የአዲስ-ኦሮምያ ጉዳይ በመቐለ-እንደርታ ዓይን – ከአብርሃ ደስታ

ስለ አዲስ አበባ ማስተር ፕላንና የኦሮምያ አርሶአደሮች መፈናቀል ጉዳይ በፃፍኩት ላይ “የኦሮሞ ተማሪዎች ዓመፅ ከብሄር አንፃር አትየው፤ መታየት ካለበት አርሶአደሮቹ ከቀያቸው ካለመፈናቀል መብት አንፃር ነው” የሚል አስተያየት ደርሶኛል። እኔም ይሄን ጉዳይ በቅርበት ከማውቀው የመቐለ እንደርታ አርሶአደሮች ልምድ አንፃር ልየው ይፈቀድልኝ።

በመቐለ የከተማ ዕድገት ፕላን መሰረት አንዳንድ በከተማው ዙርያ የሚገኙ የገጠር መንደሮች ወደ መቐለ ከተማ ይገባሉ። ይህንን ዉሳኔ ባከባቢው አርሶአደሮች ከፍተኛ ተቃውሞ አጋጥሞታል። አርሶአደሮች የተቃውሞ ሰልፍ ለማካሄድ ሞክረዋል። የክልል ፖሊስ፣ የፌደራል ፖሊስ እንዲሁም የመከላከያ ሰራዊት አባላት ጣልቃ ገብተው የኃይል እርምጃ ወስደው ሰልፈኞቹን ደብድበው፣ አስረው፣ ገድለው ዓመፁ ለግዜው አስቁመውታል። ጥያቄው ግን እስካሁን ድረስ አለ። በዚህ ምክንያት ያከባቢው አርሶአደሮች የመንግስት አገልግሎት ተነፍገዋል። አርሶአደሮቹም ከመንግስት ጋር ላለመተባበር አድመዋል። ለምሳሌ የእግሪሐሪባ አርሶአደሮች ልጆች የመማር መብታቸው ተነፍጓል። የነዚህ አርሶአደሮች ልጆች ለምን እንዳይማሩ ተከለከሉ? ወላጆቻቸው መሬታቸው ወደ ከተማ መግባቱ በመቃወማቸው ምክንያት ነው። የትግራይ ክልል ባለስልጣናት “የወላጆቻቹ መሬት የከተማ እንዲሆን ካልፈቀዱ እናንተ ህፃናት እዚሁ ትምህርትቤት አትማሩም። ምክንያቱም ይሄ ትምህርትቤት የከተማ ሆኗል” አሏቸው። እናም እስካሁን ድረስ እነኚህ ልጆች የመማር መብታቸው እንደተነፈጉ ነው።

“የገጠር መሬት ወደ ከተማ ሲገባ ለምን ይህን ያህል ተቃውሞ ይነሳበታል?” የሚል ጥያቄ መነሳቱ ተገቢ ነው። ከተማ ማደግ አለበት። ከተማ ሲያድግ በዙርያው ወዳለ የገጠር መንደር ይሰፋል። ግን ለምን አርሶአደሮች አምርረው ይቃወሙታል?

(አንደኛ) አርሶአደሮች ከቀያቸው መፈናቀል አይፈልጉም። ለመሬታቸው ልዩ ፍቅር አላቸው። የያለ መፈናቀል መብትም አላቸው (በመርህ ደረጃ)። አንድን አርሶአደር ያለፍቃዱ ከቀዩ መፈናቀል የለበትም። ግን መንግስት በኃይል ያፈናቅላቸዋል። መንግስት በአንድ በኩል “አርሶአደሮች መሬት ከተሰጣቸው ሽጠው ከቀያቸው ይፈናቀላሉ፣ ስለዚህ መሬት ሊሰጣቸው አይገባም” በሚል ስሌት መሬት የመንግስት አድርጎታል። በኢትዮጵያ ታሪክ አርሶአደሮች ከቀያቸው የሚፈናቀሉ በኃይል እንጂ በፍቃዳቸው አይደለም። በዘመነ መሳፍንት ግዜ አርሶአደሮች መሬት አልባ ጭሰኛ የሆኑ በኃይል እንጂ በፍቃዳቸው አልነበረም። አሁንም በመንግስት ትእዛዝ እንጂ በፍላጎቱ ከቀዩ የሚፈናቀል የለም። ስለዚህ ተቃውሞው ከቀያቸው ላለመፈናቀል የሚያደርጉት ትግል ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በር ያስገባል በር ያስወጣል ወዴት ያስገባል ወዴት ያስወጣል - ምትኩ አዲሱ

ግን አርሶአድሮች ከቀያቸው ያለመፈናቀል መብት ካላቸው ለምን ወደ ተቃውሞና ዓመፅ ይሄዳሉ? አርሶአደሮች መፈናቀል አይፈልጉም። መንግስት በኃይል ከቀያቸው እንዲፈናቀሉ ያስገድዳቸዋል። መንግስት እንዲፈናቀሉ ሲያስገድዳቸው ለምን አቤት አይሉም? አቤት ለማለት’ኮ ገለልተኛ የፍትሕ አካላት መኖር አለባቸው። የፍትሕ አካላት ሲኖሩ ደግሞ የያለመፈናቀል መብት በሕግ የተደነገገ መሆን አለበት። ከመሬት የያለመፈናቀል መብት በሕግ የተደነገገ እንዲሆን መሬት የዜጎች መሆን አለበት።

አሁን በኢህአዴግ ሕገመንግስት መሰረት ዜጎች መሬት ተከራይተው የመጠቀም መብት እንጂ የመሬት ባለቤት የመሆን መብት የላቸውም። መሬት የዜጎች ሳይሆን የመንግስት ነው። ስለዚህ ዜጎች መሬት የመከራየት (ሊዝ የመሬት ኪራይ መሆኑ ነው) መብት አላቸው። ባለቤትነቱ ግን የመንግስት ነው። ስለዚህ አንድ ተካራይ ከተከራየሁት ቤት (መሬት) መልቀቅ (መነሳት) የለብኝም ብሎ መከራከር አይችልም። ተግባሩ ግን መቃወም ይችላል።

እናም አርሶአደሮቹ ከመሬታችን አንፈናቀልም ሲሉ መሬትኮ የመንግስት እንጂ የናንተ አይደለም፤ ስለዚህ ትነሳላቹ ይሏቸዋል። አርሶአደሮቹም “መሬትኮ የመንግስት መሆን የለበትም” ሲሉ “መሬት የመንግስት ካልሆነማ መሬታችሁን ሽጣቹ መሬት አልባ ትሆናላቹ። መሬት በጥቂት ሃብታሞች እጅ ይገባል” የሚል መልስ ይሰጣቸዋል። መሬታቹ ሌሎች ሊወስዱት ስለሚችሉ ቀድመን እኛ ወስደነዋል ዓይነት ማለት ነው።

ስለዚህ አርሶአደሮቹ መሬታችን አንሰጥም ብለው በሕግ ፊት እንዳይከራከሩ ሕጉ አይደግፋቸውም። ምክንያቱም ሕጉ መሬት ለዜጎች ሳይሆን ለመንግስት ነው የሰጠው። ስለዚህ የሕግ ድጋፍ የላቸውም። የህግ ድጋፍ ባይኖራቸው እንኳ ተግባሩ ትክክል አለመሆኑ ያውቃሉ። እናም ይቃወሙታል። መቃወም ሳይፈቀድላቸው ሲቀር ያምፃሉ። ሲያምፁ በኃይል ይደፈጠጣሉ። እናም አማራጭ ስለሌላቸው አኩርፈው ይቀመጣሉ። በኦሮምያ ግን ዓመፁን አቀጣጠሉት።

ስለዚህ የችግሩ መንስኤ የመንግስት የተሳሳተ የመሬት ፖሊሲ ነው። መሬት የህዝብ (የዜጎች) ቢሆን ኑሮ አርሶአድሮች ከመሬታቸው ያለመፈናቀል መብታቸው በሕግ ይከበርላቸው ነበር (ገለልተኛ የዳኝነት ስርዓት ሲኖር ማለት ነው)። ምክንያቱም መሬት የአርሶአደሮች ከሆነ ማንም ከቀያቸው እንዲፈናቀሉ አያስገድዳቸውም ነበር። መሬት ለራሹ ከተሰጠ አርሶአደሮች ያለ ፍቃዳቸው ከመሬታቸው (ከቀያቸው) አይፈናቀሉም። ካልተፈናቀሉ ደግሞ መሬታችን ወደ ከተማ ይገባል ብለው ዓመፅ አይቀሰቅሱም ነበር። ስለዚህ የችግሩ ምክንያት የመሬት ፖሊሲው ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  አወዛጋቢ የተባሉት ፓትሪያርክ አቡነ ማቲያስ ለምኒልክ መጽሔት ምን ብለው ነበር?

(ሁለት) አስፈላጊ ሁኖ ሲገኝ አርሶአደሮች የሚፈናቀሉበት ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል። ይሄ የሚሆነው ግን አርሶአደሮችን በማሳመን (በፍቃዳቸው) ሁኖ ለመሬታቸው ተገቢ ካሳ (ራሳቸው በጠየቁት መሰረት) ሊከፈላቸው ይገባል። በመቐለ ዙርያ ያሉ አርሶአደሮች ግን ከመሬታቸው ተፈናቅለው ሲያበቁ በቂ ካሳም አይሰጣቸውም። የካሳ መጠን የሚወስነው መንግስት ነው (ካሳ የማያገኙም አሉ)። መሬታቸው አጥተው በቂ ካሳ ካላገኙ ከዚህ የባሰ መነቀል አለንዴ? ይህ ሲሆን እንዴት አይቃወሙም? የኦሮምያ ጉዳይም ተመሳሳይ ስጋት ሊጭር ይችላል።

(ሦስት) “መሬታቹ የከተማ አካል ሁኗል” በሚል ምክንያት አርሶአድሮች ከቀያቸው ያለፍቃዳቸውና ያለ በቂ ካሳ ከተፈናቀሉ በኋላ መሬቱ በሙስና ለሙሰኞች ይቸበቸባል። መሬት የመንግስት በመሆኑ እንዲሁም መንግስትና ገዥው ፓርቲ በመቀላቀላቸው ምክንያት የገዥው ፓርቲ ጥቂት ካድሬዎች መንግስት ሁነዋልና ከአርሶአደሮች የተረከቡትን መሬት እንደፈለጉ ለፈለጉትን ባለሃብት ይሸጡታል። መሬት ከአርሶአደሮች ነጥቀው ለራሳቸው ያደርጉታል። ወይ ይሸጡታል ወይም ደግሞ ህንፃ ያቆሙለታል። መሬት አይሸጥም አይለወጥም እየተባለ የመንግስት አካላት ግን እንደፈለጉ ይሸጡታል፣ ይለውጡታል። መሬት እንዳይሸጥ እንዳይለውጥ የተከለከለ አርሶአደሮቹ እንጂ መንግስትማ የፈለገ ያደርጋል። እናም ከአርሶአደሮች የተነጠቀ መሬት ለግል ሃብታሞች እየተሸጠ እየተመለከቱ እንዴት አይቃወሙም? እንዴት ለመሬታቸው አያምፁም? በኦሮምያም በእንደርታ የተተገበረውን እንደማይደረግ ምን ማረጋገጫ አለን?
ስለዚህ የመቐለ እንደርታ አጀንዳ በመውሰድ የአዲስ አበባ ኦሮምያ ጉዳይ መገመት ይቻላል። ጉዳዩ ከመንግስት የመሬት ፖሊሲ ጋር ይገናኛል።

“የኦሮምያ ተቃውሞ ፖለቲካዊ አጀንዳ አለው” ካላችሁኝም ያው ፖለቲካዊ ተልእኮ ሊኖረው ይችላል። ፖለቲካዊ ተልእኮ ያለው ዓመፅ ሲቀሰቀስምኮ ያለው ፖለቲካዊ ሁኔታ መሰረት አድርጎ ነው። ፖለቲካዊ ዓመፅ የሚቀሰቀሰው ጭቆና ሲኖር ነው። የፍትሕ እጦት ሲኖር ነው። የዴሞክራሲ እጦት ሲኖር ነው። ነፃነት ሲታፈን ነው። ስለዚህ ዓመፁ ፖለቲካዊ አጀንዳ ያለው ከሆነም ያው መንስኤው ደግሞ የኢህአዴግ ጨቋኝ አገዛዝ መሆኑ ነው። ምክንያቱም በሀገሪቱ ፍትሕ ቢሰፍን ኑሮ ዜጎች ፖለቲካዊ አጀንዳ ይዘው አያምፁም ነበርና ነው።
የፖለቲካዊ ዓመፅ መንስኤ ጭቆና ቢሆንም ዓመፅ ግን የጭቆና ነፀብራቅ እንጂ ጭቆና የሚወገድበት ትክክለኛ ስትራተጂ አይደለም። በዓመፅ ጨቋኞችን ከስልጣን ማባረር ይቻል ይሆናል። በዓመፅ ጭቆናን ማስወገድ ግን አይቻልም። ጭቆና የሚወገደው ዴሞክራሲ በማስፈን ነው። በዓመፅ የሚገነባ ዴሞክራሲ ደግሞ የለም። የዴሞክራሲ መንገድ ዴሞክራሲ ነው። ዓመፅ የሰው ህይወትና ንብረት ይበላል። በዓመፁ ምክንያት ህይወታቸው ላጡ ተማሪዎች ጥልቅ ሐዘን ይሰማኛል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  Ethiopian-American author Dinaw Mengestu and the aura of estrangemen

13 Comments

  1. በጣም ብዙ ቁምነገር አዘል መልእክቶችን ማንበብ ችያለሁ፣ እኔን በጣም ያስደሰተኝ ግን ”በአመጽ ዲሞክራሲያዊ መንግስት መገንባት አይቻልም” የሚለው ነዉ

  2. Dear Abraha,

    You and TPLF/Woyane are the same except the way of expression. You tried to explain politely while TPLF answered the question with gun. Your final paragraph appears like objecting and disgracing public revolt and discontent against dictators. Is it to defend and rescue the regime?

  3. As long as the land is in ethiopia the government can demarcate in any way .
    The public need to obey to the land policy.

  4. I think the way you write your expression is modern oppressor. You seems to oppose but you never opposed. The case of Oromia is different from that of Mekele. If Mekele includes surrounding area, it within the same region. But When Addis Ababa includes surrounding region, do you know that an Oromo employee working in Oromia regioanl offices cannot get land from Addis Ababa, leave alone the farmer. It is totally different. What happened to Farmers in Laga Tafo and Sendafo area? What about farmers in Sebeta area? Farmers in Burayu area? Who was beneficiary? Few corrupted OPDO leaders (here I say few because I donot believe that all members of one organization are corrupted) Rather I judge inidividually). The farmers were just thrown away like old and useless equipments. In addition, the article that talks about special benefits for Oromia region from Addis Ababa region is only polluted waste, not a single coin as far I know.

  5. አንባብያን ሆይ፣ ቤቶቹንሞ ተመልከቱ፣

    The “Ästhetik” of MLLT, worst than that of Ceausescu ze-ሮማንያ !

    “መንፈሰ” ቅል Azeb Golla-Asres aka Elena Ceausescu !

    ኢትዮጵያ ሆይ ምህረቱን ያውርድልሽ……………………!

  6. Girmay – What exactly is wrong with Abrah’s article? Who said TPLF is not doing wrong? What he is saying is simply anarchy can’t create democracy. Indeed, we are witnessing the Arab spring becoming the Arab Winter. Do you think Libya is better off now than during Gadaffi’? How about Egypt, is Sisi better than Mobark? The answer is no! Is Syria better now than before the civil war? Democracy is a slow process. It can not be achieved by Gun toting and killing of Citizens. Transition to Democracy must be a negotiated process. Violent over throw of the old and replacing with new, always creates revenge and animosity which hampers the democratic process. TPLF must stop harassing, persecuting, the killing of innocent people. If the Oromo students want their cry and struggle to bear any fruit, it must be inclusive of everyone. Only then, their cause will be justified and wholesome.

  7. There is a saying in Amharic that goes like ” a kid whose mother went to market and another one whose mother died both cry equally”. GIZE YALFAL, BESEW DEM BATALAGIT TIRU NEW!!

  8. The so called OROMO student protest is totally politically motivated.If is is about farmers displacement where have you been when thousands displaced is the other part of the region when TPLF/EPRDF sold the land to Saudi and foreign investors. Is that OKEY when other displaced but not OKEY when Addis Expands. I am sick of this double standard and Narrow minded Tribalism.I would say the TPLF/EPRDF ethnic politics start producing fruit this time Against TPLF/EPRDF itself..

  9. No one can prevent the expansion of Addis ababa.A.A will expand to any direction.It is Shame opposing once city growth ln the 21st century with a tribalism attitude.

  10. Mr Abrha you are trying to compare two unparallel things. The question of the people living in the surrounding areas of Mekele seems the question of land rights and they demand compensation and which is their right

    However these OLF students are protesting the expansion of Addis Abeba categorically and in their protest they shout not even compensation for the farmers rather they shout about OROMIYA for Oromos, the imprisonment of Teddy Afro and the removal of The statue of Menilik and these questions are part of the illusions of OLF plan of creating independent OROMIYA and never forget about the money being channeled through the likes of Jawar Mohammed from Egypt

    Awek awek siluh tesetaleh

  11. Oromia regional state pays a tax for offices in Addis Abeba, Oromo farmers don’t have any chance to compute and get housing or proper compensation. Addis was a curse for us. No way, if the country can not benefit our people, it is right that u all should fail.

    Ethiopia is a hell for Oromo.

  12. “የአራቱ ሃዋርያት በትግራይ ጉብኝት አነጋጋሪ ሆኗል

    ከአስገደ ገ/ስላሴ፣ መቐለ

    የለውጥ ሃዋርያቱ እንማን ነበሩ
    ሃዋርያቱ ስዩም መስፍን ከ36 አመት በላይ የህ.ዋ.ሃ.ት እና የመንግስት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የነበሩ፣

    አቶ አባይ ፀሃዬ እስከ 1982 ዓ/ም ድረስ የማለሊት ሊቀመንበር የነበሩ አሁን በሚኒስተርነት ማእረግ አማካሪ ሆነዉ የሚሰሩ፣

    ስብሃት ነጋ እስከ 1982 ዓ/ምድረስ የህዋሃት ሊቀመንበር የነበሩና ከዛም በኃላ የኢፈርት ቦርድ ሊቀመንበር አሁን በመንግስት ባለስልጣ

    ፀጋይ በርሀ ቀደም ሲል የትግራይ ክልል በምክትል ሊቀ መንበር እስከ ሊቀመንበር ሆነዉ የነበሩ ናቸዉ።”

    Is this action:ከልብ ከዛውል ወደ ጳውሎስነት፣ ወይንስ እንደተለመደው ጳውሎስ መስሎ ዛውልነት ?

  13. Abraha, In the case of Woyane, the only path to democracy is violence and blood shed; Woyane is an exception to the rule. The biggest difference between Woyane and other oppressors around the world is that Woyane is dismantling the country that it was suppose to unite. Its members are half Eritrean and Ethiopian Bandas. The leaders (like Meles Zenawi) are childrens of Bandas who continue the legacy of betrayal of the country that fed them, just like their parents. ONLY FORCE AND POWER WILL DESTROY WOYANE. Abraha, your cover is exposed and we know you are an undercover puppet of Woyane.

Comments are closed.

Share