“አማራ ከኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን፣ ከአፍሪካም እጅግ ድሃ ሕዝብ ነው”

ከድንበሩ ስዩም

መቀመጫውን ኳታር ያደረገው አልጀዚራ እየተባለ የሚጠራው ቴሌቪዥን ጣቢያ በኢትዮጵያ ላይ ከሰሞኑ አንድ ዶክመንተሪ ፊልም አቅርቦ ነበር። ፊልሙ የሚያተኩረው በሰሜን ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኘው በአማራ ክልል እና በውስጡ ያሉት ነዋሪዎች በዓይን ሕመም ምክንያት ለዓይነ-ስውርነት እንዴት እንደሚጋለጡ እና ከዚሁ ጋር ተያይዞ ደግሞ በዘመቻ መልክ ወደ ክልሉ ተጉዘው በነፃ የዓይን ሕክምና ስለሚሰጡት ዶክተሮችም የበጎ ተግባር ሥራ ነው። ዶክተሮቹ የበርካታ ሰዎችን ብርሃን መልሰው ሲያመጡትም ፊልሙ ያሳያል። ይህ የዓይነ-ስውርነት በሽታ በክልሉ ውስጥ እጅግ ከመስፋፋቱም በላይ በአጭሩ መፍትሄ ሳይሰጠው ለረጅም ዓመታት ተንሰራፍቶ መቆየቱም በፊልሙ ውስጥ ይተረካል። የዚሁ ክልል ነዋሪዎች የሆኑትም ‘የአማራ’ ህዝቦች ጓዳ እና የኑሮ ደረጃቸውንም የአልጀዚራ ካሜራዎች ለዓለም እያሳዩት ነበር። ከድህነት ጠርዝ በታች የሚኖሩ ሰዎችን ገመና ካሜራዎቹ አልሸሸጉትም ድህነትን ባይተርኩትም እያሳዩን ነበር። ነገር ግን ተረኩት። ተራኪዋም እንዲህ አለች፡- “አማራ ከኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን፣ ከአፍሪካም እጅግ ድሃ ሕዝብ ነው” በማለት ተናገረች። ነገሩን እንደ ኢትዮጵያዊነት ስንወስደው ልብ ይነካል። ያደማል። ያሳፍራል። ያበሽቃል። ግን ደግሞ በጥሞና ስናስበው ጉዳዩ ያልተጋነነ እውነት ሆኖ እናገኘዋለን። ምክንያቱም አበው ማየት ማመን ነው ስለሚሉ፣ የአልጀዚራ ካሜራዎች እውነቱን እያሳዩን ነበር።

ግን የአማራ ሕዝብ የአፍሪካ ድሃ ነው? የዚህ ሕዝብ ድሕነት እንዴትስ እዚህ ደረጃ ላይ ደረሰ? ቀድሞ እንዴት ነበር? አሁን ምን ሆነ? ወደፊትስ ምን ይሆናል? ብዙ ጥያቄዎችን እያነሳሳን መጫወት እንችላለን። ፊልሙ የለኮሰው የሃሳብ ክብሪት በቀላሉ የሚታለፍ አይደለም።

የአልጄዚራ ዶክመንተሪ በዓይን ሞራ ግርዶሽ እና ተያያዥነት ባላቸው የዓይን ሕመሞች ዙሪያ በጐ ፈቃደኛ ሐኪሞች የሚሰጡትን የዘመቻ ሕክምና እና የሕዝቡንም ኑሮ እያሳየ ነበር። የዓይን የሞራ ግርዶሻቸውን ለማስገፈፍ ከወጣት እስከ አዛውንትነት የእድሜ ክልል ውስጥ ያሉት ነዋሪዎች ከ20 ኪሎ ሜትር በላይ በእግራቸው ተጉዘው ሐኪሞቹ ያሉበት ቦታ ሲደርሱና ሕክምናውን ሲያገኙም ይታያል። ለረጅም ዓመታት ብርሃናቸውን አጥተው በጨለማ ሕይወት ውስጥ ሲዳክሩ የነበሩ ሰዎች የብርሃን ፀዳል ሲያዩ የሚፈጠረው ስሜት ልብን ይነካል። አንዳንዱን ደግሞ ሕክምና ቦታም ቢደርስ ዓይኑ በቀላሉ ወደማየት ደረጃ እንደማይደርስና ዓይነ-ስውርነቱ እንደሚቀጥል ሲነገረው ማየትም ልብን ይነካል። ጉዳዩ እጅግ ስሜታዊ ነው። ታዲያ ከዚህ ስሜታዊ ጉዳይ ውስጥ ተፈልቅቆ የሚወጣው ማጠንጠኛ ደግሞ ድህነት ነው።

የዓይነ-ስውርነት ሕመም በስፋት ከተንሰራፋባቸው ክልሎች ዋነኛው የአማራ ክልል ነው። በተለይ ደግሞ ጐጃም ውስጥ ጉዳዩ አሳሳቢ ነው። እኔ ራሴ የዚህ ፅሁፍ አቅራቢ በአንድ ወቅት ጐጃም ውስጥ የሚገኙ ታላላቅ አድባራትና ገዳማትን ዶክመንተሪ ፊልም ለመስራት በምዘዋወርበት ወቅት በርካታ ሕፃናት፣ ወጣቶችና አዛውንቶች ዓይነ-ስውር ሆነው በማየቴ በእጅጉ ደንግጬ ነበር። ለምሳሌ ዲማ ጊዮርጊስ ተብሎ በሚታወቀው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስትያን የቅኔ እና የሃይማኖት ማስተማሪያ ገዳም ውስጥ ያየሁት ጉዳይ ለዘላለሙ ከህሊናዬ አይጠፋም። በዚያ ገዳም ውስጥ በርካታ ወጣት ተማሪዎች አሉ። ከእነዚህ ተማሪዎች ውስጥ ሲሶው ዓይነ-ስውራን ናቸው። ይሄ ብቻም አይደለም። የእነዚህ ተማሪዎች መምህርት የሆኑት መነኩሴም ዓይነ-ስውር ናቸው። መምህርታቸውም ሆኑ ተማሪዎቹ ዓይነ-ስውራን ነበሩ። ከዚህ በላይ ልብ የሚነካ ነገር የለም። አልጀዚራ ይህን ጉዳይ ግን አልሰራውም።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የኢትዮጵያ ሕዝብ ንቃ!ማኅበራዊ እሴትህን ጠብቅ፤ “ፖለቲከኛን ያመነ ጉም የዘገነ!” - በገ/ክርስቶስ ዓባይ       

በወቅቱ የዚህን የዲማ ጊዮርጊስን ጉዳይ በተመለከተ የደብሩን ኃላፊ ጠይቄያቸው ነበር። “ለምንድን ነው ተማሪዎቹም መምህርታቸውም ዓይነ-ስውራን የሆኑት?” አልኳቸው። የደብሩ ኃላፊም ሲመልሱ፤ “ለአብነት (ለቆሎ) ተማሪዎች እንደ ድሮ ምግብ የሚሰጣቸው የለም። ዞረው ለምነው የሚበሉትን አግኝተው መማር አልቻሉም። ስለዚህ ዓይን ያላቸው (ማየት የሚችሉት) ወደ አዲስ አበባ እየሄዱ ሎተሪ ይሸጣሉ። ማየት የማይችሉት እነዚህ ደግሞ የት ይሒዱ? እዚሁ ሆነው ከነችግራቸው እንደምንም ይማራሉ። ዓይነ-ስውራኑ በከፍተኛ ችግር ውስጥ ናቸው” እያሉኝ የደብሩ ኃላፊ አጫወቱኝ።

ጐጃም ውስጥ ለምንድን ነው ዓይነ-ስውርነት የተስፋፋው? ሕፃናት ሳይቀሩ ዓይነ-ስውራን ናቸው። ይህ ጉዳይ ሊመረመር እና መንስኤው ሊታወቅ ግድ ይላል።

አልጀዚራ ዓይነ-ስውርነትን መሠረት አድርጐ “አማራ ከኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን፣ ከአፍሪካም እጅግ ድሃ ሕዝብ ነው” ብሎ ተናገረ። ይህን አባባል ከሰማ ብዙ ነገር አሰብኩ። እኔ የአማራ ክልል ተወላጅ አይደለሁም። ግን ደግሞ አማራ ኢትዮጵያዊ ነው። ያውም ብዙ ታሪክ ያለው። ብዙ ሀብት ያለው። ባሕል ያለው። ማንነት ያለው። ለሀገሩ ቤዛ የሆነ። ብዙ ነገር መጠቃቀስ ይቻላል። ታዲያ ይህ ህዝብ የአፍሪካ ድሃ ህዝብ ነው ሲባል እንደ ኢትዮጵያዊነት ሁላችንንም ጉዳዩ የሚቆረቁረን ይመስለኛል። ከዚህ ከአልጀዚራ አባባል የሚደሰት ኢትዮጵያዊ ያለ አይመስለኝም። ምክንያቱም ጉዳዩ የአማራ ሕዝብ ብቻ አይደለም። የመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ጉዳይ ነው።

የአማራ ክልል የአፍሪካ የቋንቋ ማዕከል ነው። በዚህ ክልል ውስጥ ተወልዶ እና አድጐ የመላው ኢትዮጵያ ቋንቋ የሆነው አማርኛ ከአፍሪካ ውስጥ የራሱ ፊደል ያለው ብቸኛ ቋንቋ ነው። በ1950ዎቹ ውስጥ በተሰራ ጥናት የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ መሆን አለበት እየተባለ ሁሉ የሃሳብ ክርክር ቀርቦ ተቀባይነት አግኝቶ ነበር። ቋንቋው ከመግባቢያነት አልፎ እጅግ የዳበረ የሥነ-ፅሁፍ ቋንቋ ነው። የትልልቅ ፍልስፍናዎችና አመለካከቶች መገለጫም ነው። እናም ይሄ የአፍሪካ ድሃ ሕዝብ፣ ለአፍሪካ ቋንቋንና ሥነ-ጽሁፍን ያበረከተ ነው።

የአማራ ክልል በአፍሪካ ውስጥ ቁጥር አንድ የሆነ የታሪክና የቅርስ ማዕከል ነው። ለምሳሌ የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና የባሕል ድርጅት /ዩኔስኮ/ የዓለም ድንቅዬ ቅርሶችን እያለ የሚያቆለጳጵሳቸው አያሌ ጉዳዮች መቀመጫቸው እዚሁ አማራ ክልል ውስጥ ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከይሲነት በመልካሙ መደመር ላይ እያሴረ ነው። - መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ

በሰው ልጅ የኪነ-ሕንፃ ምርምር እና ጥናት ውስጥ እስከ አሁን ድረስ የአሰራራቸው ምስጢር ምን እንደሆነ የማይታወቁት የቅዱስ ላሊበላ ፍልፍል አብያተ-ክርስትያናት የአፍሪካ ቁጥር አንድ ቅርሶች ናቸው።

የ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የዓለም የሥልጣኔ ማዕከል ናት እየተባለች በታሪክ ተመራማሪዎች ዘንድ ዘወትር የምትጠቀሰው የጐንደር ከተማ እና በውስጧ ሰብስባ የያዘችው አብያተ-መንግሥታትና አብያተ-ክርስትያናት የኪነ-ሕንፃ አሰራር የዓለም ድንቅዬ ቅርሶች ናቸው ብሎ የመዘገበው ይሄው የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት ነው። ጐንደር በ17ኛውና በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ላይ በጥበብና በስልጣኔ ገናና ሆና በምትጠራበት ወቅት መላው አፍሪካ በባርነት ቀንበር ውስጥ ይዳክር ነበር። በወቅቱ ጥቁር ሕዝቦች ሁሉ በቅኝ ግዛት ተስፋፊዎች መዳፍ ስር ገብተዋል። በጭቆና ውስጥ ለወደቁ ለጥቁር ሕዝቦች በመሉ የነፃነት አርአያ ሆኖ የኖረው ይህ ሕዝብ እና ክልል ዛሬ የአፍሪካ ድሃ ሕዝብ ነው ሲባል ይቆረቁራል። ያማል። ያሳስባል። …. አሜሪካ በእንግሊዞች የቅኝ አገዛዝ ስር ስትማቅቅ ጐንደርን የኢትዮጵያ መዲና አድርጐ ይኖር የበረው አስተዳደር የነፃነት ተምሳሌት ነበር። ዛሬ የአፍሪካ ድሃ ሕዝብ እየተባለ ነው።

በሥነ-ጽሑፍ ዓለም ውስጥም ከአፍሪካ አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃም ቢሆን 12 ጥንታዊ መፃህፍትን የዓለም ድንቅዬ ቅርሶች ሆነው የተመዘገቡት በዚሁ ክልል የተፃፉና የተገኙ ናቸው።

በሐይማኖት፣ በባሕልና በታሪካዊ እሴቶችም ቢሆን ክልሉ ያበረከተው አስተዋፅኦ ቀላል አይባልም። እንደውም አፍሪካዊ ለዛና ማንነት ያላቸው ጉዳዮችን በስፋት የምናገኝበት ክልል ነው። እጅግ በርካታ ገዳማትና አድባራት እንዲሁም ደግሞ በውስጣቸውም የጥቁር ሕዝቦች ሁሉ መኩሪያ የሆኑ ቅርሶችን የያዙ ናቸው። ከፍም ሲል ደግሞ የሰው ልጅ ሁሉ መመኪያ የሆኑ ሃይማኖታዊ ቅርሶችን በውስጡ ጠብቆ የኖረ ክልል ነው።

በቅርቡ ዩኔስኮ ከሃይማኖታዊ ክብረ-በአሎች አንዱ የሆነውን የመስቀል አውደዓመትን የዓለም ቅርስ አድርጐ መዝግቦታል። ታዲያ የመስቀል በዓልን እጅግ ብርቅ ካደረጉት ጉዳዮች አንዱ እየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ግማደ መስቀል እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይም በአማራ ክልል ግሸን ደብረ-ከርቤ ውስጥ መኖሩ ነው። ከዚህም አልፎ በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተደጋግሞ የሚጠቀሰው ግዮን /የአባይ ወንዝ/ በወርድና በቁመት ተገማሽሮ የሚገኝበት ቦታ ነው። አባይ የጣና ሐይቅ ማህፀን ውስጥ ገብቶ የሚወጣውም ከዚህ ክልል ነው። ጣና ሐይቅ ላይም 37 ደሴቶች ኖረው ሁሉም ማለት ይቻላል እጅግ ድንቅዬ አብያተ-ክርስትያናት ያሏቸው ናቸው። ያውም ከበርካታ ልዩ ልዩ ቅርሶች ጋር። ታዲያ ይህ ክልል አሁን የአፍሪካ እጅግ ድሃ ህዝቦች መኖሪያ ነው ሲባል ያሳፍራል።

ተጨማሪ ያንብቡ:   ከነ “ጃሥ“ከእሥር መፈታት ጀርባ ታላቅ ሤራ አለ ። ሲና ዘ ሙሴ  

የአማራ ህዝብ ከሌሎቹ የኢትዮጵያ ህዝቦች ጋር በመሆን ሀገሩ ኢትዮጵያን ከባዕዳን ወረራ ጠብቆ የኖረ ሀገሪቱ በቅኝ ገዢዎች መዳፍ እንዳትወድቅ መስዋዕትነትን የከፈለ ህዝብ ነው። “የነፃነት – መስዋዕት” በመሆን ሀገሩን አስከብሮ የኖረ የታሪክ ባለቤት ነው። ግን የአፍሪካ ቁጥር አንድ ድሃ እየተባለ ነው።

አማራ ክልል በርካታ የሀገሪቱን ምሁራን ያፈራም ክልል ነው። በሳይንስ፣ በፍልስፍና፣ በታሪክ፣ በቋንቋ እና በሌሎችም የትምህርት መስኮች ውስጥ አንቱ የተባሉ ሰዎችን ያፈራና እያፈራም የሚገኝ ነው። ግን ድሃ ህዝብ ነው። ኧረ ሌሎችንም ጉዳዮች እያነሳሳን መጫወት እንችላለን። ቢሆንም እዚህ ላይ ቆም እናድርገውና ድህነት ምንድን ነው? ለምንስ የአፍሪካ ድሃ ሕዝብ ሆነ የሚለውን ሁላችንም መልስ ለመስጠት መሞከር አለብን።

ይህ ሕዝብ በአንዳንድ መስመር በሳቱ ግለሰቦችና ተቋማት አማካይነት ‘አድሃሪ’፣ ‘ትምክተኛ’፣ ‘ነፍጠኛ’ ወዘተ እየተባለ የራሱ ወገኖች በሆኑ ኢትዮጵያዊያንም ሲንጓጠጥ እና ሲዘለፍ የኖረም ነው። ይሄ ደግሞ ማኅበራዊ መሸማቀቅን ፈጥሮበታል። በእነዚህ ቅስም ሰባሪ ቃላት እንደልባቸው ሲዘልፉት የነበሩት ሰዎች አንድም ቀን ሲጠየቁ እና የሚናገሩትም ነገር ስህተት እንደሆነ በአደባባይ ተነግሯቸው አያውቅም። ይሄ ሲዘለፍ የኖረው ህዝብ አሁን ደግሞ የአፍሪካ ቁጥር አንድ ድሃ ሆኗል። ኦነግን የመሳሰሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የማሸማቀቁን ሚና በሰፊው ተጫውተውታል።

ሌላውና አንገብጋቢው ነገር ደግሞ የአማራ ህዝብ ራሱን መጠየቅ አለበት። የዚህ ሁሉ ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስ፣ ማንነት ባለቤት ሆኜ ለምን ድሃ ሆንኩ ብሎ መጠየቅ ያለበትም ወቅት ነው። በርግጥ ይህን ጥያቄ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊጠይቀው የሚገባ ነው። ለምን ድሃ ሆንን?

አልጀዚራ የአማራን ህዝብ የአፍሪካ ቁጥር አንድ ድሃ ነው ቢለው ያበሽቃል እንጂ ሀሰት አይደለም። የአማራ ህዝብ በተለያዩ ከተሞች ውስጥ በልመና የሚተዳደር ነው። በሰው ቤት ሰራተኝነት የሚያገለግሉት የአማራ ተወላጆች ናቸው። ከቦታ ቦታ የሚሰደዱትም የሚፈናቀሉትም እነርሱ ናቸው። ግን እንደ አንድ ህዝብ የተሻለ ህዝብ እንዲሆን ከማን ምን ይጠበቃል የሚለው ጥያቄም መመለስ አለበት።

በባሕል፣ በታሪክ፣ በቅርስ ወዘተ መበልፀግ እንዴት ከድህነት ሊያወጣን አልቻለም ብሎ ማሰብም ተገቢ ነው። በአጠቃላይ ሲታይ ኢትዮጵያ ከድህነት ወለል በታች ናት እየተባለ በሚነገርበት ሁኔታ ውስጥ የአማራ ህዝብ ደግሞ የድህነት ጣሪያው የጐላ መሆኑን አልጀዚራ ተናግሯል፤ ስለዚህ ቆም ብለን ረጅሙን ጉዞ ከአሁኑ አሻግረን እያየን መጪውን ጊዜ የተሻለ ለማድረግ ብዙ መጣር አለብን።

9 Comments

  1. It is a realistic documentary film that exposes the secrates, propagandas & hidden agendas of the so called Ethiopian government/ a maphia group led by TPLF/!

  2. We all know that Amhara and all of us are suffering in poverty. Many ethic groups and educated people are more interested in bringing suffer in another part of Ethiopia by thinking imperialist instead of helping their own people. The poverty in Ethipia never started today but from all previous regime. Now it is getting worse as population explode.

    This is the same for all ethnics in Ethiopia, but worse for educated Amhara. Elites need to think local problems like what u mentioned before they baffale about national issue.

  3. I feel so very very sory!!! the people who was blueprint for african & world civilization,now african & world poorest nation!! what is the matter? it is weyane(ወያኔ), who robe,steal,destroy the wealth of the nation! እባካችሁ አማራዊያን ከዚህ ውርደት ለመላቀቅ መላ በሉ::

  4. as (((amhara …realy I am)))) I cant regret we are Problem makers….realy some times I assumed being an amhara,,,,,like wondafrash of nurenberg from germany….(((ye brsheleko /derg Kadrie..)))please observe how he sugestes,,,we know each other

  5. I am surprised by the stupid question raised by the writer of this article which says WHY AMHARA people remained poor???? The answer is AMHARA people were denied of INFRUSTURAL DEVELOPMENT especially the People of GOJJAM by the successive regimes who ruled Ethiopia despite they are one of the most hard working people in the world , they are the poorest people in the world

    The regimes ruled Ethiopia have been diverting development projects to OROMIYA and to the SOuthern part of the country ignoring intentionally the AMHARA region

    For instance There has been only one Textile factory in Gojjam when WOYANE came to power and WOYANES always make the case of the presence of only one Flower Factory in TIGRAY now TIGRAY is industalized fast while GOjjam and the rest of the AMHARA region remained impoverished denied of development projects, factories and industries by the current regime which is diverting every development project to Tigray

    The people of AMHARA region work from dawn to dusk and the reasons for their poverty squarely put on The Regimes who rule Ethiopia from HAilesilassie to Woyane they neglect the region and focus on developing Other regions what is worse is these AMHARA people are blamed for everything went wrong in this country and are being used as a escape Goat and the suffering and the displacement of Amhara people intensified especially under Woyane who is even giving away their land to Benshangul, Sudan not to mention the fertile lands of north Gonder taken over by TPLF

    As if their poverty and suffering is not enough AMHARA people has ardent and very dangerous enemies like OLF, TPLF, SHBIA and individuals like TESFAYE GEBRE EBABB, SEBHAT Nega, Jawar Mohamad, Samora etc who are bent on exterminating Amharas from the surface of the earth and laying grounds for the future planned GENOCIDE on These poor people who are fighting for their survival

    The hate propaganda against Amharas by TPLF and OLF based on lies and fabrication is intensified and Non AMHARA people from north to south is being told Amharas are their historical enemies and according to a research by Alemseged Abay in his book IDENTITY JILT more than 80 percent of TIGRAY people believe AMHARA are their ardent historical enemies and the same is true for OROMOS

    The survival of AMHRA people is threatned from its core from his ardent enemies OLF TPLF yet the elites from Amhara chose to give a blind eye not even dare to speak and the truth except professor Getachew Haile

  6. It is a well known fact that the Amharas have been the prime target of genocide (depopulation) from the day one by TPLF and Co, helped by the West. Using different methods such as physical desturction (by force, by bullet), vaccination with AIDS, infectiing them with different types of diseases including Trachoma, Malaria, by starvation, by sterilization, displacing them from thier home and land, and preventing them from harvesting thier farm, and so on. The Amhara region has the highest infection rate of Trachoma in the world. It was not so before. It happened after TPLF came to power. It is deliberately done. You can read it in TPLF’s manifesto. Amhara stands in thier hit list.

  7. Ok, if you know that TPLF is destroying Amhara and our people has been the target of this Tigray organization for years, then why don’t you organize yourself? Why don’t you help Moresh?
    Stop talking. Just do something.

  8. ጸሐፊው እንደ አቀራረቡ ብዙ የሚያውቅና የሚነግረን ነገርም ያለው ይመስላል:: አንዳንድ ላይ ደግሞ ችግሩ በአንድ ነገድ ብቻ እንዳልሆን ይተርካል::እንዴ እኔ ነገሮች በፈለጉት መንገድ ሊመጡ እንደሚችሉ ይገባኛል::አደገኛው አመለካከት ግን በተለይ አሁን ገዥው መደብ እየዋዥቀ ባለበትና ድሕረ-ገጽ የሚያውኩ;በማናቸውም የመገናኛ ብዙሃን የሕዝብ ተቆርቁዋሪ መስለው በመግባት የጃሚንግ ሥራ የሚሰሩ የኮሙኒኬሽን ችግር የሚፈጥሩ ተማሪዎችን በማሰልጠን ያሰማራ ስለሆነ ይህ አይነቱ ጦማሪ የዚያ ተልእኮ ሠራዊት አባል ነው::አማራውን ለዚህ ያበቃውን <>መፍትሐእውም ቢሆን በእጃችን ስለሆነ ከአላሳከከን ላይ አትከኩን ሥለ ራሳችሁ የምትሉትን በሉ የአዛኝ ቅቤ አንጓች አትሁኑ::እንከባበር!! እሽ?ዘጠጣችሁን አቁሙ::
    dear dinberu syum I read your article carefully and you are writing offensive article against amahara people you are insulting amahara or trying to degrading amahara peopleyou shoould stop.

Comments are closed.

Share