ዘ-ሐበሻ

ቆንጆ ሴቶችን በሚገባ ለማፍቀር የሚያስችሉ 7ቱ ልዩ ልዩ የስህበት ህጎች

1. የምትፈልገውን እወቅ
በዓለም ላይ የብዙዎች ችግር የሚፈልጉትን አለማወቃቸው ነው፡፡ አንዳንዶች ደግሞ የሚፈልጉትን ለማወቅም ጭራሽ አይፈልጉም፡፡ ይህ በእርግጥ ግራ የሚያጋባ ጉዳይ ቢመስልም ፍቅርን በተመለከተ ግን በትክክል የምንፈልገውን ማወቅ ይጠበቅብናል፡፡ አንዳንዶቻችን በድንገት እንገናኛለን፤ ከዚም እንፋቀራለን፡፡ ወይም ደግሞ ያገኘነው ሁሉ ተቃራኒዎች እስከሆነ ድረስ ለመፋቀር ግድ የሌለን ሰዎች አንጠፋም፡፡ ይህ ትክክል አይደለም፡፡ በትክክለኛ ውስጣዊ ፍላጎታችን ላይ የተነጣጠረ የፆታ ምርጫ ሊኖረን ያስፈልጋል፡፡ እናም በትክክል የምንፈልገውን ለማወቅ ወሳኙ ጉዳይ ምን ምን አይነት ሰው ከእኛ ጋር እንደሚጣጣምና የበለጠ እንደሚመቸንም እራሳችንን መጠየቅ አለብን፡፡ ራሳችንን በመጠየቅ ውስጥ አዕምሯችን ትክክለኛ ምላሽን ያዘጋጅልናል፡፡ ጥያቄዎችህ በሚከተሉት መስፈርቶች ላይ ያነጣጥሩ፡-
– መልክ፣ ቁመና፣ ገቢ
– የአዕምሮ ንቃተ ህሊናና የፍጥነት ደረጃ
– የስራ የሙያ አይነት
– አለባበስ፣ ስብዕና
– ዘርና የትውልድ ሁኔታ፣ ሀይማኖት፣ የትምህርት ደረጃ
– ለፍቅራዊ አቀራረብና ለወሲብ ያላት የጋባዥነትና የመስብዕነት ደረጃ
ሌላው የምትፈልገውን በትክክል አውቀሃል ለማለት ፎቶግራፋዊ ምስሉ ምን እንደሚመስል በእጅህ ለመሳል ሞክር፡፡ እርግጥ ነው ስዕል መሳል ላይሆንልህ ይችላል፤ እኔም ዳቪንቺን እንዳልሆንክ እገምታለሁ፡፡ ይሁን እንጂ የልብህን ፍላጎት የሚያንፀባርቅ ስዕል ሳል፣ ቁመና፣ የመልክ ቅርፅ፣ ፀጉር፣ ወገብ፣ ዳሌ፣ አለባበስና የመሳሰሉ የምስል ገለፃዎችን በስዕሉ ላይ አስፈር፡፡ ይህን ስታደርግም የውስጥህን በትክክል ደፍቆ ማለት ነው፡፡ ከዚያም ከዚህች መሰል ሀሳባዊ ፍቅረኛህ ጋር የምትመሳሰል ሴት ከኢንተርኔት ውስጥ ግባና አውጣ፡፡ አውጣ ስልህ ግን ሌላ ሳይሆን ፎቶውን ፕሪንት አድርገው ወይም ፎቶ ቤት አሳጥበው ለማለት ነው፡፡ ይህ ፎቶ የአንተን ፍቅረኛ ማንነት የሚገልፅ ነው ማለት ነው፡፡ ይህን ፎቶ አንተ ልታየው በምትችልበት የተለያዩ ቦታዎች ላይ ለጥፈው፣ በሞባይልህ ውስጥ፣ በኮምፒውተርህ (Screen Saver)፡- በመኝታ ክፍልህ፣ በቦርሳህ ውስጥ፣ በቢሮህ ጠረጴዛ፣ በመኪናህ ውስጥ ወዘተ…
2. የፈለካትን ሴት እንደምታገኛት እመን
ይህ ዩኒቨርስ የአንተ ውስጣዊ የምናብ ዓለም እንጂ በራሱ አንተ እንደምታምነው እውን የሆነ አይደለም፡፡ ቅርፅ የምትሰጠው አንተ ነህ፡፡ ከአንተ ውጭ ያለው ዓለም ከአንተ ውስጥ ያለው ዓለም የፈጠረው ነፀብራቅ በመሆኑ ይህችን ከውስጥህ የቀረፅካትን ውብ ልጅ ደግሞ የማግኘት ዕድልህ በጣም ሰፊ ነው፡፡ ይህ ዓለም የአንተ እምነትና ቀረፃ ውጤት ነው፡፡ ቀረፃው ከሌለህ ምን እንደሚከሰት ልታምን ትችላለህ? በቅድሚያ የምትፈልገውን ቅርፅ አላየህምና፡፡ እንዲሁም ደግሞ የምትፈልገውን አውቀህ ካላመንክበት ዋጋ የለውም፡፡ አንድ ፊቱን የምትፈልገውን ባታውቅ ይሻላል፡፡ አንተ የሕይወትህ ሊዮናርዶ ዳቪንቺ ነህ፡፡ ፈጣሪ በዚህ ዓለም ላይ ያልተገደበ የፈጠራና የፈለከውን የማግኘት ስልጣን ሰጥቶሃል፡፡ እናም በዚህ ዓለም የፈለካትን ውብ ሴት የማግኘት 100% ዕድሉ አለህ፡፡ ይህ ግን የሚወሰነው በአንተ እምነት ውስጥ ነው፡፡ ይህ ዩኒቨርሲቲ የአንተ እምነት ተገዥ ነው፤ የፈለካትን ቆንጆ በትክክለኛ በ3 ዳይሜንሽን እስከ ቀረፅካት ድረስ አንተ ዝም ብለህ ለመቀበል ተዘጋጅ፡፡
3. የማመን መገለጫ መቀበል ነው
አንድ ነገር በትክክል እጃችን መግባቱን የምናውቀው ነገር ያው አራቱ ስሜት ህዋሳትን መሰረት ሲያረጋግጥ ነው፡፡ ነገሩን ከጨበጥነው፣ በዓይናችን ካየነው፣ ጠረኑን ካሸተትነው፣ እንዲሁም ድምፁን ከሰማነው ነገሩ በገሃድ ተከስቷል ወይም ደግሞ እጃችን ገብቷል እንላለን፡፡ ይህም ነገር እንዳለ ስለምናምን መቀበላችንን እናረጋግጣለን፡፡ ይህ በእርግጥ አይቶ ማመን እንጂ ሳያዩ ማመንን አያንፀባርቅም፡፡ ይህ ማመን ሳይሆን መጠራጠር ነው፡፡ ትክክለኛው እምነት በማይታየው ዓለም ውስጥ አንተ የምትፈልገው ነገር ሊከሰት እንደሚችል ማመን ብቻ ሳይሆን እንደተከሰተ ቆጥረህ መቀበልም መቻል አለብህ፡፡ የነገሮች ክስተት የሚጀምረው አዕምሮህ ውስጥ ነው፡፡ በአዕምሮህ ውስጥ የሌለው ክስተት ከውጪ ሊከሰት አይችልም፡፡ እናም የውጪውን ክስተት ሊያፋጥንልህ የሚችለው በአእምሮህ ውስጥ የምትፈልጋት ውብ ሴት ከአንተ ጋር በፍቅር ወይም በትዳር ውስጥ እንዳለች አድርገህ ክስተቱን መቀበል ስትችል ነው፡፡ ይህን ስታደርግ በትክክል ተቀብለሃታልና ውጫዊ ክስተቱም፣ ፈጣን ይሆንልሃል፡፡ ሙሉ እምነት ማለት ይህ ነው፡፡
4. በውስጥህ የፍቅር ስሜትን አሳድር
በኑሮህ ውስጥ ቆንጆይቱ ፍቅረኛ በትክክል መቀረጿንና መቀበልህን የምታረጋግጥበት ነገር ውስጣዊ ስሜትህ የደስ ደስ ፍቅር ሲሰማው ነው፡፡ ሁላችንም እንደሚገባን አንድ ከልባችን የምንፈልገው ነገር እጃችን ሲገባ በውስጣችን ከፍተኛ የደስታ ስሜት ይፈጠርብናል፡፡ በመሆኑም ውስጣዊ የደስታ ስሜት የማግኘታችንና ነገሩን የመቀበላችን ማረጋገጫ እስከሆነ ድረስ በአዕምሯችን ውስጥ በትክክል ውቧን ልጅ ተቀብለናታል ብለን ለማመን የደስታ ስሜት ሊሰማን ይገባል፡፡ ልክ የፈለካት ልጅ ጋር በጥሩ የፍቅርም ሆነ የትዳር ህይወት ውስጥ እንደተጣመርክ አድርገህ መቀበል ብቻ ሳይሆን በሚገባ መደሰትም ይኖርብሃል፡፡ ጥሩ የፍቅርና የደስታ ስሜት በተሰማህ ቁጥር ልጅቱን የማግኘት ዕድልህ በጣም ፈጣን ይሆናል፡፡ ይህ ዓለም በአንተ ውስጣዊ ስሜት ውስጥ በቀላሉ ተፅዕኖ ውስጥ የሚወድቅ በመሆኑ እንደ እምነትህ ይሆንልህ ዘንድ ውስጥህ በልጅቷ ደስ ይበለው፤ ይህም የደስደስና የፍቅር ስሜት ለተከታታይ ቀናት ከአንተ ጋር ይቆይ፡፡ የፍቅር ስሜት ሊይዘን የሚገባው ልጅቷ በገሃድ ከመጣችና ከተዋወቅን በኋላ መሆን የለበትም!
5. ቆንጆዎችን አጉልተው በሚያሳዩ ቦታዎች አዘውትር
እንደሚታወቀው ውበት ራሱን የቻለ ኢነርጂ ነው፡፡ በዓለም ላይ ሁለት አይነት ኢነርጂ አለ፤ ከፍተኛና ዝቅተኛ፡፡ የውብ ነገሮች ሞገድ በከፍተኛ ፍሪኩየንሲ ውስጥ ያርፋል፡፡ በውበት የማይታዩ ደብዛዛ ነገሮች ደግሞ በዝቅተኛ ፍሪኩየንሲ ውስጥ ይገኛሉ፡፡ የአንተ ኃላፊነት ውቦች የሚገኙበት ፍሪኩየንሲ መሆን አለበት፡፡ ለምሳሌ ውብ መኖሪያ አካባቢዎች፣ መ/ቤቶች፣ መዝናኛ ቦታዎች፣ ሱፐር ማርኬቶች፣ ሪዞርቶች፣ ህንፃዎች፣ ሆቴሎችና የመሳሰሉ ቦታዎች ቆነጃጅትን እንደንብ የሚስቡ ቦታዎች ናቸው፡፡ ጠላትን ለማጥቃት ማነጣጠር ያለብህ ጠላት ከሚያርፍበትና ከሚኖሩበት ቦታ እንደሆነ ሁሉ ቆንጆዎችንም ለማጥመድ ወደነዚህ አካባቢዎች ከመምጣት መቦዘን የለብህም፡፡ በእርግጥ ቆንጆ ሲባል መልክ ብቻ እንዳይመስለህ፤ ትልቁ ውበት ውስጣዊውና በደስ ደስ የተመላው ስሜትና ስብዕና ጭምር ነው፡፡ ዝቅተኛ ፍሪኩየንሲ ባላቸው ቦታዎች ውስጥ መልካቸው ያማሩ ሰዎችን ልታገኝ ትችላለህ፡፡ ነገር ግን በዝቅተኛ ፍሪኩየንሲ ውስጥ የሚኖረው ስሜት ዝቅተኛና ደብዛዛ ነው፡፡
6. ፍላጎትህን በንግግር አረጋግጠው
ይህ እንግዲህ ከፍተኛው የእምነትህ ሀይል መንፀባረቂያ ነው፡፡ ‹‹ቃል ሥጋ ሆነ›› እንደሚለው መፅሐፉ የአንተም ገንቢ ቃላቶች ፍላጎትህን ወደ አካላዊ ክስተት የመቀየር አቅማቸው ከፍተኛ ነው፡፡ በመሆኑም የሚከተሉትን ንግግሮች በተደጋጋሚ አንብባቸው፤ በንግግርህ ውስጥህም እንዳስፈላጊነቱ እያስገባህ ተጠቀምባቸው፡-
1. እኔ ለቆንጆ ሴት የተፈጠርኩ ነኝ
2. ቆንጆዎች የተፈጠሩት ለእኔ ነው
3. ቆንጆ በማፍቀሬ እጅግ ደስተኛ ነኝ
4. ፈጣሪዬ ቆንጆ አፍቃሪ ስለሰጠኝ ከልብ አመሰግነዋለሁ
5. እኔ ለቆንጆ ሴት የተመቸሁ ሰው ነኝ
6. አበቦች ንቦችን እንደሚስቡ ሁሉ እኔም ቆንጆዎችን የመሳብ ሀይል አለኝ፡፡
7. ቆንጆ ማፍቀር እችላለሁ፤ መብቴም ነው
8. ይህ ዩኒቨርስ የፈለኩትን ቆንጆ ስለሰጠኝ አመሰግነዋለሁ፡፡
9. በዚህ ዓለም ውስጥ እጅግ ብዙ ቆንጆዎች አሉ
10. ውስጤ በቆንጆ ልጅ ፍቅር ተሞልቷል!
7. ደካማ ጎናቸውን እወቅ
እንደሚታወቀው የትኛውም አይነት መስተጋብር በችግር ወይም በክፍተት ውስጥ የሚፈጠር ነው፡፡ ነጋዴና ደንበኛን የሚያስተሳስረው የሁለቱም ችግርና ድክመት ነው፡፡ ነጋዴው ከደንበኛው ገንዘብ ይፈልጋል፤ ደንበኛው ደግሞ የጎደለውን ለመሙላት አገልግሎትና የምርት ውጤት ከነጋዴው ይፈልጋል፡፡ ይሁን እንጂ ሁለቱም ሙሉ ከሆኑና የጎደላቸው ከሌለ ነጋዴውም ሆነ ደንበኛው ሊገናኙ አይችሉም፡፡ ባልና ሚስትን የሚያስተሳስራቸው ነገር ቢኖር ሌላ ጉዳይ አይደለም፤ የሁለቱም ድክመት ነው፡፡ ሴቷ ያላትን ድክመት በወንዱ ጠንካራ ጎን ለመሸፈን ስትል ወንዱን ትፈልገዋለች፤ ወንዱ ያለውን ደካማ ጎን ደግሞ እሱ በሌለው ነገር ግን ሴቷ ባላት ጠንካራ ጎን ለመሸፈን ስለሚፈልግ ሴቷን ይፈልጋታል፡፡ ነገር ግን ሁለቱም ደካማ ጎን ከሌላቸው ወይም ደግሞ አንዱ የሌላውን ደካማ ጎን መሙላት የማይችል ከሆነ ትዳሩ አይመሰረትም፤ ሁለቱም ፆታዎች ከትውውቅ የዘለለ ፍቅር ሊኖራቸው አይችልም፡፡
በመሆኑም ፍቅር ሊመሰረት የሚችለውም ሆነ ቆንጆዋ እንስት ወዳንተ ልትመጣና ከአንተ ጋር ልትቆይ የምትችለው አንድ ወይም ከአንድ በላይ ችግሮች ወይም ደካማ ጎኖች ወይም አስጊ ጉዳዮች ሲኖራት ብቻ ነው፡፡ በመሆኑም በትክክል የምታስፈልግህን ሴት ለማወቅ በቅድሚያ የአንተ ደካማ ጎኖች፣ ችግሮችና ስጋቶች ምን ምን እንደሆኑና እነዚህን የባህሪ ድክመቶችና ስጋቶችም ምን አይነት ባህሪ ያላት ሴት ልትሸፈንልህ እንደምትችል አስብ፡፡ እንዲሁም በትክክል የምትፈልጋት ሴት የትኛዋ ልትሆን እንደምትችል ለማወቅ ደግሞ የሴቷን ደካማ ጎኖች በሚገባ ማወቅና አንተም ይህን ለመሙላት የሚያስችሉህ ጠንካራ ጎኖች በሚገባ እንዳሉህ ለማወቅ ሞክር፡፡ ይህ እንግዲህ ‹SWOT analysis› ወደሚለው ፅንሰ ሀሳብ ይወስደናል፡፡
‹SWOT analysis› ለአንተ፣
‹SWOT analysis› ለእሷ፣
(‹SWOT› Means “S=Strength, (ጠንካራ ጎኖች)፣ W=Weakness (ደካማ ጎን)፣ O=Opportunity (መልካም ዕድሎች)፣ T=Threat” (አስጊ ጉዳዮች) የሚሰኙ ናቸው፡፡ በዚህ መልክ ከተነተንክ በኋላ ወደማማለሉ ቀጥል፡፡ ካማለልካት በኋላም በሚገባ ልታቆያት እንደምትችል ማወቅ ትችላለህ፡፡ የእሷ ጥንካሬዎች የአንተን ደካማ ጎኖች የሚሞሉ መሆን አለባቸው፤ የአንተ ጥንካሬዎች አደግሞ የእሷን ደካማ ጎኖች የሚሞሉ መሆን አለባቸው፡፡ µ

Reflections of a "Netch Lebash" (Eritrean agent)

By Eskinder Nega
There was something in the air on Tuesday, April 14, 2011. Intrigued by news of Ethiopian protesters in North America against the frivolous and mechanically hyped GTP, the glee on the faces of Addis residents was transparently noticeable.
I could sense breaking news in the making. And I was determined to report it as soon as possible. This could not possibly wait up to Friday, the designated day for my weekly English articles. But first I had to finish an Amharic article about Ambassador Donald Booth, the US Ambassador to Ethiopia.

I had to struggle to finalize the Amharic commentary, the last of a two-part article. My heart was no more into it in light of developments in North America over the weekend.

By 1 PM local time I was blissfully free to gauge popular mood in Addis and to surf the Internet for news. Two hours later, I was typing the first lines of my “breaking news” to the Diaspora.

Here is what had I had written:

News of protests plagued GTP meetings in North America has stirred emotions in Addis Ababa. A curiously significant number of people are openly arguing and opinionating about the protests in public venues, where sports and the North African uprisings, rather than domestic politics, normally dominate conversations.

Estimated as only “a handful” by ETV, protesting Ethiopians in DC succeeded in compelling the University to cancel the GTP meeting on Sunday. ETV reported that a bomb threat had been made.

But in an apparent signal as to which side was prone to violence, it was a protester, Tewdros Kabtyimer, who was gratuitously beaten by EPRDF supporters. His crime: proposing a silent prayer in memory of those who had died by government violence. There were also death threats against protesters.

In sharp contrast , not a single government supporter was harmed. As noted by Professor Teodros Kiros, who attended the protest in Boston, “they (government supporters) thought (that with ample provocations) the protesters would be frustrated and enter into street fights.

Instead the protesters remained cool…. The protest against tyranny in Cambridge, attended by an adequate number, was disciplined, well organized and qualitatively impressive.” The only incidence of violence in Boston, too, involved government supporters. A devotee of the EPRDF was arrested for attacking a photographer. Presumably, she was released after being fingerprinted.

And then I had to stop. It was time to see my mother. I had neither inkling nor premonition about the tragedy that was to swiftly and unexpectedly strike several hours later. This was supposed to be a routine visit.

My cell phone rang as the mini-bus approached my mother’s home forty minutes later. It was veteran journalist Bezu Wendemagegnehu calling from Canada. Would I have a few minutes to confer online about the protests? Sure. This should take no more than fifteen minutes.

We explored what the number of people who had turned out for the meetings imply for the EPRDF. Where were the tens of thousands of supporters it claims in North America? Certainly, turn out was strikingly low.

This is noteworthy for two reasons. First, unlike 2005, when the EPRDF cunningly used the ethnic card to rally support, no particular ethnic group turned out in large numbers to the meetings. The allure of the TPLF no more appeals to the middle, only the irrelevant fringe remains. And second, the low numbers mean that even its dwindling supporters have lost hope in the future. They see a sinking ship in the EPRDF.

And then a personal descent to the abyss. The unexpected loss of my beloved mother, who had raised me as a single parent, is a shock I am not sure I will ever recover from. Our unique bond was that of a mother and her only child. I will not try to explain it here.

The EPRDF struck on the third day after my loss, a sacred day of mourning to Ethiopians.This is calculated timing to maximize pain and terror. That the timing was clearly an unprecedented breach of decency and tradition seemed not to have mattered.

“Nech lebashu (secret agent),” a friend teased me as he sat next to me in the huge tent put up for the mourning period.

I stared back in utter bewilderment. Nech lebash is a term Meles Zenawi recently used to describe “opponents of the Ethiopian government who are allied with the Eritrean government.”

“Don’t tell me you haven’t read it yet,” he said, plainly surprised.

I hadn’t. Obviously, family members were doing their best to keep it a secret until the next day.

Taking up a full page of Chanel, a pro-EPRDF weekly noted for its “lumpen journalism”, I was accused of a long list of personal shortcomings. So be it. They do not merit a response. Slander is the least of my worries. But, alas, the central theme of the article was not the personal affronts. They were merely the side show. The thrust of the message was that I am “one of the opponents of the government who is effectively in alliance with Shabiya (Eritrea’s ruling party).” And thus the rational for the title of the article: Nech lebashu gazetengna! The same charge was repeated a week later, last Saturday.

And so, as I mourned the death of my cherished mother, the EPRDF has finally settled on my branding: Nech Lebashu gazetegna! An agent of Shabiya!

Congratulations Dilwenbru Nega! Your voice has been heard.

THANK YOU FOR THE MESSAGES OF CONDOLENCES.
We are simply awed and humbled by the messages of condolences we received over the past two weeks. We intend to respond to all of them in due time. They have been a source of profound comfort. We are indented to your generosities.

God bless you all.

Eskinder Nega and Serkalem Fasil.
The writer could be reached at serk27@gmail.com

ይድረስ ለእንግሊዝ ሠርገኞች

(by Daniel Kibret) አየ ሠርግ አየንላችሁ፡፡ እንዴው ምን ነክቷችሁ ነው እቴ፡፡ እናንተ አሁን ንጉሣውያን ቤተሰቦች ትመስላላችሁ፡፡ አካሄዳችሁ፣ አለባበሳችሁ፣ ንግግራችሁ፣ መኪናችሁ፣ ሥነ ሥርዓታችሁ ሁሉ ዘመናዊነት የጎደለው፣ ጥንታ ጥንት ብቻ፡፡ እንኳንም እኛ ሀገር አልሆናችሁ፡፡ እንዲህ ያለውን የጥንት ወግ ስታደርጉ ብትታዩ ምን ምን የመሳሰሉ ስሞች ዳቦ ሳንቆርስ እናስታቅፋችሁ ነበር፡፡

ነፍጠኛ፣ ያለፈው ሥርዓት ናፋቂ፣ ፊውዳል፣ ርዝራዥ፣ አድኃሪ፣ ጎታች፣ አክራሪ፣ ወገኛ፣ ያልገባው፣ ኧረ ስንቱ፡፡ እንግሊዝ ሆናችሁና ተረፋችሁ፡፡ አሁን እንደዚህ ጥንታ ጥንት ነገር ሰብስባችሁ እኛ ሀገር ሠርግ ብትሠርጉ እንኳን በቴሌቭዥን ልትታዩ ማንስ ይመጣላችኋል፡፡

ለመሆኑ የጥሪ ካርዳችሁ ከየት ነው የመጣው? እዚያው እንግሊዝ ነው የተሠራው እንዳትሉ ብቻ፡፡ ይኼው ድፍን አበሻ ከአሜሪካ አይደል እንዴ የሠርግ ካርድ የሚያስመጣው፡፡ የኛ መንግሥትኮ የወረቀትን ግብር ለሠርግ ካርድ ቢያደርገው ኖሮ እንኳን የሚያማርረው ትዝ የሚለው አይገኝም ነበር፡፡ የሚያማክር አጥታችሁ ነው እንጂ እንዴት ሀገር ውስጥ በታተመ የሠርግ ካርድ ትጋባላችሁ? ሠርጋችሁስ ላይ ምን ተብሎ ይወራል? መቼም ሠርግ ለወሬ ነው እንጂ ለዕድገት ወይንም ለጽድቅ ተብሎ አይደለም፡፡

አንቺስ ሙሽሪት ለመሆኑ ምን ስትይ ነው እንደዚያ በአያቶችሽ ጊዜ የተለበሰ የሚመስል የጥንት ቬሎ ዓይነት የለበስሺው፡፡ ነውርም አይደል እንዴ? ስንት ዓይነት ዘመናዊ የሆነ ብትፈልጊ ደረት፣ ብትፈልጊ ጡት፣ ብትፈልጊ ወገብ፣ ብትፈልጊም ሌላ ነገር የሚያሳይ ቬሎ ሞልቶ፣ በሀገርሺም ከጠፋ ከውጭ ሀገር ማስመጣት እና ሀገር ጉድ ማስባል ሲቻል ምነው ምነው ልጄ፡፡

አይ እንግሊዝ መሆን፡፡ ለዚህ ለዚህ ጊዜ ነበር አበሻነት የሚጠቅመው፡፡ አታይም እንዴ እኛ ሀገር የባህል ልብስ ለብሰው የሚያገቡትን እንዴት እንደምናንጓጠጣቸው፡፡ አንዳንዶቹ እንኳን ባህላዊ የሆነ ቬሎ እንሠራለን ሲሉ አዳሜ የሠርጉን እንጀራ ሲያነሣ ስማቸውንም በቢላዋ እያነሣ ይውላል፡፡ ሠርጉ ላይማ «አንቺ ቬሎውን ከየት ሀገር ነው ያመጣችው? ማነው የላከላት? እኅቷ ውጭ ናትኮ? እርሱም ከውጭ ነው የመጣው ይዞት መጥቶ ነው አሉ፡፡ ማንም ያልለበሰው አዲስ እንደ ወረደ ነው ይባላል» እየተባለ ካልተወራ ምኑን ሠርግ ሆነው፡፡

በተለይ ሙሽሪት የምትገርሚ ነሽ የኔን የሠርግ ልብስ የምትሠራው እንግሊዛዊት መሆን አለባት ብለሽ ነበር አሉ፡፡ እናንተ ሀገር «ለሀገር ውስጥ ምርት ቅድሚያ እንስጥ» የሚለው መፈክር ሠርቷል ማለት ነው፡፡ የሚገርማችሁ ግን ይህንን መፈክር በየኤግዚቢሽን ማዕከሉ የሚያሰሙት የሀገራችን ነጋዴዎች ይህንን መፈክር ሲያሰሙ እንኳን አንድም የሀገር ውስጥ ምርት አይለብሱም፡፡ እኛ ሀገር ይኼ መፈክር የሚሠራው ለድኻ ነው፡፡ እናንተ ጋ ለሀብታም መሥራቱ ገረመኝ፡፡ ሳስበው ሳስበው ግን አሜሪካ የሚኖር ዘመድ ያላችሁ አይመስለኝም፡፡ ምነው ዲቢ ሞልታችሁ ጥቂት ጊዜ እዚያ ሰንብታችሁ ብትመጡ ኖሮ፡፡ ብታጡ ብታጡ እንዴት ዱባይ ዘመድ የላችሁም፡፡

እኔ ያፈርኩባችሁ መኪናችሁን አይቼ ነው፡፡ ወይ የንጉሥ ልጅ መሆን፡፡ እኛ ሀገር እንኳን የንጉሥ ልጅ የድኻውስ ልጅ ቢሆን አፍንጫውን ነክሶ ተበድሮ በሊሞዚን ይሄዳል እንጂ ጋሪ የመሰለ መኪና ለዕድሉም አያሳየው፡፡ ርግጥ ዛሬ በሠላሳ ሺ ብር ሊሞዚን የተጓዘውን ሙሽራ በቀጣዩ ሳምንት ታክሲ ሲጋፋ ልታገኙት ትችሉ ይሆናል፡፡ ቢሆንም ቢሆንም ለታሪኩስ ቢሆን፡፡ ኧረ ዋናው ለቪዲዮው፡፡ «ሠርግ አላፊ ነው፣ ቪዲዮ ቀሪ ነው» የሚለው ተረት እናንተ ሀገር የለም እንዴ? በርግጥ ያ ሁሉ ወጭ የወጣበትን ቪዲዮ ሙሽሮቹ ሳያዩት አምስት ዓመት ሊሆነው ይችላል፡፡ ቢሆንም፡፡

አስታወሳችሁኝ፡፡ ለመሆኑ ቪዲዮ ቀራጮቹ የት ላይ ነበሩ፡፡ ወይስ ጭራሽ አልነበራችሁም፡፡ እናንተ እንግሊዞች ስትባሉ የማታመጡት ነገር የላችሁምኮ፡፡ ከፊት ከፊታችሁ እየተደረደሩ «ያዛት፣ ተያያዙ፣ ቀስ በሉ፣ መሥመሩን አስተካክሉ» ካላሏችሁማ አልተቀረፃችሁም ማለትኮ ነው፡፡ ተሸውዳችኋል፡፡

የወንድ ሚዜዎችን ኮት ሴቶች ሳይይዙ፣ ወንዶቹ ሴቶች ላይ፣ ሴቶቹ ወንዶች ላይ ሳይደገፉ፣ ሁለት ሁለት እየሆኑ ሳይለቀቁ፣ እንዴት ቪዲዮ ይቀረፃል? ለመሆኑ የናንተን ሠርግ የመራው ማነው? እኛ ሀገር ሠርግ ምርጥ የሚሆነው ቪዲዮ ቀራጭ ሲመራው ነው፡፡ ቁም፣ ተቀመጥ፣ ያዝ፣ ልቀቅ፣ ቀና፣ ደፋ፣ ሳቅ፣ ፈገግ፣ ና፣ ሂድ፣ ውረድ፣ውጣ፣ እዚህ ዛፍ፣ እዚያ ዛፍ፣ እያለ እንደ ኮንዳክተር ካልመራውማ አልተጋባችሁም ማለት ነው፡፡

ኧረ ደግሞ የገረመኝ በሀገራችሁ መንገድ ጠፍቶ ነው አያቶቻችሁ በሄዱበት መንገድ በሠረገላ የሄዳችሁት፡፡ ምነው እኛ ሀገር ብትመጡ ኖሮ፤ በቀለበት መንገድ፣ በወሎ ሠፈር፣ በጎተራ መሣለጫ መንገድ፣ በመገናኛ አዲሱ መንገድ፣ በስድስት ኪሎ፣ በአራት ኪሎ፣ በላፍቶ፣ በጉለሌ በስንቱ እናዞራችሁ ነበር፡፡ ያውም ጲጵ ጲጵ ጲጵ እያስባልን፡፡ ደግሞ የመንገድ ላይ ደሴት ስናገኝ ቪዲዮ ቀራጩ ያሰልፋችሁና አዙሪት እንደ ለከፈው ሰው ደሴቱን ስትዞሩት ስትዞሩት መዋል ነው፡፡ ለቪዲዮ አሪፍ ነዋ፡፡ በርግጥ ያንን መንገድ ከልጅነታችሁ ጀምሮ የሄዳችሁበት ሊሆን ይችላል፡፡ ቢሆንም ማን አድርጎ ማን ይቀራል፡፡

አንድ ያላማረባችሁን ነገር ልንገራችሁ፡፡ እንዴት የንጉሥ ልጅ ሆናችሁ ቤተ ስኪያን ገብታችሁ ተጋባችሁ? ለክብራችሁ ጥሩ አይደለም፡፡ አይ እኛ ሀገር አለመሆናችሁ ጎዳችሁ? እኛ ሀገር የበላይ መሪዎቻችን በተስኪያን ገብተው አይተን አናውቅም፡፡ ነውር መስሎን ነበርኮ፡፡ እናንተ ግን ስትገቡ ዝም ተባላችሁ? የናንተ ሀገርት ፓርቲ አይከለክልም? አንዱ በተስኪያን ገብታችሁ ከሌላው ስትቀሩ «መብታችን ተነካ፣ የሃይማኖት አድልዎ ተደረገብን፣ እነ እገሌ በተ ስኪያን ተገብቶ እኛጋ ለምን ይቀራል?» የሚል የለም እንዴ? አይ እንግሊዝ መሆን፡፡ ኢትዮጵያ ብትሆኚ አድልዎ ፈጽመሻል ተብለሽ ትገመገሚያት ነበር፡፡

አንድ ሌላ የገረመኝ ነገር አለ፡፡ እናንተ ሀገር ያሉት የቤተ ክርስቲያን መሪ ምነው በደንብ ሳናያቸው ቀረን፡፡ እንዲህ የንጉሥ ልጅ አግብቶ ቀርቶ አንድ የታወቀ ነጋዴስ ሲሞት በሚገባ መታየት አልነበ ረባቸውም፡፡ ትዝብት ነው ትርፉ፡፡ እንዲህ ባለ ጊዜ ነበርኮ የንጉሥ ወዳጅ መሆናቸውን ጎላ ጎላ ብለው ማሳየት የነበረባቸው፡፡ ተሳስተዋል፡፡ መቼም መካሪ አሳስቷቸው መሆን አለበት እንጂ እርሳቸው ደፍረው አያደርጉትም፡፡ ለወደፊቱ ባይደገም ጥሩ ነው፡፡

ምን ነው ግን የካንትበሪው ሊቀ ጳጳስ ባለ ሥልጣን አይመስሉምሳ፡፡ ከግራ ከቀኝ የሚደግፋቸው፣ ጎንበስ ቀና የሚያደርግላቸው፣ ሕዝቡን የሚገፋላቸው አጃቢ የላቸውም፡፡ በሰው ሠርግስ ቢሆን መወድስ ምናምን አይቀርብላቸውም እንዴ እንዴት በሼክስፒር ሀገር ቅኔ ሳይወርድ ቀረ? አይ እኛ ሀገር ቢሆን እንኳን እንዲህ በቴሌቭዥን የሚተላለፍ ሠርግ ቀርቶ በፎቶ ግራፍ የሚተላለፍም ከተገኘ ማን ይለቅቃል፡፡ ከብለል ከብለል የሚሉ አጃቢዎች መድረኩን ይሞሉላችሁ ነበር፡፡ ወይ ነዶ፤ ወይ እንግሊዝ መሆን፡፡

ግን እስኪ አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ፡፡ ያ ሁሉ ሕዝብ አደባባይ የወጣው በገዛ ፍቃዱ ነው ወይስ በቀበሌ በኩል ተነግሮት፡፡ መቼም መመሪያ ከዴቪድ ካሜሮን ተላልፎ መሆን አለበት፡፡ እርግጥ ብዛቱ ደስ ቢልም የአደረጃጀት ችግር ግን አለበት፡፡ እንዴት አንድ የረባ መፈክር አይያዝም፡፡ ሲሆን ሲሆን ከበላይ አካል አምስት ስድስት መፈክር ተጽፎ በመመርያ መልክ መተላለፍ ነበረበት፤ ካልሆነም በቀበሌ በኩል መዘጋጀት ይገባ ነበር፡፡ ደግም አልሠራችሁ፡፡

አንድ ነገር ልምከራችሁ፡፡ ይህንን ቢቢሲ የሚባል ቴሌቭዥን እናንተ ሥልጣን ስትይዙ መቅጣት አለባችሁ፡፡ «በሠርጉ ሕዝቡ መደሰቱን ገለጠ፤ ሠርጉ ቀጣይነት እንዲኖረው ተጠየቀ፤ ይህ ሠርግ ለሌሎች አገሮች አርአያነት እንዳለው ተጠቆመ፣» እያለ እንዴት ዜና አልሠራም፡፡ እንዲህ ያለውን ከቴሌቭዥን አትቁጠሩት፡፡

ይህንን ሁሉ የለፈለፍኩት ታዝቤ ታዝቤ ሳልነግራችሁ ብቀር አምላካችሁ ይታዘበኛል ብዬ ነው እንጂ ባህላችን ስለሆነ አይደለም፡፡ እንደ ባህላችንማ ሠርግ ላይ ተገኝቶ እየበሉ ማማት እንጂ ያሙትን መናገር ነውር ነበር፡፡ በሉ ይኼ በናንተ ያየነው በለሌሎች እንዳይደገም ቢቢሲ ባለሞያዎችን ጋብዞ ውይይት ያካኺድበት፡፡

በሉ ጋብቻችሁን የአብርሃም የሣራ ያድርግላችሁ፤

ያልተጋበዘው ታዛቢያችሁ ከአዲስ አበባ

Ethiopia Aid Agencies Back Call for Aid for 2 Million People Facing Hunger

A group of aid organizations in Ethiopia backed the government’s request for $75 million to help feed 2 million people facing hunger in the arid south and southeast of the country.

The crisis has been caused by a seven-month drought that is likely to persist until October, the Ethiopia Humanitarian Country Team, or EHCT, said in an e-mailed statement yesterday in Addis Ababa, the capital. The lack of rainfall has been caused by La Nina, a weather phenomenon in which the surface of the Pacific Ocean cools and reduces moisture in the atmosphere.

In addition to the 2 million people in the Somali, Oromia and Southern regions of Ethiopia, 1 million people in the rest of the Horn of Africa nation require urgent help, said the EHCT, which includes representatives of United Nations agencies, international and domestic non-governmental organizations and donors. The figure for the south and south east will be updated in early May, it said.

“Additional funds will be needed in the second half of the year,” Kristen Knutson, spokesman for the UN Office for the Coordination of Humanitarian Affairs, said in a phone interview from Addis Ababa. “We will have a better idea of further requirements once they have the results of the assessment.”

About 3 million of Ethiopia’s 80 million people are in need of emergency food assistance, the government said on April 12. Another 7.8 million people receive food or cash under an aid program, World Food Programme spokesman Susannah Nicol said in a phone interview yesterday from Addis Ababa.

The government issued an appeal on April 12 for funds needed in April and May. Recent rains in the region raised government hopes that the problem may be easing, said Akloweg Nigatu, information officer at the Agriculture Ministry’s disaster management agency.

“If there is rain there will be a lot of grazing land,” Akloweg said.

In addition to the drought, farmers have had to contend with high food and fuel prices exacerbated by a drop in demand for cattle because of political unrest in the Middle East and North Africa, ECHT said.

To contact the reporter on this story: William Davison in Addis Ababa via Nairobi at pmrichardson@bloomberg.net.

To contact the editor responsible for this story: Paul Richardson in Nairobi at pmrichardson@bloomberg.net.

በዓባይ ወንዝ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የነበራት ታሪካዊ ሚና ምን ነበር፤ አሁንስ ምን ዓይነት ሚና መጫወት ትችላለች??? (በፍቅር ለይኩን ከደቡብ አፍሪካ)

በዓባይ ወንዝ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የነበራት ታሪካዊ ሚና ምን ነበር፤ አሁንስ ምን ዓይነት ሚና መጫወት ትችላለች??? (በፍቅር ለይኩን ከደቡብ አፍሪካ)fiker ለማንበብ እዚህ ይጫኑ


የኖርዌይ ፖሊስ በኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ ስለወሰደው የኃይል እርምጃ በተመለከተ፤አኢጋን

ከጥቂት ቀናት በፊት ለተባበሩት መንግሥታ የስደተኞች ኮሚሽነር በዓለም ዙሪያ ግፍ እየተቀበሉ ስላሉት ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን በጻፍነው ደብዳቤ ላይ የኖርዌይ ስደተኞችን ሁኔታ በዝርዝር መጥቀሳችን የሚታወስ ነው፡፡ ከእነዚህ ኢትዮጵያውያን መካከል በኖርዌይ እስከ 16 ዓመታት የኖሩ የሚገኙበት ሲሆን በእነዚህ ዓመታትም ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ ባይሰጣቸውም ባገኙት ሕጋዊ የሥራ ፈቃድ እንደስደተኛ የመንግሥትን ድጎማ እየተቀበሉ ከመኖር ይልቅ ያገኙትን ሥራ እየሠሩ፣ ግብር እየከፈሉ እንዲሁም ራሳቸውን ከማኅበረሰቡ ጋር ለማዋሃድ ቋንቋ በመማር፣ ቤት በመሥራትም ሆነ በመግዛት ቤተሰባቸውን በዓቅማቸው ለማስተዳደር ሲጥሩ ቆይተዋል፡፡ ይህም ሆኖ ከኖርዌይ መንግሥት የተሰጣቸው ምላሽ ያልጠበቁት ከመሆን ባሻገር ኑሮዋቸውን እጅግ አስከፊ ደረጃ በፍጥነት እንዲደርስ ያደረገ ሆኗል፡፡

በቅርቡ ስደተኞችን አስመልክቶ የኖርዌይ መንግሥት ያደረጋቸውን ለውጦች የተቃወሙ 63 የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን (ሴቶችንና ህጻናትን ጨምሮ) በኦስሎ በሚገኝ ቤተክርስቲያን ጠለላ ባኙበት ወቅት የቤ/ክኑ ኃላፊዎች ከመንግሥት ጋር (ከኢሚግሬሽን ጽ/ቤት) ተነጋግረው በተስማሙት መሠረት እዚያው ኦስሎ ውስጥ ወደጊዜያዊ የስደተኛ ካምፕ ተዛውረው ነበር፡፡ ከእነዚህ ወገኖቻችን መካከል አንዲት የስድስት ወር እርጉዝ፣ ሌላ የ14 ህጻን ሴት ልጅ ያላት እናት፣ በኖርዌይ ለበርካታ ዓመታት ሲሰሩ የቆዩና በሌሎች የምዕራብ አገሮች ቤተሰቦች ያላቸው ዕድሉም ከተሰጣቸው ወደዚያው ለመሄድ የሚችሉ በርካታ ኢትዮጵያውያን ይገኙበታል፡፡ እነዚህ ወገኖቻችን ወደዚህ ካምፕ ተዛውረው ከኖሩ ከጥቂት ቀናት በኋላ ማክሰኞ ሚያዚያ 18፣ 2003 ዓም ያልተጠበቀ ሁኔታ ተከሰተ፡፡

የኖርዌይ የደኅንነትና የፖሊስ አካላት ወደካምፑ በመምጣት ኢትዮጵያውያኑን ከዚያ እንዲወጡና ወደፈለጉበት እንዲሄዱ ድንገተኛ የሆነና ለሰሚው ግራ የሚያጋባ ትዕዛዝ ይሰጣሉ፡፡ በአንድ በኩል የኢሚግሬሽን ጽ/ቤቱ በካምፑ እንዲቆዩ ሲፈቅድ በሌላ በኩል ደግሞ የፖሊስ አካላት እንዲህ ዓይነቱን እርስበርሱ የሚጋጭ ትዕዛዝ መስጠት እንደኖርዌይ ካለ አገር ሳይሆን እነ አቶ መለስ ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ›› ከሚሉት ራሱን በመርህም ሆነ በፖሊሲ የሚቃረን አገዛዝ ስንሰማ የቆየነው ነው፡፡ ሆኖም ግን ይህንን የፖሊስ ትዕዛዝ ለመቀበል አስቸጋሪ የሆነባቸው ወገኖቻችን በድርጊቱ ላይ ያላቸውን ተቃውሞ በገለጹበት ወቅት በተለይም አቶ ልዑል አለማየሁ የተባለውን የቡድኑን አስተባባሪ ፖሊሶቹ በሠንሰለት አስረው በሚወስዱበት ወቅት ተቃውሟቸውን የገለጹትን ሴቶች እህቶቻችንን በአሰቃቂ ሁኔታ መሬት ለመሬት እየተጎተቱ ሲወሰዱ ከዚህ በታች የሚታዩት ፎቶግራፎች ህያው ምስክርነት ይሰጣሉ፡፡ በተለይ መሬት ላይ በፖሊሶች ከተዘረረች በኋላ ታስራ የተወሰደችው እህታችን ወርቅዬ አማረ በግራ እግሯ ላይ ስብራት የደረሰባት ሲሆን ሌላኛዋ እህት ህሊና ሰለሞን ደግሞ በእጆቿ ላይ የተለያዩ ጉዳቶች ደርሶባቸዋል፡፡
እንዲሁም ከላይ የተጠቀሰችው የስድስት ወር ነፍሰጡር በደረሰባት እንግልት እንዲሁ ወደሆስፒታል ተወስዳለች፡፡ ምንም ዓይነት ወንጀል ያልፈጸመው ነገር ግን ለራሱና ለሌሎች መብት መከበር የሚሟገተው አቶ ልዑል አለማየሁ ወንጀለኞች ከሚታጎሩት ተወስዶ ለ7 ሰዓታት ያህል ከቆየ በኋላ ተፈትቷል፡፡

የቀኑን የፖሊስ ግርግርና ግፍ የተቋቋሙት ወገኖቻችን ካምፓቸው ቢቆዩም ምሽት ወደ 4 ሰዓት አካባቢ ጨለማን ተገን አድርገው የተመለሱት ፖሊሶች በርካታ የማጎሪያ መኪናዎችን ከተጨማሪ የፖሊስ ኃይል ጋር በመያዝ ተመልሰው በመምጣት እነዚህን ወገኖቻችንን በጭለማ እያስገደዱ ወደየመኪናው ካጎሯቸው በኋላ በተለያየ አቅጣጫ ከከተማ ውጪ አውጥተው በመጣል ‹‹የኖርዌይ መንግሥት እናንተን አይፈልግም፤ ከዚህ ወደፈለጋችሁበት ሂዱ›› በማለት የማስፈራሪያና የዛቻ ቃል በመናገር ለብዙዎቹ ፈጽሞ እንግዳ የሆነ ቦታ ላይ በጭለማ እንዳይገናኙ አድርገው በትነዋቸዋል፡፡ በከባድ ፍርሃት እና ጭንቀት ውስጥ የገቡት ወገኖቻችን ከያሉበት በስልክ በመገናኘት እንዲሁም ከተማ ውስጥ የሚገኙ ወዳጆቻቸውን በመጥራት ካሉበት እንዲወስዷቸው በርካታ ሙከራ ከተደረገ በኋላ እኩለሌሊት ላይ ሁሉም እንደገና ለመሰባበሰብ ችለዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜም ወደካምፕ መመለሱ ለህይወታቸውም ጭምር የሚያሰጋ እየሆነ የመጣ በመሆኑ ቀድሞ ጠለላ አድርገው ወደነበረበት ቤ/ክ ሜዳ ላይ ድንኳን በመትከል ሌሊቱ አሳልፈው መጻዒ ዕድላቸውን እየጠበቁ ይገኛሉ፡፡

ታሪካችንን ወደኋላ መለስ ብለን ስንመለከት ለኢትዮጵያዊ ስደት ማለት የውርደት መጨረሻ እንደነበር ከብዙዎች ሲነገር እንሰማለን፡፡ በቀድሞው ዘመናት ለትምህርት ወደውጪ አገር የሚሄዱ ኢትዮጵያውያን ትምህርታቸውን ከጨረሱ በኋላ ለምረቃ ለመቆየት ካለመፈለጋቸው የተነሳ የትምህርት ማስረጃቸውን በኤምባሲ በኩል አዝዘው ወደአገራቸው በፍጥነት ይመለሱ እንደነበር የብዙዎች ትዝታ ነው፡፡ ‹‹እናት ኢትዮጵያ›› በማን ተተክታ ነው ስደት እንደ ክብር ተቆጥሮ በሰው አገር የሚኖረው? በማለት ወደ አገራቸው የሚሄዱበትን ቀን እንደ እርጉዝ ሲቆጥሩ ነበር የሚቆዩት፡፡

አሁንስ? አሁንማ ስደት ‹‹ክብር›› ከመሆን አልፎ ዓለምአቀፋዊ መለያችን ሆኗል፡፡ ቁጥራቸው እጅግ በርካታ የሆኑ ኢትዮጵያውያን በአገራቸው ውስጥ የሚኖሩት በየቀኑ ወደውጪ የሚሄዱበትን በናፍቆትና በተስፋ ካልሆነም ወደሚክሲኮና አረብ አገራት እንደሚሄዱቱ ህይወታቸውን አደጋ ላይ ለመጣል በመዘጋጀት ነው፡፡ ለቅኝ ገዢዎች የእግር እሣት የነበረው የኢትዮጵያዊነት ኩራት እዚህ ደረጃ ላይ ደርሶ ማየትን የመሰለ ውርደት የለም፤ አይኖርምም፡፡ ይህንን በህዝባችን ላይ ከተለያየ አቅጣጫ ለሚደርስ በደል መከታ የሚሆን አለኝታ መንግሥት የሌለን መሆናችን ደግሞ ሃዘናችንን እጥፍ ድርብ ያደርገዋል፡፡

የኢትዮጵያችን ችግር የስደት ብቻ አይደለም፡፡ የኢትዮጵያውያን የስደት ችግር በኖርዌይ ብቻ ተጀምሮ የሚያልቅ አይደለም፡፡ በጃፓን፣ በስዊድንና ሌሎች የአውሮፓ አገሮች፣ በሳዑዲአረቢያና በበርካታ የአረብ አገሮች፣ በአጠቃላይ በመላው ዓለም የአገራችን ሕዝብ ተበትኖ የሰው ልጅ ሊደርስበት ይችላል ተብሎ የማይገመት መከራ እየተቀበለ ይገኛል፡፡ ጥያቄው ያለው ‹‹ሕዝባችን ለምንድነው ይህንን የስደት ኑሮ መፍትሔ አድርጎ የመረጠው?›› የሚለው ላይ ነው፡፡ መልሱንም በጥየቄ መመለስ ይቻላል፡፡ በአገራችን ነጻነት፣ እኩልነት፣ ፍትሕ፣ ሰላም ቢኖርና ሁሉም እንደዜጋ ተከብሮና አኩል የመሥራትና የመኖር ዕድል አግኝቶ መብቱም ተከብሮ ለመኖር ቢችል ለመሰደድ የሚፈልግ ምንያህሉ ይሆን ነበር? ለዚህም ነው የጋራ ንቅናቄያችን ‹‹ከዘረኝነት ይልቅ ለሰብዓዊነት ቅድሚያ የሚሰጥባትን›› እና ‹‹ሁላችንም ነጻ›› የምንሆንባት ‹‹አዲሲቷን ኢትዮጵያን›› ለመመሠረት የሚታገለው፡፡ ለዚህ ዘርፈብዙ ለሆነው ችግራችን ዋንኛው መፍትሔ ከዚህ ውጪ ፈጽሞ ስለማይሆን ሁላችንም በምንችለው ለራሳችን ብቻ ሳይሆን ለሌሎች ነጻነት፣ መብት መከበርና እኩልነት በያለንበት እንቁም፡፡

ማሳሰቢያ፡- በአሁኑ ጊዜ ይህንን ከፍተኛ ችግር እየተጋፈጡ ያሉትን በኖርዌይ የሚገኙትን ወገኖቻችንን ይረዳ ዘንድ ለተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ኮሚሽነርና ለሌሎች ከፍተኛ ባለሥልጣናት በአንድ ጊዜ በኢሜይል መልክ እንዲደርስ ያዘጋጀነውን አቤቱታ እንድትሞሉ በድጋሚ ጥሪ እናደርጋለን (http://solidaritymovement.net/signPetion.cfm) እንዲሁም እዚያው ኖርዌይ ድረስ በመደወል የሞራልም ሆነ ማንኛውንም ዓይነት ድጋፍ ለመስጠት ለምትፈልጉ ሁሉ የስደተኞቹ ጉዳይ አስተባባሪ የሆኑትን አቶ አዳነ አስረስን 47 47 62 65 79 መደወል ወይም በኢሜይል(Adeew2000@yahoo.com) ማግኘት የምትችሉ መሆናችሁን እየገለጽን በተለይም በዓለምአቀፍ የስደተኞች ጉዳይ ላይ ባለሙያ የሆናችሁ በሙሉ የምትችሉትን የሙያ ድጋፍ እንድትሰጡ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን)
**************************************************************************************************
ለዚህ ደብዳቤ ምላሽም ሆነ ለተጨማሪ መረጃ ዋና ዳይሬክተሩን ለአቶ ኦባንግ ሜቶ (obang@solidaritymovement.org) በመጻፍ ወይም ድረገጻችንን (www.solidaritymovement.org) በመጎብኘት ለመረዳት ይችላሉ፡፡

ሚጢጢ መዳፍ

By Wannaw

ንፋሱ የፒያሳን ጎዳናዎች ከጥግ እስከጥግ አዳርስ ተብሎ ከላይ እንደተላከ ሁሉ የላስቲክና የኮተት መዐት እያንኳኳ ያልፋል :: ቀሚስ ይገልባል … በእድሜ ብዛት የተጣፈ ሻንጥላን እያወላገደ ይታገላል :: ሚጡ ዓይኖቿ ውስጥ የገባዉን አዋራ በትናንሽ ጣቶቿ እንደጨፈንች እያሸችው በእንባዋ ታሟሟዋለች : ከዛም ዓይኖቾ ይቀላሉ :: ቀይ ፊቷን በብርድ ፊርማ ተዥጎርጉሮም ውብ ገጿ እንዳለ ነው :: ካፍንጫዋ ስር የደረቀው የንፍጧ ቅርፋፊ እርብትብት ከናፍርቷን ያመላክታል ::
ሚመጸወት ሲመጣ ልክ እንደፒያሳው ነፋስ እሷም በሚጢጢ ባዶ እግሯ እየሮጠች ትንሽ መዳፏን ትዘረጋና አንገቷን ዘመም ታደርጋለች :: ከተጎነጎነ መቆየቱን በመቦዘዙና በመበታተኑ ሚያስታውቅ ፀጕሯን ባንደኛው እጇ እያከከች በኮልታፋ አንደበቷ ትለምናለች : ግን አልተሳካላትም እንደሠውም የቆጠራት የለም :: እሷም ሆድ አይብሳትም ወዲያው ወደጨዋታዋ ትሮጣለች የተንከረፈፈ ቀሚሷን እያዘናፈለች ወደሞነጫጨረችው መሬት ላይ ድንጋይ እየወረወረች እናጣጥ እንጣጥ ትላለች … ወዲያው ደግሞ መዳፏን ዘርግታ ራሷን ጋደድ አድርጋ አላፊ አግዳሚዉን ትለምናለች ::

”ዛሬ ምነው አንቺም እንደመስከረም ንፋስ ቅልብልብ አደረገሽ ሚጡዬ …?”
አሏት ጋሽ አስቻለው የተወረወረላቸዉን ሣንቲም ባንድ እጃቸው እየቆጠሩ አንደኛው እጃቸው የለም … ወይም አልነበረም :: ሁለቱ እግራቸዉም እንደዚሁ … የመጸዋቹ አንጀት ጨክኖ ሚቆጥሩት ቀርቶ ብድግ ሚያደርጓት ሳንቲም ‘ንኳን ሲያጡ የተሸበሸበ የፊታቸው ቆዳ ላይ ሚንጠባጠበዉን እንባ በትከሻው አንገታቸዉን ቆልመመው እየጠረጉ
”አይ ፈጣሪ ለዚች ግማሽ በስባሳ ስጋዬን ‘ንኳን መሆን አቃተህ …?”
እያሉ ያለቃስሉ ::
ከርሳቸው ፈንጠር ብላ የሚጡ እናት ሎሚዎቿን ዘርግታ ገቢያ ትጠብቃለች :: ቀጫጫ ሠዉነቷ እጥፍጥፍ ብሎ ትንሽ ሆናለች : በጊዜ ጠባሳ የተደበቀ ውበቷ ዳመና እንደጋረደው የማታ ጀንበር ሆኗል ::

”ምነው ዛሬ ደግሞ ልጅሽ እንዲያ ስትፈነጥዝ አንቺ መተከዝሽ …?”
አሉ ጋሽ አስቻለው ወደሚጡ እናት እያዩ : ቀሚሷን ለመግለብ ከሚታገላት ንፋስ በክንዷ እንደመመንጨቅ ብላ ያጠፈች እግሯ መሀል ሸጎጠችና

”አይ አባት … መቼ ሳልተክዝ ውዬ አውቅና ነው …? ነው ወይስ ዛሬ ነው በመስከረሙ ብረሐን ያስተዋሉኝ …?”
ፈገግ ለማለት ስትል ብልጭ ያሉ ጥርሶቿ እውነትም በቁጠባ ብቻ እንደሚከፈቱ … ለክት ብቻ እንደሚታዩ ሁሉ በረዶ ናቸው ::
”ኤዲያ ምን ቢተክዙ ቢያብሰለስሉ አይሞላ ….. እንዳስቻለው ገላ ጎዶሎ ለሆነ ሕይወት ደግሞ …”

መፅዋቹ ጠብ ሚያደርግላቸዉን ሣንቲም አይተው ቀና ይሉና የምርቃት መዐቱን ያወርዱታል :: ሚጡ ለርሳቸው የመፀወተዉን እየተከተለች ስትለምን መፅዋቹ 10 ሣንቲም ትንሽ መዳፏ ላይ አቀበላት ሳንቲሙን በስስት አይታው ወደናቷ ስታመራ
”ምነው ሚጡዬ አሳሳሽ እንዴ ?”
አለቻት በአዋራው የቀሉ ዓይኖቿን አይታ
”ከለሜላ ልግዛበት …?”
አለቻት ሣንቲሙን ወደጀርባዋ እንደመደበቅ እያደረገች

”ግዢበት …”
አለቻት እናትየው በከረሜላ ጉጉት የበሩ ድፍርስ ዓይኖቿን በሀዘን አይታ : ሚጡ ሮጣ ማስቲካ ሲጋራና ከረሜላ ወደሚቸረችረው ጫማ ጠራጊ ሄደች ::

”ይሄ ከረሜላ አይገዛም …”
አላት ድንገት ጉልበቱ መሀል አጣብቆ የያዘዉን ያረጀ ጫማ በጅማት ወስውሶ በወረንጦ መጎልጎሉን ገታ አድርጎ እጇ ላይ ያለዉን ድፍን አስርሣንቲም እያየ ..
ሚጡ ሣንቲሙን አገላብጣ አየችዉና ሸንኮራ ወደሚሸጠው ደግሞ ሄደች

”እናትሽን 10ሣንቲም ጨምሪ …. በያት ::”
አላት ሸንኮራ ሻጩ :: በጨርቅ እንደቁስለኛ የተበተበ ቢላዉ የሸንኮራ ፍርፍሪ በመያዙ ዝምቦች ሊወሩት ያንዣብባሉ :: ከሻጩ ይልቅ ያልተነኩት አገዳዎች በኩራት የመዘጋጃ ጊቢን ግንብ ተደግፈዋሉ :: አሁንም ሚጡ 10ሣንቲሙን አይታው ወደመፋቂያ ሻጩ ሄደችና ቀልቧ የወደደዉን መፋቂያ ስታነሳ ሻጩ እጇን ቀብ አደረጋት ::

”… ልገዛ ነው ….”
አለች እንደማልቀስ ብላ
”ለየትኛው ጥርስሽ እስቲ እኝኝኝኝ በይ ::”
አላት መፋቂያ ሻጩ : እጇን ሳይለቃት የጉንጩ ከፊቱ አጥንት ላይ መለጠፍ የዓይኖቹ መጎድጎድ የከንፈሩ መድረቅ … እሕል ቀምሶ ሚያውቅም አይመስልም ::

”እኝኝ ”
አለች ሚጡ ትንንሽ ጥርሶቿን ለማሳየት ቀይ ድዷን እያበራች
”… ለኔእኮ አይደለም ለእማዬ ነው …”
አለች እኝኝ በማለቷ እንዳፈረች ሁሉ አንገቷን ደፍታ

”ለናትሽ ወተት ጥርስማ እኔ በነጻ እሰጥሻለው ታዲያ ንገሪያት እሱ ነው የላከልሽ ብለሽ …”
አላት የተከናነበችዉን ሎሚ ሻጭ እናቷን እያየ

ሚጡ መፋቂያው ቢሰጣትም ለምና ያመጣችው ሣንቲም ምንም የመግዛት አቅም እንደሌለው አይታ ተናዳለች …

”ልመዘን …?”
አለች ሚዛን ስሩ አኑሮ ቀጫጫና ወፍራም በመለካት ዳቦዉን ሚጠብቀዉን ወጣት …. 10ሣንቲሟን እያሳየችው : በቁጣ
”ሂጂ ወደዚያ እቺ ሳትፈለግ ተፈልፍላ …”
ከተናገረ ሣምንት ያልፈው ሚመስል ድምፁን ትንሿ ሚጡ ላይ ሞረደ … በሞረድ ዓይኖቹም እያፈጠጠባት …. ሚጡ እንደንፋስ በርግጋ ወደናቷ ሮጠች

”እማዬ መፋቂያ አመጣዉልሽ …”
አለቻት ለናቷ ቅርፊቱ በቄንጥ የተቀረፀ ረጅም መፋቂያዉን እያቀበለቻት
”አይ ሚጢዬ …. ላንቺ ከረሜላ ብለሽ … ለኔ መፋቂያ ገዛሽ ?”
አለቻት አቅፋ አንገቷ ስር እየሳመቻት እንዲህ አድርጋ ስትስማት የሚጡ አባት ትዝ ይላታል እሱም በፍቅራቸው ጊዜ ተላፍቷት ካደከማት በኌላ አንገቷ ስር ነበር ሚስማት
”እስቲ … ባክህ … ምን እንደድመት አንገቴን …”
ትላለች ስሜት ባወረዛው ፊቷ የውሸት ቁጣ እየሞከረች
”ለዛሬ ድመት ብንሆን ምን አለበት ውሻ እያረጉን ስንት ጊዜ እንኖር የለ …?”
ይላታል በቀን ስራ የጠነከረ መዳፉን ወገቧ ላይ እየጠመጠመ …
አንድ ቀን እንዲሁ በድሕነት ፍቅራቸው ሐሤትን እያገኙ በመዋደዳቸው ድሕነትን ድል እየነሡ እንዲህ አለችው
”እኔ ያንተ ልፊያ በቃኝ አሁንማ ምትላፋው ላመጣልህ ነው …”

”አልገባኝም …?”
አላት ዓይኖቹን አፍጥጦ

”አሳድገህ ምትላፋው ላመጣልህ ነዋ …”

”አሁንም አልገባኝም …”
አላት

”ኡፍፍፍፍ አንተ በቃ ይሄ ሢሚንቶ ጆሮህን ደፍኖታል አይደል ?”
አለችው በነኚያ ጥርሶቿ ፈገግ ብላ የጎን እያየችው

”ጆሮዬማ እየሠማ ነው ግን ….”
ይሄኔ መዳፉን ይዛ ሆዷ ላይ አኖረችው : ፈነጠዘ
”እውነት እርጉዝ ነሽ ?”

”እና በቅሎ መሰልኩህ ….?”
ፈነጠዘ ማንቆርቆሪያ ጠላ አስልኮ ዋንጫዉን አጋጨ ::

”ግን ሤት መሆን አለባት …”

”እሱን አንተ አትወስንም እኔ ደግሞ ምፈልገው ወንድ ነው …”
ትላለች እሷም
”በጭራሽ … አቤት …. ፓ ! እንደምንም ጥሩ አድርጌ ነው ማሳድጋት ”

”እስቲ ልጁ ይምጣ መጀመሪያ … እሳቸው በመጡና አፈር በበሉ አለች አክስቴ ….”

ግን ልጁን አላየም :: ሚጡ ልትወለድ 3 ሣምንታት ሲቀረው ከሚሠራበት ፎቅ ላይ ድንጋይ ወደቀበት … ያ ቀን የጣለው ድንጋይ የሚጡ አባትንም ሕይወት ጣለው ::

”እማዬ … ያ ከቻቻው ልጅ ‘ኮ ነው የሰተሽ የኔ 10ሳንቲም ምንም አልገዛ አለኝ …”
አለቻትና ሳንቲሙን እንደመደበቅ እያደረገች አሳየቻት እናትየው ፊቷ በሀዘን ቀጭሟል

”… አስል ሳንቲም ምንም አይገዛም ?”
አለች ሚጡ ለማትሠማት እናቷ

”አባባ አስል ሳንቲም ምን ይገዛል ?”
አለች ለጋሽ አስቻለው

”አዬ ልጄ ትንሽ አርፈድሽ ተፈጠርሽ እንጂ … ብዙ ነገር ይገዛ ነበር …”
አሏት ::
ከማዶ የጊዮርጊስ ቤ /ቲያን ቅዳሴ ከታክሲዎች ጥሩንባና ከአውቶብስ ፍሬን ቡጥጫ ጋር እየተሻማ ይሠማል ::

”አባባ … በካ ምንም አይገዛም ?”
አለች ሚጡ : ሁሉም ዝም ብሏል ያ ሣንቲም የመግዛት አቅሙን ሊነግራት የቻል የለም :: እናቷ ወደትላንትና ትዝታዎቿ ነጉዳለች

ሚጡ ሣንቲሙን ጋሽ አስቻለው ግማሽ እግሮች ስር ወርውራ ወደ እናቷ ሮጠች

”ለምን ታልክሺያለሽ መፋኪያውን ልመልስለት ….?”
አለቻት እንባዋን በሚጢጢ እጇ እያበሠች

”ሚጡ …”
አሉ ጋሽ አስቻለው : ሚጡ ዞር ብላ አየቻቸው

”10 ሣንቲም ምርቃት ይገዛል …”
አሏት

”ምንድነው ምንድነው …?”
ብላ ሮጠች

”እግዚያብሔር ፊቱን አያዙርብሽ …”
አሏት :: ሚጡ ሣንቲሙን መስጠቷን ረስታው ሚጢጢ መዳፏን አየች :

የጊዮርጊስ ደወል …. የመዘጋጃ የሠዓት ደወል …. ይሠማል ጊዜ በማንኛዉም ቅፅበት ስልጣን እንዳለው ለመናገር ሚያሾፍ መሠላቸው ጋሽ አስቻለው ::

______________________////__________________________

መጀመሪያ
ተፃፈ በኢት አቆጣጠር 19 91

ከጨረቃ ስር

By Wanaw

አንቺ የምሽት ኮከብ ጨረቃ
ድንገት በሕልሜ አይቼሽ ብነቃ …

የዳዊትን ዜማ ጮክ ብላ ታዜማለች : ስታዜም ወደጨረቃዋ አንጋጣ ነው ከጀርባዋ የተከፈተው የመጠጡ ቤት የሚንቦገቦግ መብራት ከፊል የፊቷን ገፅ እየቀያየረ ያሳየኛል ከፊል ፊቷን ደግሞ በጨለማው ውስጥ ያበራችው የምታዜምላት ጨረቃ ብረሐን ታሳየናለች :: ሲጋራዋን አንዴ ስትስበው እሳቱ ፈመ :: ከሷ ጎን አንዲት ሌላ ሴት ፀጉሯን እንደማስተካከል እያለች ድራፍቷን ትጎነጫለች ከመጠጥ ቤቱ ውስጥ ”ልጁን ያያችሁ አዬ እስቲ ን .ገ .ሩኝ …” ‘ሚለውን ዜማ ብዙ ድምፆች አጅበው ያዜማሉ :: የምሽቱ አየር ሞቅ ያለ ስለሆነ ከውስጥ ይልቅ በረንዳው ተመችቶኛል :: እዚህ ናዝሬት ከመጣው 1ሣምንት ሆነኝ የመጣዉበት ዓላማ ስላልተሳካ ዛሬ በተለይ ምርር ብሎኝ ነው የዋልኩት እዚች ቤት ሆኜ የምሽቱን ንግስቶች መልክ ሳጠናና ሳስተውል ይሄው ዛሬ 3ኛ ቀኔ ነው ::
አንዲት አጭር ሞንዳላ ሴት ከማጨሠው ሲጋራ ‘ወጋው ‘ ስትለኝ ሌላ ሲጋራ ስሰጣት
”ፍሬንድ ምነው አንተ ደግሞ ቺክህ ጥላህ ኮበለለች እንዴ … የሆነ ትካዜ ምናምን ነገር … አቦ ግባና ወዝወዝ በልበት ካስፈለገም ድብርቱን ….”
አለችና ሌባ ጣቷን ካጣበቀቻቸው ሁለት ጣቶቿ ጋር ጧ ! አድርጋ እያማታች
”እኛ እንነቅልልሀለን ”
ብላኝ ወደ ውስጥ ገባች : በፈገግታዬ ሸኘዋት ያቺ ልጅ አሁንም ታዜማለች ሢጋራው አልቆ አመድና ቁራሽ ስፖንጅ ሆኖ ተወርውሮዋል …
”መስኮት ከፍቼ ውጪ ባይሽ
ጨረቃም የለች አንቺም ጠፋሽ
ዳግም አልተኛ ምን አደርጋለሁ
እስክትመጪ እጠብቃለሁ ”

ስታዜም ወደ ጆሮዎቿ ጥግ ተንጋደው ቀልበስ ያሉ ዓይኖቿ ይጨፈናሉ ቀለም የቃሙ ከናፍርቷ ይሾላሉ … የምጠጣዉን ድራፍት ያዝኩና አጠገቧ ሄድኩኝ
”ይቻላል …?”
አልኳት አጠገቧ ያለዉን ወንበር ድራፍት በያዘ እጄ እያመላከትኳት አልመለሰችልኝም …
ከራሷ ጨማምራበት ካልሆነ መቼም የዳዊት ግጥም እንደሆን አልቅዋል ተቀመጥኩኝ
”ጨረቃ ትወጂያለሽ ?”
አልኳት እንደመፍራት ብዬ : ያቺ የቅድሟ ከመፀዳጃ ቤት ስትመለስ ገላምጣኝ ፈንጠር ብላ ተቀመጠች :
”እ … እኔን ነው ?”
አለችኝ ያቺ ጨረቃ አፍቃሪ
”እንግዲያ … ጨረቃዋማ እንኳንስ እኔን ልትሰማ አንቺንም ስታዋራ አላየዋት ለሷ ማወራው ”
አልኳት : ሳቀች ስትስቅ ሸራፋ ጥርሷ ሳቋን ቄንጠኛ አደረገላት :
”ከመጣህ 1 ሠዓት አልፎሀል እንዴት አሁን ታየውህ ?”
አለችኝ ተቀምጬ የነበርኩበትን ወምበር ገልመጥ አድርጋ ቀይ ፊቷ ስጠጋው እንደቅድሙ ሲጋራዋ ፍም ቦግ ብሎ ታየኝ :
”አሁን አይደለም የታየሽኝ ቅድም ነው ዘፈንሽን ማቋረጥ አልፈለኩም ነበር ”
አልኳት
”እዚህ ቤት ሳይህ 3ተኛ ቀኔ ነው ሁሌም ብቻህን ሆነህ ሲጋራህን እያቦነንክ ድራፍትህ ላይ ተተክለህ ነው ….. ሸርሙጣ ማትወድ ነህ ብዬ ደምድሜ ነበር ”
አለችኝ አገጯን በመዳፏ ጥግ እንደደገፈች
”እንዴት አስተዋልሽኝ ?”
”እኛ ሸርሙጣዎች ነን ስጋችንን ምንቸረችርለት ሠው በዓይናችን የመፈለግ ግዴታ አለብን ”
ድምጿ ይርገበገባል ዝም አልኳት ከደረት ኪሴ የሲጋራ ፓኬት አወጣዉና አቀብያት ለራሴም ለሷም አቀጣጠልኩኝ
”ጅን ግዛልኝ ዛሬ አባቴ በታም ናፍቆኛል እንዲህ ሙሉ ጨረቃ ስትወጣ አባቴ ይናፍቀኛል ;”
ገብቼ ለኔ ድራፍት ለርሷ ጅን ይዤ መጣው ከውስጥ የቦብ ማርሊ ሙዚቃ ይጮኻል ጎረምሶች አንድ እግራቸውን እያፈራረቁ አንድ እጃቸውን ወደጣሪያው ዘርግተው ሌባ ጣታቸዉን ቀስረው ይወዛወዛሉ

”ሰካራምም አጫሽም አትመስልም ”
አለችኝ ጅኑን ተቀብላ ከኔ ድራፍት ጋር አግጭታ እየጠጣች ስታንቆረቁረው አንገቷን ቀና ስታደርግ አይቼያት አንገቷ ረጅም ነው :
”የጠጣ ሁሉ ሰካራም ሲጋራ ያጨሰ ሁሉ አጫሽ አይባልም ”
አልኳት : ሳቀች እነኚያን ቅርጻቸው ደስ ያሉኝን ዓይኖቿን እየጨፈነች
”ምናለ ለብር ስትል ጭኗን ከፍታ …… የሰጠች ሸርሙጣ አይደለችም …… የሚል ውሸት ቢጀመር ….. ምናለ ጠላቶቻቸዉን በቢላ ወግተው የገደሉ … ነብሠገዳይ አይደሉም የሚል ውሸት ቢመጣ …..”
ያጠላለፈችው እግሯን ስታቀያይር የባቷን ቅርፅ አየውት … አሸራሟጭ በሆነ ስሜት ይሁን ተፈጥሮን በማድነቅ ስሜት ብቻ አደነቅኩት ጎመዠዉትም ::

”ሳይህ ደደብ አትመስልም ብዙ ወንዶች ደደቦች ናቸው ለምንድነው ?”

”እኔንጃ ….”
ሲጋራዋን የያዘችበት የጇ አውራ ጣት ዓይኖቿን አበሰችና ወደጨረቃዋ እያየች
”ጨረቃ ትወዳለህ ?”
አለችኝ
”አስቤው አላውቅም ማለተ ልውደድ ልጥላ ስሜቱን አላውቀዉም ”
አልኳት : የጡቶቿን ቅርፅ አሳምሮ የሚያሳይ ልብሷን ወደ ዳሌዋ ቁልቁል ሳብ አድርጋ
”ለፉገራ እወዳለሁ ብትለኝ ደደብ ነህ ልልህ ነበር ምክኒያቱም ለጨረቃ ግድ እንደሌለህ ታስታውቃለህ … አባቴ ሲነግረኝ የተፀነስኩትም የተወለድኩትም በሙሉ ጨረቃ ነው ይሄው እኔም በጨረቃ ሸርሙጨ በጨረቃ ፍም ስንዴ ዳቦ እጋግራለሁ … የአስቴርን ዘፈን ታውቀዋለህ ?”
እስክመልስላት አልጠበቀችኝም የአስቴርን ዘፈን ቀጠለች
”ስንዴ ዳቦ ጋገርኩ በጨረቃ ፍም ….”
አንድ ጡንቻው የለበሠዉን ጠባቃ ሸሚዝ ያስጨነቀ ወጣት ደረጃዉን አልፎ ወደ በረንዳው ብቅ አለ እንደሚፈልጋት ነግሯት ወደውስጥ ገባ የልጁ የራስ ፀጉር በተልባ ተዘፍዝፎ እንደከረመ ሁሉ ሉጭጭ ብሎ እዛው ተጠቅልሏል ::
”ዛሬ ሽቀላ ካላገኘው እሱን አቅፌ የመተኛት ግዴታ አለብኝ ”
አለች ምርር እንዳላት ሁሉ ዘፈኗን አቋርጣ
”ለምን …?”
ጥያቄዉን ለምን እንደጠየቅኳት ከጠየቅኳት በኌላ ራሴም ግራ ገባኝ
”እሱ የቤቱ ጋርድ ነው የፈለገዉን እንዲያደርግ የቤቱ ሕግ ይፈቅድለታል ”
ወዲያው ያ ፈርጣማ አንዱን እየጠፈጠፈ ይዞት ወጣ
”እና እስከመቼ ….?”
አልኳት እየተጠፈጠፈ ሚፈራገጠዉን ልጅ አይቼ
”ምን እስከመቼ አለው እሱ ቢሄድም ሌላው ጉልበተኛ ይተካል … አየህ ምግብ ቤት ‘ሚሠሩ ሠዎች ቤታቸው እየሄዱ አይበሉም ከሚሠሩበት ምግብ ቤት ውስጥ ያለዉን ምግብ ይበላሉ … ልክ እንደዛ ነው :”
ሲጋራዋን ወርውራ
”አናግሬው ልምጣ ”
ብላ ተነሳች ስትሄድ መቀመጫዋን ቃኘት ሳደርግ የቅድሟ ሴት ዓይኖቼን አይታ እንደማሽሟጠጥ ብላ አብሯት ወዳለው ሠውዬ ዞረች ሠውዬው ጥምብዝ ብሎ ሰክሯል ይለፈልፋል ይጠጣል … ከዛ የሷን ጭን ይዳብሳል እያመናጨቀች እጁን ስትገፈትረው ምንም አይላትም ይስቅና ድጋሚ መጠጡን ያነሳል : ከትንሽ ቆይታ በኌላ ልጅቷ
”ይቅርታ ሳልጠይቅህ አመጣው ”
አለችና ድራፍትና ጅን ይዛ መጥታ ተቀመጠች
”ምንሽ ነው ? አይለኝም …”
”ምን አልሽው ?”
” ምን እለዋለሁ ምኔም እዳልሆንክና አንተ ይዘህኝ እንደማታድር ነግሬው መጣዋ …?”
ሲጋራ ጠይቃኝ አቀጣጠልኩላት

”ይዤሽ እንደማልሄድ በምን አወቅሽ ?”

”አወቅኩዋ !”
በወፍራም ሳቋ ጥያቄዬን ከአፌ ቀማችኝ
”…ይልቅ ስለጨረቃ ላውራልህ ሚሰማኝ አግኝቼ ስለማላውቅ እኮ ነው … ምክኒያቱም አንተ ደደብ አይደለህም ታስታውቃለህ … እናልህ ……ልጅ ሆኜ አባቴ በረንዳችን ላይ ይዞኝ ይወጣና ጨረቃን ያሳየኛል ስለኳክብት ይነግረኛል ….”
ትልና ምስጥ ብላ ወደ ሠማዩ አንጋጣ ትቀራለች ጨረቃዋ ደመና ውስጥ ተወሽቃለች ለዚች የምሽት ንግስት መፅናኛ ወይም መተከዣ ለመሆን የኮራች ይመስላል : ትኩር ብዬ ሳያት ጨቅላ ዕድሜዋ ፈክቶ ታየኝ
”ስንት ዓመትሽ ነው ?”
አልኳት ከሃሣቧም ለማባነን
”አሁን 18 ሞልቶኛል … ምነው ፂፂ ሆንኩብህ ….? ቀጫጫ ነኝ አይደል ? ግን ‘ኮ ተማመን የሆነ ሼፕ ነው ያለኝ ስማ ይሄንን ፉራ ማይቋምጥበት የለም ….ኽ ?”
እያለች ከተቀመጠችበት ወንበር ሠውነቷን ጋደል አድርጋ መቀመጨዋን ባንድ ጎኑ ብድግ አድርጋ እያዞረች አሳየችኝ ::ወዲያው ሀዘኗ ወደቀልድ ተቀየረ : ሳቅኩ
”ቆንጆ ነሽ :”
አልኳት
”አባቴ … ግን ‘ኮ ቁንጅናሽ ፈተና እናድይሆንብሽ እፈራለሁ … እያለኝ ነው የሞተው ”
የሆነ ስሜት ተሰማኝ : አሁን ጊዜ ማባከን አልፈለግኩም እየተጣደፍኩ ድራፍቱን ጠጣውና
”ይቅርታ አብረን ማደር እንችላለን ?”
አልኳት
”ከምርህ ነው ?”
አለች ፍጥጥ ብላ እያየችኝ
”አዎ … የጀመርሽልኝን ወሬ ለብቻችን ሆነን ትጨርሺልናለሽ እሺ …?”
ተያይዘን ስንወጣ ያ ወጠምሻ በቢጫ ዓይኖቹ ገላምጦ ሸኘን
”እንዴት ግን በፍራቻ ከማትወጂው ሠው ጋር ትተኚያለሽ ?”

”ምን ማለትህ ነው ነብሱ ከምወደው ሠው ጋር ተኝቼ አላውቅም መዋደድ ሚባለውን ነገር ሳላውቅ ነው የሸረሞጥኩት ”
ሽቶዋ መኪናዬን አጠነው
”የት ነው አልጋ የያዝከው ?”
ነገርኳት :
”ነጋዴ ነህ ?”
አለችኝ መኪናዬን በደንብ ቃኝታው
”አይደለሁም …ምነው ?”

”አማኑኤል ሆስፒታል ለቀሻል ብለው ያስተኙኝ ጊዜ እዛ የተዋወቅኩት አንድ ዶክተር ነበር ልክ ሳይህ እሱን መስለህኝ ነበር ”
(‘ኝለቀሻል ‘ ምትለዋን ቃል ስትጠራት በሌባ ጣቷ የአናቷን ጎን ጠቁማ አሽከረከረች /በጨ … ለማለት / ) አንዱን ርዕስ ጀምራ ወደሌላ የመሄዷን ነገር እያሰብኩት በአሕምሮ መታመም ምክኒያት ሆስፒታል መተኛቷን ስትነግረኝ እንደምፍራትም እንደ ማዘንም አደረገኝ : በርግጥ አሳዝናኛለች በጣም ታሳዝናለች : ገና በእምቡጥ ዕድሜዋ ተቀጥፋ ዝሙት ውስጥ መወርወሯ አሳዝኖኛል ::
ሆቴል እንደደረስን መጠጥ አዘዝኩኝ : መኝታ ክፍሌ ስንገባ ሲጋራ ተቀብላኝ አልጋው ጫፍ ቁጭ አለች : አሁን ትኩር ብዬ አያዋት ጉንጯ ላይ ጠባሳ አለባት ጥርት ያለች ቆንጆ ናት
”እስቲ ስለ አባትሽ ንገሪኝ …”
አልኳት ….. የሸሚዜን ሁለት ቁልፎች ከላይ ከፈትኩና ዘና ብዬ ከፊትለፊቷ እግሬን ደራርቤ ወምበሩ ላይ ቁጭ አልኩኝ
”አባቴ … ”
ፀጥ አለች ….. ከዛም አነባች :: ስቅስቅ ብላ አነባች

”ለምን ታለቅሺያለሽ ?”

”ብዙ ጊዜ ሃዘኔን ያዩ ሠዎች ሃዘኔን ጠይቀው እያነባው መጥፎ ትዝታዬን ስነግራቸው ‘ተባኖብሻል የእኛን ሆድ አባተሽ የሠው ሙድ ከስክሰሽ ሳትንፊ ልታመልጪ ነው ‘ እያሉ ቅጥቅጥ አድርገው እንደፈለጉ ያደርጉኛል ….”
ዕምባዎቿ ሲፈሱ አልጠረገቻቸዉም …………………. የመኝታ ክፍላችንን በር ቀብቅቅቦ ጥርሱ ያለውበት ከተማ ነዋሪነቱን ሚመሰክር አስተናጋጅ መጥጥና ብርጭቆዎች ይዞ መጣ ቀድቼ አቀበልኳት ቀጠለች ታሪኳን
”አባቴን ፊትለፊቴ ገደሉት … ወንድሜ አመለጠ … አባቴ ግን በደም የተለወሰ እጆቹን ዘርግቶ የኔን እርዳታ እየጠየቀ ሞተ … እናትም ጓደኛም ሆኖ ያሳደገን አባታችን …”
በእንባ ሙላት የቀሉ እነኚያ ዓይኖቿን ወደመጠጡ ስታይ ደገምኳት :
”ወንድሜንም ገለዉት ይሆናል አላውቅም ደደቦች አይደሉ … እኔን በዛ እድሜዬ ራሴን እስክስት ደፈሩኝ …”
ንግግሯን የሚያቋርጥ ሳግ ልቧን እያፈነው ሲጋራ ጠየቀችኝ ሰጠዋት መጠጥ ድጋሚ ስትጠይቀኝ ከለከልኳት …
”ይሄንን ሀዘኔን ልቀይርልህ ከፍለህ እስካመጣህኝ ድረስ በሀዘን የተጨማደደ ስሜት ማግኘት የለብህም … ”
እጆቿን ስትዘረጋ ከለከልኳት ታገለችኝ : ሠውነቷ ከሠውነቴ ሲነካካ አንዳች ስሜት ነዘረኝ ምናልባትም እሷ ደደቦች ብላ የሰየመቻቸው ዓይነት ድድብናን መውረስ የፈልግኩ መሰለኝ : እንደ እብድ ስትጮህ ጠርሙሱን አቀበልኳት ጠጣችው ፊቷን እያኮማተረች ጠጣች :
ከዚህ በኌላ ታሪኳን የመስማት ዕድሉ አልነበረኝም : ግን በጣም ተደስቺያለሁ : :
ሲነጋ የናዝሬት ፀሐይ በንፋስ ታጅቦ መኝታቤታችን ገባ :: ልብሷን ለባብሳ ወምበሩ ላይ ቁጭ ብላለች ስካሩ ሙሉ በሙሉ እንዳልለቀቃት ታስታውቃለች
”ምነው ?”
አልኳት ሠዓቴን እያየው
”ብር ስጠኝና ልሂድ …”
”የት ነው ምትሄጂው ገና ጠዋት እኮ ነው …”
”ተጠይፈህኝ ነው አይደል አንተ መሬት ተኝተህ ያደርከው ?”
እጆቿን አጣምራ በተቀመጠችበት እግሮቿን ትወዘውዛለች

”ይቅርታ ስምሽ ማነው ?”
አልኳት
”ስሜ ምን ያደርግልሀል … አሀ ለካስ ማታ ስሜን እንኳን አልጠየቅከኝም ”

ፊቷ ባንድ ጊዜ ቲማቲም መሰለ : ቆመች አንጠልጥላው የነበረ ቦርሳዋን አጥልቃው
”ለነገሩ ሁሉንም ነገር የማድረግም ያለማድረግም መብትህ ነው …. ግን … ግን …”
ስቅስቅ ያለ ለቅሶዋ ንግግሯን አቋረጠው
”…. ሠው ሚፀየፈኝ ያህል ደረጃ መድረሴ ታውቆኝ አያውቅም …”
ንግግሯ አስደነገጠኝ በእርግጥ ማታ ከስሜቴ ጋር ክፉኛ ስንሟገት ነበር በተለይ ከቦርሳዋ ውስጥ የሌሊት ልብሷን አውጥታ ፊትለፊቴ ስትቀይር ገላዋ ተገላልጦ ሳየው መስከር ፈልጌ ነበር ስክር ብዬ ራሴን ስቼ እዛ ገላ ውስጥ ተጣብቄ ማደርን ፈልጌ ነበር :
ለቅሶዋንም ለማባበል ተጠግቺያት

”ረጋ በይ ሂሩት ….”
ስላት ቦርሳዋን በቁሟ ለቀቀችው ዓይኖቿ ፈጠጡ
”ስ …ስ … ሜን እንዴት አወቅከው … በዚህ ስም …”
ስጠጋት ፈራችኝ ወደበሩ መሸሽ ጀመረች
”አትጠጋኝ ……. አትጠጋኝ … አን …ተ … ማነህ ?”

”ይሄውልሽ ሂሩት ቁጭ በይ ስለ ሁሉም አስረዳሻለሁ … እዚህ ናዝሬት የመጣውት አንቺን ፍለጋ ነው አንቺን ስፈልግ ወደ 3 ወር ፈጅቶብኛል … ወንድምሽ በሕይወት አለ እሱ እንድፈልግሽ ሠው ልኮብኝ ነው ….”

”ምን …….?”

”ውጪ አገር ነው ያለው …”
አልኳትና ደብዳቤዉን ከኪሴ አውጥቼ ሠጠዋት ማንበብ ቀጠለች …
‘ሂሩትዬ … ከአባታችን ገዳይ ውስጥ አንዱ ገለሽ መሠወርሽን ሠማው ………..’’

የተሠጠኝን ኃላፊነት በትክክል የተወጣውት መሠለኝ : ዛሬ ወንድሜ ጋር ደውዬ የሂሩትን ወንድም ማናገር አለብኝ : ከሸሚዝ ኪሴ ፎቶግራፏን ስሰጣት ደብዳቤዉን በለቅሶ አንብባ ጨርሰዋለች ….

ተፈፀመ

አባይ በአባዮች አስጨረሰን! በነጻነት ዘገዬ

The Nile River has become a point of contention between Egypt and Ethiopia.

( ከ’አባይ’ – ‘ባ’ ጠብቆ ይነበብ፤ ከ’አባዮች’ – ‘ባ’ ላልቶ ይነበብ (ዋሾዎች ለማለት ፈልጌ ነው፡፡)
ይድረስ ለተወደዳችሁ በውጭ ሀገራት የምትኖሩ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት እንዲሁም ይህን ጽሑፍ ልታነቡ የቻላችሁ ክቡራን የሰው ዘር አባላት በሙሉ፤
ብዙዎች ኢትዮጵያውያን በኃያል መቅሰፍትነቱ የምናውቀው ኢትዮጵያ ላይ የነገሠው የሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ መንግሥት ባጭር አጠራር ‹ወያኔ‹ በመባል የሚታወቀው የወንበዴ ቡድን እየሠራ ያለው ሕዝብን የማራቆት ሥራ ቢያንገበግበኝ ጊዜ ይህችን ማስታወሻ ለታሪክ መታሰቢያት ለመጻፍ ተነሳሁ፡፡ አሁን በምንጽፈውም ሆነ በምንናገረው ነገር ለጊዜው ምንም ዓይነት ፍርድ የምናገኝ አለመሆናችንን ብንረዳም እንደነዚህ ተመዝግበው በሚቀመጡ ታሪካዊ ማስታወሻዎች መነሻነት አጥፊዎች የሥራቸውን እንዲያገኙና ሌሎች ተረኞችም አሁን ከምናሳልፈው ግላዊም ይሁን ማኀበራዊ የሕይወት ገጠመኞች ልምድ ቀስመው አካሄዳቸውን እንዲያስተካክሉ ስለሚረዳ እንደዚህ በአደባባይ መጮሃችን ለጊዜው አስፈላጊነቱ አነስተኛ መስሎ ቢታይም ለወደፊቱ በእጅጉ ጠቃሚያችን መሆኑ የሚካድ አይደለም፡፡

በግርድፍ ግምት ከዘጠና በመቶ በላይ የሚሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከከፋ የድህነት ወለል በታች በሚኖርበት በአሁኑ ወቅት ችግር የሚባል ሲያልፍ የማይነካውና ስለችግር ምንነትም አንዳችም ግንዛቤ ያለው የማይመስለን የወያኔ መንግሥት በአባይ ግድብ ምክንያት ሕዝቡን በየአቅጣጫው እየዘረፈ ነው፡፡ የወቅቱ አንገብጋቢ ጥያቄ ‹ከዚህ በገንዘብ ፍቅር ለይቶለት ካበደ የወያኔ መንግሥት ማን ይታደገን?› የሚለው ነው፡፡

አሁን ህመሙ ባሰበትና ከነአካቴው ቅጥአምባሩ ጠፋበት እንጂ ቀድሞም ቢሆን የወያኔ ጎጠኛ የዘራፊዎች ቡድን የሚሠራው ሥራ ሁሉ ጤናማ መንግሥት ይሠራዋል ተብሎ የሚጠበቅ አልነበረም፤ አይደለምም፡፡ የአሁኑ ግን እጅግ የከፋ ሆኖብናል፡፡ ዜጎች በተለይም አነስተኛ ገቢና ጥቃቅን መተዳደሪያ ያለን በበርካታ ሚሊዮኖች የምንቆጠር ወገኖች የግፉ ቀንበር ሸክሙ ከብዶብን መድረሻ አጥተናል፡፡ እባካችሁ ተሰሚነት ያላችሁ ወገኖቻችን ለሚመለከተው ሁሉ ጩሁልን፡፡

በመሠረቱ እንደወያኔ ያለ አጭበርባሪና ሌባ መንግሥት ሳይሆን ሁነኛ የሕዝብ መንግሥት በሀገራችን ሥልጣን ላይ ወጥቶ በምክክርና በሕዝባዊ ይሁንታ ላይ በተመሠረተ ሁኔታ ለአንድ ግድብ ቀርቶ ለበርካታ የኒኩሌየር ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ግንባታ(ለሰላማዊ አገልግሎት) አዋጡ ቢባል አንድም ሰው አይከፋውም – በደስታ ጮቤ ይረግጣል እንጂ እንዲያውም፡፡ የአሁኑ የወያኔ ዓላማ ግን ለሀገርና ለሕዝብ ተጨንቆና ተቆርቁሮ ወይም ተጠብቦ ሳይሆን ሕዝብን በ‹ፍቅሩ› ለማማለልና ውዴታን ለማግኘት ታስቦ ከመሆኑም በተጨማሪም የሃሳቡን መነሻ ጊዜ ስናጤነውና የአብዛኛውን ሕዝብ የኑሮ ሁኔታ ስንቃኘው እንኩዋንስ ለግድብ ማሠሪያ አዋጣ ሊባል ከእጅ ወደአፍ መሆንም አቅቶት በርሃብ አለንጋ እዬተገረፈ ባለበት ሁኔታ የሚገኝ በመሆኑ ይህን ሕዝብ አፅሙን መጋጥና መቅኒውን መምጠጥ ወንጀል ብቻ ሳይሆን ይቅርታና ሥርየት የሌለው ኃጢያት መሆኑን በቀላሉ መገንዘብ የሚያዳግተው ጤናማ ዜጋ የለም፡፡ ይህን አለሁህ ባይ የሌለውን ሕዝብ በግላጭ አገኘሁት ብሎ ይህን ያህል መጨከን የዞረ ድምር እንዳለውና ለልጅ ልጅ የሚተርፍ አበሳ እንደሚያስከትል የወያኔው መንግሥት ቢረዳ ለሁላችን በበጀን ነበር፡፡ እንዲህ ሕዝብን አስለቅሶ እንደዋዛ ተሸሽጎ መቅረትና ተደብቆ ዓለምን መቅጨት የማይታሰብ መሆኑን እነዚህ ሕዝብ አስለቃሽ ወሮበሎች ሊገነዘቡም በተገባቸው – አእምሮኣቸው በጊዜያዊው ዓለማዊ ደስታ ባይታወር ኖሮ፡፡ የሂትለር ጀሌዎች በዘመናቸው በሠሩት ጥፋት የተነሣ እስከቅርብ ጊዜ ድረስ በዓለም ዙሪያ ከየተደበቁበት እየታደኑ ካረጁ ካፈጁ በሁዋላም ቢሆን ለፍርድ ሲቀርቡ ማየታችን ለዚህ እውነት አንዱ ማስረጃችን ነው፡፡

በአሁኑ ወቅት ለዚህ መከረኛ ግድብ የምናዋጣበት መንገድ በጣም ብዙ ነው፡፡ እኔ ለምሳሌ በመሥሪያ ቤቴ የአንድ ወር ደመወዜ በአንድ ዓመት ውስጥ ተቆርጦ ገቢ እንዲሆን በግድ አስፈርመውኛል፡፡ አካሄዱ እንዲህ ነው፤ ስብሰባ ተጠራን፡፡ የመሥሪያ ቤታችን ዋና አለቃ በይምሰልና በሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ የልግጫ ፈገግታ ተሞልቶ እንዲህ ብሎ ስብሰባውን ጀመረ፤‹ በእውነቱ በዚህ መሥሪያ ቤት ሠራተኞች እንደዛሬ ኮርቼ አላውቅም፡፡ በየዲፓርትመንታችሁ ተወያይታችሁ ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ለአባይ ወንዝ የአንድ ወር ደመወዛችሁን በአንድ ዓመት ውስጥ ለመስጠት መወሰናችሁ ማኔጅመንቱን በደስታ አስፈንድቆኣል፤ ኩራትም አላብሶናል፡፡ … › አድርባይነት ማለት እንዲህ ነው፡፡ ድርጅታዊ አሠራር ማለትም እንደዚህ ነው፡፡ ደርግን ‹በየት ዞረህ ቀደምከኝ?› ብሎ መጠየቅ አሁን ነው – እንደአለቃ ገ/ሃና ቀልድ፡፡ ሁሉም ሠራተኛ አንገቱን ደፍቶ ከአዳራሹ ወጣ – ምርጫ አልነበረውም፤ ጎልያድን በአንደበት ብቻ መጋፈጥ ትርፍ እንደሌለው ከተረዳን ሰነበትን፤ ሌላ ዘዴ መቀየስ ነው የሚያዋጣው፡፡ ወንበዴን በቃላት እሩምታ ማሸነፍ እንደማይቻል ተገንዝበናል፡፡ ወሮበላን ለመርታት የመናገር ችሎታ ብቻ ሳይሆን ውሃ የማያሰኝ ወፍራም ዱላም መያዝ ግድ የሚልበት ጊዜ አለ፡፡ እንዶድ በየዋህነትዋ ወንዝ እንደወሰዳት ለመረዳት የ97 ምርጫን ማስታወስ በቂ ነው፡፡ ያኔ አላሳን ወተራዊ ሥልት ተጠቅመን ቢሆን ኖሮ ዛሬ መለስ ዜናዊ ድመት የአይጥ ግዳይዋን ከመብላትዋ በፊት እንደምትጫወትባት ዓይነት የፉገራ ጨዋታ አይጫወትብንም ነበር፡፡

በነገራችን ላይ የሚሰማንን በገሃድ አውጥተን አለመናገራችን ለወያኔው የተስማማው ይመስላል፡፡ መጥፎነቱ ጫካውን ሁሉ ናፍጣና ቤንዚን እያርከፈከፉ ሳይቀር በሰደድና በጋያ አቃጥለውና መንጥረው ስለጨረሱት ጫካ የለም እንጂ ከኩርፊያው መረዳት እንደሚቻለው ብዙው ሠራተኛ በምናቡ ‹ፋኖ ተሠማራ› የሚል ይመስላል፡፡ ጥቃት መጥፎ ነው፡፡ እንደጥቃት ውስጥን የሚያቃጥል ነገር የለም፡፡ በእውነቱ ሁሉም እዬተቃጠለ ነው፡፡ ምን ማድረግ እንደሚችልም ግራ የተጋባው ዜጋ ብዙ ነው፡፡ በቁምህ ካለውዴታህ ቆዳህን ሲገፉት ስታይ፣ በአራቱም አቅጣጫ ስታማትር የሚደርስልህ አንድም ሰው ስታጣ፣ ተስፋህ ይመነምንና ቅስምህ ይሰበራል፡፡ ወያኔዎች ቅስማችንን ብቻ አይደለም እዬሠበሩት ያሉት ፤ የኀልውና እስትንፋሳችንንም እዬዘጉት ናቸው፡፡ ‹እኔ እምሞት ዛሬ ማታ፤ እህል እሚደርስ በፍልሰታ› እንደተባለው የአባይ ግድብ እውነት እንኩዋን ቢሆን አሁን የምንቀምሰውንና የምንልሰውን አጥተን እነሱው በፈጠሩት የኑሮ ውድነት እየተቆላን እያለን እንደዚህን ያህል ወርደው ኢሰብኣዊ ከሆኑ ዕንባችን ይፋረዳቸው እንጂ ለጊዜው ምንም የምንለው ነገር የለንም፡፡ ግን ወዮ ለቀናቸው! ቀናቸው ሲደርስ ይገቡበትን ቀዳዳ ያጣሉ፡፡

በመሥሪያ ቤቴ ብቻ አይደለም የሚገፉኝ፡፡ (‹ፉ›ን በሁለቱም አገባብዋ ልትወስዱዋት ትችላላችሁ፡፡) በትምህርት ቤት በልጆቼም እንዲሁ ተገድጄ የተጠየቁትን ብር ዛሬ ጥዋት ልኬያለሁ፡፡ በሠፈር ነዋሪነቴም መጥተውብኛል፡፡ በዕድርም ገና ይመጣሉ፡፡ በምገብርባቸው የመንጃ ፈቃድና ሌሎች ካርዶችና መታወቂያ ወረቀቶችም እንደሚመጡ ግልጥ ነው፡፡ እነሱ እንደሆኑ በጽዋ ማኀበሬም ሳይመጡብን አይቀሩም፡፡ አንዴውኑ በወጥመዳቸው ገብቻለሁና ካልሞትኩላ(ባ?)ቸው እንደማይለቁኝ ተረድቻለሁ፡፡

በመሠረቱ ወያኔ ማለት መርዝ ማለት ነው፡፡ የመርዝነት ደረጃውም ኃይለኛው የአናኮንዳና የኮብራ ወይም የእፉኝት ዓይነት ነው፡፡ የወያኔዎች ንድፊያ በምንም ዓይነት መንገድ መድኃኒት አይገኝለትም፡፡ ብቸኛው መዳኛ መንገድ የሕዝብ አንድነትና እምቢ ለነጻነቴ ባይነት ነበር፡፡ ያ ግን እስካሁኒትዋ ቅጽበት በተግባር ሊታይ አልቻለም፡፡ እነሱም የሕዝቡ አለመተባበርና ተለያይቶ መሰባበር የልብ ልብ ስለሰጣቸው ይሄውና ያሰኛቸውን ከማድረግ አልተቆጠቡም፡፡ ዘረፋቸውም ቅጥ አጥቶ የገንዘብ ፍቅር አንድያውን አራዥቶኣቸዋል፡፡ አያያዛቸው ሲታይ በቀላሉ የማይወጡት አፍቅሮተ ንዋይ ውስጥ ተዘፍቀው ራሳቸውም አብደው ሕዝብንም እያሳበዱ ለመሆናቸው በግልጽ የሚታይ ሆንዋል፡፡ እግዚኣብሔር ይሁነን እንጂ አካሄዳችን በፍጹም አያምርም፡፡

እግዜር ያሳያችሁ እንግዲህ፤ ተማሪን ለግድብ ማሠሪያ ገንዘብ አምጣ ማለት ምን ማለት ነው? ከየትስ ያመጣል? ስንቱ ወላጅ ነው የልጆቹን ወስፋት ሳይሸነግል ባዶ ሆዳቸውን ት/ቤት የሚልከውና ምሣ ሰዓት አካባቢ በጠኔ (…) ኦ! ሌላ የቅንጦት ብሶት ላሰማችሁ ፤ ‹በጠኔ› ካልኩ በሁዋላ አሁን በዚህ አንቀጽ ውስጥ በቅንፍ ካስቀመጥኩት ነጠብጣብ በፊት ስንትና ስንት ነገር ጽፌ ነበር፡፡ ነገር ግን መብራት በመሄዱ ያ ሁሉ የለም፡፡ ‹በጠኔ› እስከሚለው ብቻ የጻፍኩትን አገኘሁ፡፡ ግዴለም እሱስ ይሙዋላል፡፡ ግና ተመልከቱ ችግራችንን፡፡ መብራት ያለማስጠንቀቂያ ሲፈልግ በየአሥር ደቂቃና ከዚያም በታች ወይም በላይ በሆነ የጊዜ ርዝማኔ እየሠራህ እያለ ሊጠፋብህ ይችላል፡፡ ለቀናትም ላይኖርህ ቢችል ተጠያቂ የለም፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ስትኖር አቡዋራና ትቢያ ነህ፤ ሰው መስለህ የምትታየው በአካል እንጂ በኅሊናዊ ኑባሬህ አይደለም፡፡ እናም እንኩዋንስ ‹መብራት ጠፍቶብኝ ጨለማ ዋጠኝ፣ ውሃዬ ጠፍታ ከነቤተሰቤ በጥም ሞትኩኝ፣ ስልኬ ተጠልፎ ባለዕዳ ሆንኩኝ ወይም በብልሽት ምክንያት አግልግሎት ተቁዋረጠብኝ› ብለህ ልትጮህና ልትደመጥ ቀርቶ እንዲህ በማለትህ ራሱ በቅንጦተኛ ባለአቤቱታነት ተወንጅለህ በጥቂቱ ይሳቅብሃል፤ አለበለዚያ ያልሠራኸው ወንጀልና ጥፋት ተፈልጎልህ ሸቤ ትገባለህ – ከ‹ስህተትህ እስክትማርና እንድትማርም›፡፡ በዚያ ላይ የመብራቱም፣ የውሃውም፣ የስልኩም፣ የነዳጁም፣ የሸቀጡም፣ የአገልግሎቱም፣ የምኑም የምናምኑም ታሪፍ በየጊዜው – በዬደቂቃው – ህልምና ቅዠታቸው በሉ ባላቸው ቁጥር – ጠጥተው ወይም ቅመው በመረቀኑ ጊዜ ገንዘብ የማግኛ ሥልት በነደፉ ቁጥር – ያንተን የድሃውን አቅም ባላገናዘበ መልክ ተመኑን ወደሰማይ ሽቅብ ያሽቀነጥሩትና – እንደወስፈንጠር ወደሰማየ ሰማያት እንደኩዋስ ያጉኑትና በቤትህ የነዚህን አገልግሎቶች አጠቃቀም ለመቀነስ ስትል ቤተሰብህን አፍነህ ለመያዝ ሁሉንም የእመቃ ዘዴዎች እንድትጠቀም ልትገደድ ትችላለህ፡፡ ለውሃው ተነቃይ ቁልፍ፣ ለመብራቱ ጭል ጭል የሚል ኃይል ቆጣቢ አምፖል፣ ለስልኩ አስተማማኝ ጉዋጉንቸር ገዝተህ እያንዳንዱን ትከረችምና ቤተሰብህን ማንጫጫት ትጀምራለህ፡፡ ወያኔ ከላይ አንተን ሲያንጫጫ አንተ ደግሞ በተራህ በሥርህ ያሉ ምሥኪኖች ሚስትህንና ልጆችህን እጥፍ ድርብ የሆነ መብረቃዊ ቁጣህን ታወርድባቸዋለህ – ምርጫ የለህማ! እቶናዊ የሲዖል ኑሮ ይሉሃል ይቺ ናት ታዲያ፡፡ ይህ ሁኔታ ግን ወያኔውንና አድርባይ ነጋዴውን አያካትትም፤ ሙሰኛውንና የወር ደመወዙን በወዳጅ ዘመዶቹ ልመና እዬተጉዋደደ የሚወስደውን ጉቦኛ አይጨምርም፡፡ ሀገር የሚሸጠውንና የሚያሻሽጠውን ወፍ ዘራሽ ትውልድ አይመለከትም፡፡ የወያኔው መንግሥት በሥሩ ያሉትን ዘበናይና ቅንጡ አጫፋሪዎቹንና ባስነጠሰው ቁጥር መሃረብ የሚያቀርቡለትን እንደነእንቶኔ ያሉ ሀብታሞችን የተንደላቀቀ ኑሮ እያየ በሚያወጣው ሕግና የዋጋ ጭማሪ የምንጎዳው እኛ ምንዱባኑ ተራ ዜጎች ነን፡፡ እኛን ለማየት ወደኛ ዝቅ ብሎ ችግራችንን መጠየቅና ኑሮኣችንን መመልከት ይገባል፡፡ አራት ኪሎ ቤተ መንግሥት ተቀምጦ ወይም በሚያማምሩ ሆቴሎች እየተንፈላሰሱ ‹ዕድሜ ለወያኔ፣ የኢትጵያ ሕዝብ አልፎለታል› ማለት ከለየለት ነፍሰ ገዳይነት የማይተናነስ ትልቅ ወንጀል ነው፡፡

ለማንኛውም የጀመርኩትን ሃሳብ ልቁዋጭና ብሶቴን ላብቃ፡፡ … ምሣ ሰዓት አካባቢ በጠኔ ምክንያት እዬተዝለፈለፉ በየት/ቤቶች ቅጽር ግቢዎች የሚወድቁትን የድሃ ቤተሰብ ልጆችን ሃያና ሠላሣ ብር አምጡ ማለት ምን ትርጉም ሊሰጠው ይችላል? በበርካታ ት/ቤቶች በበጎ ፈቃደኞች የተደራጁ የድሃ ቤተሰብ ልጆች ተማሪዎችን የሚመግቡ በጎ አድራጊ ግለሰቦችና ድርጅቶች አሉ፡፡ ከነሱ የምንሰማው ወሬ በሚዘገንን ሁኔታ ያስደነግጣል፡፡ አብዛኛው ተማሪ እንኩዋንስ ለግድብ ገንዘብ ሊከፍል ይቅርና የራሱም ነፍስ ከግድቡዋ ልትወጣና እስትንፋሱ በርሃብ ልታልፍ አንድ ሀሙስ ነው የቀራት፡፡ ተማሪውም ሆነ ወላጁ የግዳቸውን ነው የሞት ሞታቸውን በጠኔ እዬተንጠራወዙ የሚኖሩት፡፡ ‹እኔ እምሞት ዛሬ ማታ እህል እሚደርስ በፍልሰታ› ይባላል፡፡ ወያኔ የሚቀልድበትና የሚያፌዝበት የአባይ ግድብ ሥራ ተጠናቅቆ ኃይል ወደውጭ ሀገራት በመሸጥ ገንዘብ የምናገኝበት ጊዜ በዕቅዱ መሠረት ይከናወናል ቢባል እንኩዋ የዛሬ አምስት ዓመት ገደማ ነው፡፡ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ሁለት በመቶ የማይሆነው ተንደላቅቆ እዬኖረ ሰፊውን ድሃ ሕዝብ በዚያች ባለችው ሽርፍራፊ ሣንቲምና ለምኖም ሆነ ተመጽውቶ በሚያገኛት እጅግ አነስተኛ ‹ገቢ› የዕለት ጉሮሮውን እንዳይዘጋ ከሌለው ላይ እነኚያ በሚሊዮንና በቢሊዮን ደረጃ ያላቸው ኀሊናቢስ ዜጎች በፈረዱበት ግፈኛ ፍርድ ምክንያት የማይወጣው ዕዳ ውስጥ እየተዘፈቀ ይገኛል፡፡ ይህ የግፍ ግፍ ፍርድ እንደጤዛ የሚረግፍ ወይም እንደጉም የሚበንን ሳይሆን ተጠራቅሞ የልጅ ልጅ ድረስ የሚወራረድ የኃጢያትና የመርገምት ቁልል የሚያስከትል መሆኑን የአሁኖቹ የሀገር መሪ ተብዬዎች በቅጡ ሊገነዘቡት በተገባ ነበር፡፡ ግፍን ለትውልድ ማስቀመጥ ደግሞ ኩነኔ ነው፤ በቀጣይ ትውልዶች ክፉኛ ያስወቅሳል፡፡ የአሁኑን ትውልድም መቅኖ ያሳጣል፡፡

ስለዚህ የተወደዳችሁ በውጭ ሀገራት የምትኖሩ ወንድምና እህቶቻችን እባካችሁ ይህንን ብሶታችንን ሰው ለሆኑ ሰዎች አሰሙልን፡፡

ምሬታችን የሰማይን በሮች ከአንኩዋኩዋ ዘመን የለውም፡፡ ዕንባችን ኩሬና ምንጮችን ሞልቶ ሀይቅና ባህርም ሆኖ ወደ ውቅያኖሶች እየፈሰሰ ነው፡፡ በላያችን ላይ የወደቀው ወያኔያዊ የግፍ አገዛዝ ቀምበር ልንሸከመው ከምንችለው በላይ ሆኖብን ትከሻችን ጎብጦ እንደ ክርስቶስ ኤሎሄ ማለት ከጀመርን ሃያ ዓመት አስቆጥረናል፡፡ የእስካሁኑን ልቅሶና ዋይታችንን ያዳመጠን የለም፡፡ ለወትሮው ‹የእስራኤል አምላክ፤ የኢትዮጵያ አምላክ፤ የአንድዬ እናት ወለለዋ …› እያልን በራሱና በቅዱሳኑ አማካይነት የምንለምነው እግዚኣብሔርም የኃጢያታችን ብዛት ከኛ ስላራቀው ይመስላል ፊቱን ሊያዞርልን አልቻለም፡፡ የኛ እርግማን ለወያኔዎች እንደምርቃት እዬተቆጠረ ኃይላቸውና ብርታታቸው ሳይዝል በብረት እንደወገሩን እስካሁን አሉ፡፡ ከፍ ሲል ለመግለጽ እንደተሞከረው አንድ ብቸኛ መታደጊያችን የኛ መተባበርና በአንድነት መነሣት ነበር፡፡ አሁን ለጊዜው ግን ያ እውን እንዳይሆን የያዘን ነገር ያለ ይመስላል፡፡ ይህን እኛን የሚለያዩበትን ድግምት መሰል መሠሪ ተንኮላቸውንና ደንቃራቸውን በጋራ ሆነን መክረን መፍትሔ በመፈለግ ትብታባቸውን ካልሻርን ወይም ካላከሸፍን ወዮልን! ሌትና ቀን በሚያካሂዱዋቸው ስብሰባዎች የሚማከሩት ለኛ ሳይሆን የሚመሣጠሩት በኛ ላይ ነው፡፡ ከምድረ ገጽ ሊያጠፉን የቀራቸው ጊዜ በጣም ኢምንት መሆኑን ተረድተን አሁኑኑ አንዳች የመፍትሔ እርምጃ ልንወስድ ጊዜው ያስገድደናል፡፡ እየተፈራራንና አንዳችን አንዳችንን እዬተጠራጠርን ብዙ ጊዜ አባክነናል፤ ያም ሊቆጨን ይገባል፡፡ ከአሁን ወዲያ ግን የመጣው ይምጣ ይለይልንና በክቡር ሞታችን ክቡር ነጻነታችንን እንጎናጸፍ፡፡ ሞቱ እንደሆነ አሁንም ቢሆን አልቀረልንም፡፡ ተበታትነን በድህነትና በውርደት ከምንጠፋ ተባብረን ለብልጽግናና ለጋራ ዕድገት የክብር ሞትን እንሙት፡፡ በዚያውም የፍርሀትንና የትግስትን ገደብ ለነዚህ ፈሪዎች እናሳያቸው፡፡ ፈሪዎች ስል እውነቴን ነው፡፡ ፈሪ ብቻ ነው ያሸነፈውንና ጠላቴ ነው ብሎ የፈረጀውን ካሸነፈውም በሁዋላ እንኩዋን ማሸነፉን ስለማይተማመን እስከመጨረሻው የሚያሰቃዬው፡፡ ወያኔ ጀግና ቢሆን ኖሮ ኢትዮጵያ ይሄኔ የት ትደርስ ነበር? ብለን መጠየቅ እንችላለን፡፡ እንደውነቱ ከሆነ ጀግና መሐሪ ነው፤ ጀግና ታጋሽ ነው፤ ጀግና ባገኘው ድል በከንቱ አይታበይም፤ ጀግና አብሮ የሚበላና የሚጠጣ ትሁትና በቃኝን የሚያውቅ እንጂ እንደወያኔ ስግብግብና እሱቅ ውስጥ እንደገባ ሕጻን በዓይን ዐዋጅ ሁሉንም እኔ ልውሰድ የሚል ባሕርይ የለውም፡፡ ጀግና በራሱ ስለሚተማመን ‹እንዲህ ባደርግ እንዲህ ያደርጉኝ ይሆናል› በሚል ከንቱ ጥርጣሬና የራስ ሥሪት ዓለም ውስጥ ተቀምብቦ ዕድሜ ልኩን በምርኮኞቹ ላይ ተንኮል ሲሸርብና ሤራ ሲጎነጉን አይኖርም፡፡ ስለዚህ ወያኔ አንድም የጀግንነት ባሕርይ የሌለው የተራ ወሮበሎችና ወንጀለኞች ጥርቅም መሆኑን ለማጠየቅ በግድ ፍርድ ቤት ሄዶ ነቃሽ መቁጠርና ማስመስከር አያስፈልግም፡፡ ወያኔዎች ከሕዝብ ተዘርፎ በተገኘ ገንዘብ የተገዛ የፈሪ ዱላ አላቸው እንጂ ሌላ የአስተዳደር ዕውቀትም ሆነ ጥበብ፣ ፈሪሃ እግዚኣብሔርም ሆነ ሰብኣዊነት፣ ሕጋዊነትም ሆነ ፍትሃዊነት ፈጹሙን የላቸውም፡፡ እነሱ የቀን ጅቦችና ዓሣማዎች ናቸው፡፡ አእምሮም ሆነ ኀሊና የሚባል ነገር አልፈጠረባቸውም፡፡ ከአፍ እስካፍንጫ የማያስብ ትንሽዬ የዶሮ ጭንቅላትና እንደፊኛ የሚለጠጥ እምብርት የሌለው አንዳች እሚያህል ቀፈት ብቻ ነው ያላቸው፡፡ በዚህ ማንም ይወራርድ – ያሸንፋል፡፡ የሁሉም ዓሣሞች አንደበት መለስ ዜናዊ ነው፡፡ እሱ ባለብላቢት ምላሱ እንደሥራዬ ቤት ነገርን እየመለሰ እዬቀለሰ ያሸሙርላቸዋል፤ በአግቦ መግነጢስና በድርቅና እንዲሁም በ‹ሞኝ እንዴት ያሸንፋል?› ቢሉት ‹እምቢ ብሎ› ዓይነት የሞኝ ጉልበተኞች ፈሊጥ እየተመራ ተቃዋሚዎቻቸውን ያነጉድላቸዋል፤ በብልጥነትና በመሠሪነት ከመለስ ያነሱቱ ሌሎቹ የምርም ሆኑ የተጋቦት ወያኔዎች በትልቁ ጋንኤል በመለስ ዜናዊ ብብት ሥር ተወትፈው በርሱ ቡራኬ ሀገሪቱን ይመዘብራሉ፤ በእጃቸው የገባን ገንዘብ ወደውጭ ያሸሻሉ፤ ባገር ውስጥም ሕንጻና ፋብሪካ ይገነባሉ፡፡ ነገም ሌላ ቀን ነው፤ እስኪ ሲኖሩበት ያሳየን … ቻው፡፡

ወቅታዊ ልዩ ማሳሰቢያ፤ ምዕመናን እባካችሁ ለማንበብና ያነበባችሁትን ላላነበበ ለማካፈል አትሰልቹ! ጊዜው ደርሶኣል፡፡ የመኸሩ ወቅት እዬተቃረበ መሆኑን የሚያመላክቱ ከዋክብት በሰማይ ላይ እየታዩ መሆናቸውን ‹ዐውደ ነገሥቱ›ንያነበቡ ሊቃውንት እዬጠቆሙ ስለሆነ ከፖለቲካችን ብዙም አንራቅ፡፡ ከሀገር እንዴት ይራቃል? እናት ሀገር እንዴት እስከወዲያኛው ትተዋለች? ኩርፊያው ይብቃንና ለራሳችን ጉዳይ እኛም እንደሚያገባን ተገንዝበን ቀጥተኛ ተሣታፊ እንሁን፡፡ ‹ሲሞቅ በማንኪያ ሲቀዘቅዝ በዕጅ›ንም እናስወግድና በሙሉ ልብ ለአንድ ዓላማ እንረባረብ፡፡ ያገር ጉዳይ ለጥቂቶች ብቻ የሚተውአለመሆኑንም እንረዳ፡፡ አክብሮት ከሞላበት ምሥጋና ጋር፡፡
(netsanetzegeye3@gmail.com)

በግላቸው የሚሰሩ እንዴት ለጡረታቸው ገንዘብ ማጠራቀም ይችላሉ? – ጉዳዩ ለትናንሽ ድርጅቶች የሚሰሩትንም ያጠቃልላል

ከዮሃንስ አለማየሁ
በዚህ ጽሁፌ ለግላቸው የሚሰሩ ሰዎችና የትንንሽ ድርጅቶች ባለቤቶችና ሠራተኞች ለጡረታ ጊዜ የሚሆናቸውን ሃብት ለማጠራቀም ምን ማድረግ እንዳለባቸው አንዳንድ ሃሳቦችን ለመጠቆም እወዳለሁ:: በመጀመሪያ ከዚህ በላይ የጠቀስኳቸው የህብረተሰባችን አባላት ለጡረታ የመዘጋጀት ጥቅሙን በመጠኑ እጠቁማለሁ።

1. ለመንግስት የሚከፍሉትን ቀረጥ ለመቀነስ ወይም ጭራሽ ለማስወገድ
2. ለጡረታ የሚሆናቸውን ሃብት ከሌላው ሃብታቸው በመለየት ከግልም ሆነ ከድርጅት ጋር ከተያያዘ እዳ ለመከላከል
3. ለቤተሰቦቻቸው ከድርጅታቸው ወይም ከሥራቸው ጋር ያልተያያዘ የጡረታ ጊዜ የሃብት ዋስትና ለመስጠት
በተለይ የግል ድርጅት ባለቤቶች የሚሰሩላቸውን ሠራተኞች ለጡረታ እንዲዘጋጁ በመርዳት ሥራቸው ላይ እንዲቆዩ ማበረታታትና በሚያገለግሉበትም ህብረተሰብ አካባቢ ጥሩ ሃሳቢና ደግ በመባል የበለጠ ደንበኞችን ለመሰብሰብ ይረዳል።
ጥቅሞቹ በከፊሉ ከላይ የተጠቀሱት ከሆነ በግላቸው የሚሰሩ ሰዎችን የትንንሽ ድርጅቶች ባለቤቶችና ሰራተኞች ለጡረታ ለመዘጋጀት የምጠቀሙባቸው ዘዴዎችን በከፊሉ እንደሚከተለው አመለክታለሁ። እነዚህ ሰዎች መጠቀም ካለባቸው የጡረታ ሃብት ሃብትማጠራቀሚያ ዘዴዎች ውስጥ ዲፋይንድ ኮንትሪቢውሽን (Defined contribution) በሚለው ውስጥ የሚጠቃለሉትን እናያለን።
Simplified Employee Pention (SEP):- በዚህ ዘዴ ለግላቸው የሚሰሩ ከገቢያቸው በዓመት 20%ን እስከ 45 ሺ ዶላር በ2009 እና እስከ 46 ሺ ዶላር በ2010 ለጡረታቸው ከታክስ ነጻ በሆነ መንገድ ማስቀመጥ ይችላሉ።
ለትናንሽ ድርጅት ባለቤቶችም ይህ ዘዴ ይጠቅማል፣ እሱም ከላይ የጠቀስኩትን መጠን ከገቢያቸው ቀንሰው ለጡረታ ማስቀመጥ ይችላሉ። የድርጅቱ ባለቤት በዚህ ዘዴ ተጠቅሞ ለራሱ የጡረታ ገንዘብ ካስቀመጠ ለሠራተኞቹም ከደሞዛቸው ከ1% – 15%የሚደርስና ከ24 ሺ ዶላር የማይበልጥ ለጡረታ የሚሆን ገንዘብ ማስቀመጥ ይገባዋል። ሠራተኛው ራሱ ተጨማሪ SEP ውስጥ ማስቀመጥም ይችላል። በዚህ ዘዴ የድርጅቱም ባለቤት ሆኑ ሠራተኞቹ የሚከፍሉትን ታክስ ይቀንሳሉ። SEP ለመክፈትና ለመጠቀም በጣም ቀላል ነው።
SOLO 401K:- በዚህ ዘዴ ለግላቸው የሚሰሩ ግለሰቦች በዓመት እስከ 46 ሺ እድሜ ደግሞ ከ50 በላይ ከሆነ እስከ 51ሺ ዶላር ለጡረታ ጊዜ ከታክስ ነጻ ማስቀመጥ ይችላሉ። በዚህ ዘዴ አነስተኛ ለሆኑ የግል ድርጅቶች የሚሰሩ ሰራተኞች በዓመት እስከ 10ሺ ከታክስ ነጻ የሆነ ገንዘብ ለጡረታ ማስቀመጥ ይችላሉ። በዚህ ላይ የድርጅቱ አሰሪ ወይም ባለቤት ከጨመረ (ማች ካረገ) የጡረታም ጊዜ ሲመጣ ብዙ ገንዘብ ሊሆን ይችላል።
ROTH IRAs:- SEP ወይም 401K ውስጥ ከሚያስቀምጡት ገንዘብ ሌላ ROTH IRAs ውስጥ በዓመት 4 ሺ (በ2007) እንዲሁም 5 ሺ (በ2008) ማስቀመጥ ይችላሉ። ሮት አይ አር ኤ ውስጥ ማስቀመጥ የሚችሉት ታክስ ከከፈሉበት ገንዘብ ላይ ስለሆነና ወደፊት ገንዘቡ ሳያድግ የሚያገኙት ትርፍ ላይ ምንም ታክስ ስለማይከፍሉ ጠቀሜታው በጣም ከፍ ያለ ነው። ስለዚህ ይህ የጡረታ ሃብት ማከማቻ ዘዴ በጣም ተመራጭ የሆነ ዘዴ ነው፤
Payroll Deduction IRAs:- አነስተኛ ድርጅቶች ውስጥ የሚሰሩ ሰዎች በዚህ ዘዴ ከደሞዛቸው እየተቆረጠ በዓመት እስከ 2000 ዶላር ከታክስ ነጻ የሆነ ገንዘብ ለጡረታ ጊዜ እንዲሆናቸው ማስቀመጥ ይችላሉ። ይህን ዘዴ ለመጠቀም አይ አር ኤ አካውንት መክፈትና ከደመወዝ ተቆራጭ በማድረግ እንዲቀመጥ ማድረግ ብቻ ስለሆነ ቀላል ግን የአሰሪዎችን በጎ ፈቃድ የሚጠይቅ ነው።
ከላይ የዘረዘርኳቸው ለግላቸው ለሚሰሩም ሆነ ለትናንሽ ድርጅቶች ባለቤቶችና ሰራተኞች ለሆኑ ግለሰቦች የጡረታ ጊዜ ሃብት ማከማቻ ይሆናሉ ብዬ ያሰብኳቸውን ምክሮች ነው። እነዚህ ዘዴዎች ሁሉንም ያጠቃለሉ ባይሆኑም ዋና ዋናዎቹና ለኛ ህብረተሰብ ይጠቅማሉ ያልኳቸው ናቸው። ተጨማሪ ምክር ለማግኘት በዚህ መስክ እውቀቱና ልምዱ ያላቸውን በማነጋገር ታክስ የሚከፍሉትን በመቀነስና ለጡረታ ጊዜ የሚያስፈልጎትን ሃብት በሚገባ ማከማቸት ይችላሉ።
__________________________________________
* አቶ ዮሃንስ አለማየሁ በሙያቸው ሲ ፒ ኤ የሂሳብ ሰራተኛ ሲሆኑ ለአንድ ፎርቹን 100 ትላልቅ ኩባንያዎች ካላቸው ለአንዱ ተቀጥረው በመስራት ላይ ይገኛሉ::S

ጥሩ የክሬዲት ነጥብ (ክሬዲት ስኮር) እንዲኖርዎት (ለማሻሻል) 5ቱ ቀላል መንገዶች

1. የክሬዲት ካርድም ሆነ ሌላ መንኛዉን ብደር በወቅቱ ይክፈሉ፡፡ 35 በመቶዉ የክሬዲት ስኮር የሚወሰነዉ በዚህ ስለሆነ ትልቅ አስተዋፅኦ አለዉ፡፡
2. እዳ አያብዙ፣ በክሬዲት ካርድዎትም ቢሆን ብዙ እዳ አያስቀምጡ፡፡ በተለይም በወሮቹ መጨረሻ አካባቢ (ሪፖርት በወር ነዉ የሚወሰደዉ) አነስተኛ እዳ ቢኖርዎት ይመረጣል፡፡
3. ሙሉ በሙሉ የተከፈሉ ክሬዲት ካርዶችን አይዝጉ፡፡ የዚህ ጉዳት አጠቃላይ ያለዎትን የብድር መጠን ስለሚቀንስ ያለብዎት እዳ ካለዎት ጋር በፐርሰንት ሲታይ ይጨምራል፡፡ ይህም ያገኙትን ሁሉ የሚጠቀ ሙ ያስመስልዎታል፡፡
4. ብዙ ብድር ካለብዎት ከብድር ምክር አገልግሎት ድርጅቶች (አትራፊ ያልሆኑ) ምክር ይጠይቁ፡፡ ብዙ ድርጅቶች ድጋፍ እንሰጣለን ብለዉ ስለሚያስተዋዉቁ ለሌላ ‹‹ዝርፊያ›› እንዳይጋለጡ ይጠንቀቁ፡፡
5. በተቻለ መጠን ከኪሳራ (ባንክራፕሲ) ተጠበቁ፡፡ ይህ የክሬዲት ሂስትሪዎን በጣም የሚጎዳ ነዉ፡፡ አማራጭ ካልጠፋ በስተቀር መደረግ የለበትም፡፡ በፋይል ላይ እስከ 10 አመት ስለሚቆይ ህይወትን በጣም አስቸጋሪ ያደርጋል፡፡ የተሻለ አራጣ ለማግኘት ወሳኝ ስለሆነ ክሬዲታችሁን ተንከባከቡ፡፡

የአሜሪካን ሲትዝን ያላገኘ ሰው በድራግ ወንጀል ቢገኝ ምን ያጋጥመዋል?

አንዳንድ ወገኖቻችን እየተስፋፋ ባለው፤ መንግስትና ሕብረተሰቡ በጥንካሬ እየተዋጋው ባለው የአደገኛ እጽ (Narcotic drugs) እና የተከለከሉ መድሐኒቶች (controlled substances) መጠቀምና ይዞ መገኘት ወንጀል ውስጥ ተሳትፈው በመገኘታቸው በፖሊስ ተይዘው ምርመራው ተጣርቶ ለተገቢው አቃቢ ሕግ መ/ቤት (District Attorney office) ከተላለፈ በሁዋላ መዝገባቸው ለፍርድ ሸንጐ (Jury) ቀርቦ ክስ ስለተመስረተባቸው ፍርድ ቤት ቀርበው በአጋጣሚ አገኛቸዋለው ። በተለይ ደግሞ በጣም የማዝነው የአሜሪካ ዜግነትን ያልወሰዱ ወገኖቻችን ላይ የሚያስከትለው ጣጣ በጣም የከፋ መሆኑን ስለማውቅ ነው። ይሕንን በተመለከተ በዚሕ ውስጥ ያለውን የወንጀል ሕግ (criminal law) ከስደተኞች ህግ (Immigration Law) ጋር በማገናዘብ ወደ ፊት በሰፊው የማቀርበው ሲሆን ለዛሬው ግን በወንጀሉ ዙሪያ አተኩራለሁ። ይህ ምክር በአደገኛ እጽ መያዝ ወይንም መጠቀም ለተከሰሰ ሰው ላይ ብቻ ሳይሆን በሌላ አይነት ወንጀልም ለተከሰሰ ሰው የሚረዳ ምክር ይሆናል።
በአደገኛ እጽ እና የተከለከሉ መድሐኒቶች ዙሪያ የሚሠራውን ወንጀል በመሉ የሚቆጣጠረው የህግ ክፍል የራሱ አንቀጽ አለው።
የተከለከሉ መድሐኒቶች (controlled substances) የሚለው አጠራር በጣም ብዙ የሆኑ በላቦራቶር የተፈጠሩና የተቀየሩ አደገኛ እጽ እና መድሃኒቶች ሲሆኑ በዋናነት የምንጠቅሳቸው ግን marijuana፣ cocaine (crack cocaine)፣ Methyl amphetamine (Meth) እና Heroine የመሳሰሉት ናቸው ።
አንዳንድ ሰዎች በዚህ ዝርዝር ውስጥ ጫት መታቀፉ ወይንም አለመካተቱ ቢይደናግራቸውም እኔ በግሌ ባደረግሁት ጥናት ግን የሚኒሶታን ባላውቅም በምኖርባት ጆርጅያ ግዛት ውስጥ ያገኘሁት የሕግ ክፍል ወይንም የፍርድ ቤት ውሳኔ የለም። ስለሆነም በጆርጅያ ውስጥ ጫት የተከለከሉ መድሃኒቶቸ ወይንም አደገኛ እጽ ውስጥ አልተጠቀስም ብል መሳሳት አይሆንብኝም። በሚኒሶታስ? የህግ ባለሙያዎችን በቅርብ ያነጋግሩ።
በመጀመሪያ ደረጃ አደገኛ እጽ ወይንም መድሓኒት መጠቀም ለጤናና ሕይወት ጠር ነው ። በዚህ አባባል ላይ ከአብዛኛው አንባቢ አስተሳሰብ ጋር የምገጥም ይመስለኛል። በመቀጠልም እንደ አደገኛ እጹ ወይንም የተከለከለ መድሕኒቱ አይነትና መጠን፡ እንደ አጠቃቀሙ ወይንም ማስተላለፉ አይነትና ይዘው እንደተገኙበት ቦታ ቅጣቱም እየከበደ ይሄዳል ። ለምሳሌም በብዛት የያዘ ሰው፤ ሲሸጥ ወይንም ለሽያጭ ሲያዘጋጅ ከታየዘ ሰው ጋር ሲነጻጸር ወንጀሉና ቅጣቱ ከባድ ይሆናል ማለት ነው። ኰኬይን የያዘ ማሪዋና ከያዘው ወይንም ከተጠቀመው ወንጀሉና ቅጣቱ
ይከብዳል ማለት ነው። በመኖሪያ አካባቢ የያዘው በትምህርት ቤት አካባቢ ይዞ ከተገኘው ወንጀሉና ቅጣቱ ይቀንሳል ማለት ነው። በማንኛውም አይነት ወንጀል አደገኛ እጽና የተከለከለ መድሀኒት ይዞ ወይንም ሲጠቀም የተገኘውንም ሠውን ጨምሮ በፖሊስ በቁጥጥር ሥር በሚውልበት ጊዜ የእንግሊዝኛ ቋንቋ በሚገባ የማይናገርና የማይገባው ከሆነ አስተርጉዋሚ መጠየቅ፣ በመቀጠልም ምንም አይነት ቃል ለፖሊስ ከመስጠቱ በፊት ጠበቃ እንዲቀርብለት መጠየቅ፣ ጠበቃ ካልቀረበለት ምንም አይነት የእምነትም ሆነ የክህደት ቃል አለመስጠት አለበት። ፖሊስ ምርመራውን አጣርቶ ለተገቢው ዓቃቢ ህግ መ/ቤት (District Attorney) በሚያቀርብበት ጊዜ ተከታትሎ ጉዳዩ የተመራለትን ዓቃቢ ህግ መ/ቤት በማነጋገር ክስ ተመስርቶ ወደ ፍ/ቤት ከመተላለፉ በፊት በዓቃቢ ህግ መ/ቤት ውስጥ ከፍርድ ውጭ ጉዳያቸው በተለያዩ ፕሮግራሞች ውስጥ ተሳትፈው
ለሚያጠናቅቁና እራሳቸውን ለመቀየር ለተዘጋጁ ሠዎች የሚሠጠውን እድል ለመጠቀም ማመልከት አለበት።
እነኚህም መርሀግብሮች (pretrial diversion programs) ተብለው የሚጠሩት ናቸው። በመርሀግብሩ እንዲሳተፉ እድል ከተገኘ በሚገባ ተከታትሎ አጠናቆ የሚያረካ ማስረጃ ከተገኘ በኋላ የዓቃቢ ህግ መ/ቤት የግለስቡን የእሥር ሪፖርት (arrest record) እንዲደመሰሥና ከፋይል ውስጥ እንዲሰረዝ (expunge) ይደረጋል። ይህም የግለስቡን የወንጀል ታሪክ ለማወቅ ለሚፈልጉና ማጣራት ለሚያደርጉ መ/ቤቶችና ግለስቦች ምንም ዓይነት የወንጀል ሪኮርድ እንደሌለበት ያሳያል።ያም ሆነ ይህ ግን ፖሊስ፣ ዓቃቢ ህግና የፌደራል ፖሊስ (FBI) ይሀን የእሥር ሪፖርት የማየት መብቱና ችሎታው አላቸው።
ከላይ የተጠቀስው መንገድ ካልተሣካና ክስ ተመስርቶ ፍርድ ቤት በሚቀርቡ ጊዜ መንግሥት በጀት ይዞ ገቢያቸው
አነስተኛ የሆኑ ሠዎችን እንዲወክሉ ለተዘጋጁት የመንግስት ጠበቆች (Public Defender) ጉዳይዎን እንዲይዙለት ማመልከት ነው። ባለዎት የገቢ መጠን ምክንያት የመንግስት ጠበቆች ጉዳይዎን መያዝ የማይችሉ ከሆነ ግን በግልዎ ጠበቃ ማቅረብ አለብዎት ማለት ነው።
ለመጀመሪያ ጊዜ በአደገኛ እጽ እና የተከለከሉ መድሐኒቶች ወይንም በማንኛውም አይነት ወንጀል ክስ ለቀረበባቸውና መስፈርቱን ለሚያሞሉ ግለሰቦች እንደ ቅደም ተከተላቸው መሠረት የመጀመሪያ ጊዜ ወንጀለኛ (first offender treatment) መብት መጠቀም ይችላል።
በጆርጅያ የወንጀል ሕግ 16-13-2 መሰረት ለመጀመሪያ ጊዜ በአደገኛ ውጽ ወይንም በተከለከሉ መድሀኒቶች ይዞ መገኘት ወንጀል የተከሠሠ ሰው ፍርድ ቤት በሚቀርብበት ጊዜ ጠበቃው ይህንኑ መብቱን መጠቀም እንዲችል እንዲያመለክትለት ማስታወስ ይገባል። ይህንን መብት ለመጠቀም ሌሎች መሟላት ከሚገባቸውና ህጉ በዝርዝር ከሚያስቀምጣቸው መስፈርቶች በተጨማሪ ከዚህ በፊት በተመሳሳይ ወንጀል ተከሦ ይህንን እድል ተጠቅሞ መገኘት የለበትም። ጥያቄው የቀረበለት ፍ/ቤትም ተከሳሹን ከላይ በተጠቀሰው ሕግ የሚያስተናግደው ከሆነ ተከሳሹ ከዚህ በታች የተጠቀሱትን ጥቅሞች ያገኛል ማለት ነው።
ተከሣሹ በፍርድ ቤቱ የጣለበትን የእስር ወይንም በውጭ ሆኖ የተጣለበትን የቅጣት ገደብ እንዲጨርስ እድል ይሰጠዋል፣ የተጣለበትን ገደብ በሚገባ አጠናቆና መክፈል የሚገባውን ቅጣትና ክፍያዎች አጠናቆ ከጨረሰ፣ በማሕደሩ ላይ የተቀጣ ወንጀለኛ የሚል አይኖርም። ለማንኛውም ጉዳይ ቢሆን በፍርድ ቤት ተቀጥተኃል ወይንም ተወስኖብህ ያውቃል ለሚለው መልሱ በአሉታ (የለም) የሚል ይሆናል። የግለሠቡን የፍርድ ቤት ቅጣት (ወንጀል) ሪኮርድ ለማየት የሚፈልጉ ግለሰቦችና ድርጅቶች የሚያገኙት የፍርድ ውሳኔ አይኖርም። ከተወሰነ ጊዜ በኋላ እንደአግባቡ በአጠቃላይ የወንጀል ታሪክ ከፍርድ ቤት ማሕደር ውስጥ በአካል እንዲጠፋ ወይንም እንዲደመሰስ (expunge) መጠየቅ የሚቻልበት እድል ይከፍታል። ከማንኛውም የሥራ ወይንም የትምሕርት እድል በወንጀል ታሪካቸው ምክንያት እንዳይሰናከሉ ይረዳል።S

USA Citizenship Sample test in Amharic የአሜሪካ ዜጋ ለመሆን የቃለ መጠይቅ ፈተና ናሙና

1. የባንዲራችን ቀለሞች እነማን ናቸው? ቀይ፣ ነጭ ፣ ሰማያዊ
2. ባንዲራው ላይ ያሉት ኮከቦች ምንን ይወክላሉ? እያንዳንዱ የአሜሪካ አንዳንድ ግዛት (ስቴት)
3. በባንዲራው ላይ ምን ያክል ኮከቦች አሉ? 50
4. የኮከቦች ቀለም ምን አይነት ነው? ነጭ
5. በባንዲራው ላይ ስንት አግድም መስመሮች አሉ? 13
6. በባንዲራው ላይ ያሉት አግድም መስመሮች ምንን ይወክላሉ? የመጀመሪያወችን 13 ግዛቶች
7. በባንዲራው ላይ ያሎት አግድም በስመሮች ቀለማቸው ምን አይነት ነው? ቀይ እና ነጭ
8. በአሜሪካ (ዩናይትድ ስቴትስ) ውስጥ ስንት ግዛቶች (እስቴቶች) አሉ? 50
9. የፈረንጆችን ጁላይ (ሀምሌ) 4 ለምን እናከብራለን? የነፃነት ቀን ስለሆነ
10. የነፃነት ቀን የሚከበረው ከማን ነፃ መውጣትን አስመልክቶ ነው? ከእንግሊዝ
11. በለውጥ ጦርነት (ሪቮሉሽን ዋር) ጊዜ ከማን አገር ጋር ነው የተዋጋነው? ከእንግሊዝ
12. የዩናይትድ ስቴትስ (አሜሪካ) የመጀመሪያው ፕሬዜዳንት ማን ነው? ጆርጅ ዋሽንግተን
13. ባሁኑ ወቅት የዩናይትድ ስቴትስ (አሜሪካ) ፕሬዜዳንት ማን ነው? ባራክ ኦባማ
14. ባሁኑ ወቅት የዩናይትድ ስቴትስ (አሜሪካ) ምክትል ፕሬዜዳንት ማን ነው? ጆ ባይደን
15. የዩናይትድ ስቴትስ (አሜሪካ) ፕሬዜዳንትን ማን ይመርጥዋል? ኤልክትሮረል ኮልጅ
16. ዋናው ፕሬዜዳንት ቢሞት ማን ይተከዋል? ምክትል ፕሬዜዳንቱ
17. ሕገ መንግስቱ (ኮንስቲትዊሽን) ምንድን ነው? የሀገሪቷ ዋና/የበላይ መመሪያ ህግ
18. የህገ መንግስት መቀየር ምን ይባላል? የማሻሻያ ነጥብ (አመንድመንት)
19. በህገ መንግስቱ ውስጥ ምን ያክል ለውጦች/ማሻሻያወች ተደርገዋል 27
20. ሶስቱ የእኛ መንግስት ቅርንጫፎች እነማን ናቸው? ኤግዛኬቲቭ (ዋና መወሰኛ)፣ ሕግ ምክር ቤት (ጁዲካል)፣ ሕግ አርቃቂ (ሌጂስትሌቲቭ)
21. የመንግሰት የህግ አራቃቂ (ሌጄስቲሌቲቭ) ቅርንጫፍ ማን ነው? ኮንግረስ
22. ጉባኤ(ኮንግረስ) ከነማን የተውጣጣ ነው? የህግ መወሰኛ ምክር ቤት (ሴኔት) እና የተወካዮች ምክር ቤት (ሐውስ ኦፍ ሪፕረዘንታቲቭስ)
23. በዮናይትድ ስቴትስ (አሜሪካ) የብሄራዊ ህግ (ፌድራል) ማን ነው የሜያወጣው? ኮንግረስ
24. ኮንግረስን ማን ይመርጠዋል? የዩናይትድ ስቴትስ (አሜሪካ) ህዝብ
25. በኮንግረስ ውስጥ ምን ያክል የምክር ቤት አባላት (ሴናተሮች) አሉ? 100
26. አንድ የተመረጠ ሴናተር ምን ያክል ያገለግላል? 6 ዓመት
27. እርስዎ ከሚኖሩበት ግዛት ውስጥ ሁለት ሴናተሮችን ይጥቀሱ (ከሚኒሶታ Norm Coleman and Amy Klobuchar)
28. በተወካዮች ምክር ቤት (ሀውስ ኦፍ ሪፕሬዘንታቲቭስ) ውስጥ ምን ያክል ተመራጮች አሉ? 435
29. አንድ የሀውስኦፍ ሪፕሬዘንታቲቭ ተመራጭ ምን ያህል ጊዜ እንዲያገለግል እንመርጠዋለን2ዓመት
30. ለዩናይትድ ስቴትስ መንግስት የበላይ አካል (ኤግዛኬቲቭ) ቅርንጫፍ ተጠሪ ማን ነው? ፕሬዜዳንቱ
31. ፕሬዜዳንቱ ለምን ያክል ጊዜ ይመረጣል? 4 ዓመት
32. ለመንግስት ታላቁ የህግ መወሰኛ ክፍል ቅርንጫፍ ማን ነው? ከፍተኛ ችሎት
33. የከፍተኛው ችሎት ተግባራት እነማን ናቸው ህጎችን በተግባር ማስተርጎም እና መግለጽ
34. የዩናይት ስቴትስ ዋናው የመተዳደሪያ ህግ ምንድነ ነው? ሕገ መንግስቱ
35. ቢል ኦፍ ራይትስ ምንድቸው? የመጀመሪያወቹ 10 የህገ መንግስቱ ለውጦች (አመንድመንዶች)
36. የሚኖሩበት ግዛት (ስቴት) ዋና ከተማ ማነው? የሚኒሶታ ሴንት ፖል
37. የሚኖሩበት ግዛት የወቅቱ አስተዳዳሪ ማንው? Governor Tim Pawlenty
38. ዋናው እና ምክትል ፕሬዜዳንት ቢሞቱ ስልጣኑ ለማን ይሸጋገራል? ስፒከር ኦፍ ዘሀውስ (አፈ ጉባዔው)
39. የከፍተኛው ችሎት ዋና ዳኛ ማናቸው ? ዊሊያም ራንኮስትS

Share