው ሲተላለፍበት ቆይቶ፣ ከትላንት በስቲያ ለመጪው ዓመት ተቀጠረ፡፡ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት፣ ሐምሌ 11 ቀን 2006 ዓ.ም ጋዜጠኛው የቀረቡበት ሶስት ክሶች ላይ ማስረጃዎችን መርምሮ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ሲጠበቅ፣ዳኛው አዲስ ናቸው በሚል ተለዋጭ ቀጠሮ ለሐምሌ 24 መሰጠቱ ይታወሳል፡፡ ከትናንት በስቲያ ሃሙስ ከሰአት በኋላም በድጋሚ ዳኛው በመቀየራቸው መዝገቡን መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ለጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ በጋዜጠኛው ላይ የቀረቡት ሶስት ክሶች በቀድሞው “ፍትህ” ጋዜጣ ላይ “መጅሊሱ፣ ሲኖዶሱና የአብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ማጥመቂያዎች”፣ “የፈራ ይመለስ” እና “የብሄረሰቦች መብት እስከ መጨፈር” በሚሉ ርእሶች በተለያዩ ጊዜያት በወጡት ፅሁፎች፤ መንግስትን በአመፅ ለመናድ ቀስቅሷል፣ የመንግስትን ስም አጥፍቷል፣ የህዝብን አስተሳሰብ ለማናወጥ ሰርቷል፤ የሚሉ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ የፍ/ቤት የክርክር ሂደቱ ሁለት አመታትን መፍጀቱ ታውቋል፡፡

ምንጭ፥ -አዲስ አድማስ

addis ababa realethiopia 141
Previous Story

በአዲስ አበባ ሕገወጥ የመሬት ወረራ ተባብሷል

Next Story

አረና ፓርቲ ተከፋፈለ መባሉን አስተባበለ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop