August 3, 2014
2 mins read

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የፍ/ቤት ቀጠሮው ለመጪው ዓመት ተቀጠረ

 

ተመስገን ደሳለኝ)
የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የፍ/ቤት ቀጠሮው ለመጪው ዓመት ተቀጠረ 1

በቀድሞው የ“ፍትህ” ጋዜጣ ላይ ዋና አዘጋጅ ሆኖ ሲሰራ ሶስት ክሶች የቀረቡበት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ በተደጋጋሚ ቀጠሮው ሲተላለፍበት ቆይቶ፣ ከትላንት በስቲያ ለመጪው ዓመት ተቀጠረ፡፡ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት፣ ሐምሌ 11 ቀን 2006 ዓ.ም ጋዜጠኛው የቀረቡበት ሶስት ክሶች ላይ ማስረጃዎችን መርምሮ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ሲጠበቅ፣ዳኛው አዲስ ናቸው በሚል ተለዋጭ ቀጠሮ ለሐምሌ 24 መሰጠቱ ይታወሳል፡፡ ከትናንት በስቲያ ሃሙስ ከሰአት በኋላም በድጋሚ ዳኛው በመቀየራቸው መዝገቡን መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ለጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ በጋዜጠኛው ላይ የቀረቡት ሶስት ክሶች በቀድሞው “ፍትህ” ጋዜጣ ላይ “መጅሊሱ፣ ሲኖዶሱና የአብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ማጥመቂያዎች”፣ “የፈራ ይመለስ” እና “የብሄረሰቦች መብት እስከ መጨፈር” በሚሉ ርእሶች በተለያዩ ጊዜያት በወጡት ፅሁፎች፤ መንግስትን በአመፅ ለመናድ ቀስቅሷል፣ የመንግስትን ስም አጥፍቷል፣ የህዝብን አስተሳሰብ ለማናወጥ ሰርቷል፤ የሚሉ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ የፍ/ቤት የክርክር ሂደቱ ሁለት አመታትን መፍጀቱ ታውቋል፡፡

ምንጭ፥ -አዲስ አድማስ

addis ababa realethiopia 141
Previous Story

በአዲስ አበባ ሕገወጥ የመሬት ወረራ ተባብሷል

Next Story

አረና ፓርቲ ተከፋፈለ መባሉን አስተባበለ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop