February 28, 2024
8 mins read

ከመቅዳላ የተዘረፈውና ለጨረታ የቀረበው ቅርሳችን…!! ለጨረታው ቀረበው የመቅደላ ቅርሳችን ወደ ሀገሩ፣ ኢትዮጵያ እንዲመለስ ድምፃችንን በአንድነት እናሰማ!!

በተረፈ ወርቁ (ዲ/ን)

የኢትዮጵያ ታሪክ ትልቅ ባለውለታ የሆኑት የነፍሰ ኄር ፕ/ር ሪቻርድ ፓንክረስት ልጅ የሆኑት ዶ/ር አሉላ ፓንክረስት፤ በውጪ ሀገር የሚገኙ የኢትዮጵያ ቅርሶች አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ በመሆን እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ ባለፉት ጥቂት ዓመታትም በተለይ በመቅደላ ዘመቻ ወቅት በእንግሊዝና በሌሎች የአውሮፓ ሀገራት ተዘርፈው የተወሰዱ ቅርሶቻችንን በማስመለስ ረገድ ትልቅ ሥራ እየሠሩ ናቸው፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም የሠራ ባልደረባ ነበርኩበት ጊዜ እንደማስታውሰውም፤ ወላጅ፣ አባታቸው ፕ/ር ሪቻርድ ፓንክረስት (ባለቤታቸው ሪታ ፓንክረስት)፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት የነበሩት ፕ/ር አነድርያስ እሸቴ፣ የታሪክና የቅርስ ጥበቃ ምሁራን፣ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ወዳጆች ማኅበር፤ በሀገር ውስጥና በውጪ ሀገር በሚገኙ የኢትዮጵያ ታሪክና ቅርስ ተቆራቋሪ በሆኑ ወዳጆች በተቋቋመው AFROMET በተባለ ድርጅት አማካኝነት- የዐፄ ቴዎድርስ ክታብ፣ የጸሎት መጽሐፋቸው፣ ጎራዴያቸውና ሌሎች ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው ነበር፡፡

እነዚህ በመቅደላው ዘመቻ ተዘርፈው ወደ እንግሊዝ ተወስደው የነበሩና የተመለሱ ብርቅዬና ውድ የሆኑ ቅርሶቻችንም በአንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፤ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ቤተ-መዘክር ውስጥ ለሕዝብ ቀርበው እንደነበርም አስታውሳለሁ፡፡

ይህ የእነ ነፍሰ ኄር ፕ/ር ሪቻርድ ፓንክረስትና በሀገር ውስጥና በውጪ ሀገር ያሉ የኢትዮጵያ ታሪክና ቅርስ ተቆርቋሪዎች ጥረት ዛሬም ሳይቋረጥ- በፕ/ር ሪቻርድ ፓንከረስት ልጅ በሆኑት በዶ/ር አሉላ ፓንክረስት ቀጥሎ ባለፉት ጥቂት ወራትም በመቅደላ ዘመቻ የተዘረፉ ታቦታትን ጨምሮ የተለያዩ ቅርሶቻን ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ ተደርገዋል፡፡

ታቦታቱ በእንግሊዝ፣ የለንደን ቅድስት ማርያም ቤ/ክ በተደረገ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓት ለቤተክርስቲያኒቱ እንዲመለስም ተደርጓል፡፡

ሌሎች ቅርሶቻችንም በኢትዮጵያ እንግሊዝ አምባሳደር በሆኑት አምባሳደር ተፈሪ፤ ለቅርስ ጥበቃ ባለ ሥልጣን በአካል ተገኝተው ማስረከባቸውን ከመገናኛ ብዙኃን ተከታትለናል፡፡ ይህ ብዙዎቻችንን ከልብ ያስደሰተ፤ ይበል የሚያሰኝ ሥራ ነው፡፡

ይሁን እንጂ ከሰሞኑን ደግሞ፤ ከመቅደላ የተዘረፈ እጅግ የተዋበና በልዩ ጥበብ የተሠራ ጋሻ በአንድ ግለሰብ አማካኝነት ለጨረታ መቅረቡን ዶ/ር አሉላ ገልጸውልኛል፡፡

ይህ የኢትዮጵያ ቅርስ የሆነ ጋሻ ወደ ሀገሩ እንዲመለስም የቅርስ ተቆርቋሪ የሆኑ ሁሉ በቲወተር (በኤክስ) እና በሌሎች ሶሻል ሚዲያ የትስስር ገጾች ድማፃችንን እንድናሰማ የቪዲዮ መልእከት አስተላልፈዋል፡፡

ይህ ቅርስ፣ ጋሻ የኢትዮጵያውያን፣ የአፍሪካና የመላው ጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ተጋድሎ ትልቅ ትእምርት/ተምሳሌት ነው፡፡ ይህ ለጨረታ የቀረበውና ከ150 ዓመታት በላይ ያስቆጠረ ቅርስ ‹ጋሻ› በክብር ወደ ሀገሩ እንዲመለስ ለታሪካችንና ለቅርሶቻችን የምንቆረቆር ኢትዮጵያውን ሁሉ ድምፃችንን በአንድነት ሆነን ልናሰማ ይገባናል፡፡

ይህ የኢትዮጵያውያን ጥበብ የፈሰሰበትና እጅግ የተዋበ ቅርሳችን፤ ‹ጋሻ› የኢትዮጵያውያን፣ የአፍሪካና የመላው ጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ተጋድሎ ትልቅ ትእምርት/ተምሳሌት ነው ስልም በምክንያት ነው፡፡

አውሮፓውያን ቅኝ ገዢ ኃይላት ጥቁር ሕዝብ ከእንሰሳ ያነሰ ስብእና ያለው፤ የራሱ ታሪክ፣ ሥልጣኔ፣ ዕድገት፣ ባህል… ወዘተ. የሌለው ብለው ድመድመው አፍሪካን እንደ ቅርጫ ሥጋ ተቀራምተው ሕዝቦቿን በባርነት ሲያግዙ በነበረበት ዘመን- አንድ የጥቁር ምድር/የሐበሻ ንጉሥ፤ የቋራው አንበሳ/ዐፄ ቴዎድሮስ የእንግሊዝንና የአውሮፓውያንን መልእክተኞች እግረ ሙቅ ውስጥ አስገብቶ ራሷን ታላቋ ብሪታንያ እያለች ከምትጠራውና የዓለም 1/3 በቅኝ ከምትገዛው ሀገር ጋር እኩል መደራደሪያ እድርገዋቸው ነበር፡፡

መላው አፍሪካና ጥቁር ሕዝብ በባርነትና በቅኝ ግዛት ቀምበር ስር ወድቆ ሲማቅቅ ነበረበት ወቅት የሐበሻው ጥቁር ንጉሥ፤ ዐፄ ቴዎድሮስ ሁላችንም በፈጣሪ ፊት እኩል ነን፤ በሚል መርሕ ራሳቸውን ከሁሉም በላይ ነን ብለው የሚያስቡትን አውሮፓውያንን/ነጮችን- በኢትዮጵያውያን የነጻነት እሳቤና ከፍ ባለ የመንፈስ ልእልና ድል በማድረግ ለአፍሪካና ለመላው ጥቁር ሕዝቦች የነጻነትና የጀግንነት ኩራት ሆነዋል፡፡

ይህ ከመቅዳላ ተዘርፎ ለጨረታ የቀረበው ቅርሳችን- ‹ጋሻ› የዚህ ኢትዮጵያዊነት የነጻነት እሳቤ፣ የሰው ልጆች እኩልነት መገለጫና የመንፈስ ልእልና ትእምርት/ምልክት ነውና ቅርሳችን ወደ ሀገሩ፤ ኢትዮጵያ እንዲመለስ፤ ከዶ/ር አሉላ ፓንክረስትና ኬሎች ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ጋር በአንድነት ሆነን ድምፃችንን እናሰማ!!

የዶ/ር አሉላ ፓንክረስት ከመቅዳላ ተዘርፎ የነበረና ለጨረታ የቀረበውን ቅርሳችንን/ጋሻ  ወደ ሀገሩ እንዲመለስ ሁላችንም በጋራ ድምፃችንን እንድናሰማ የቪዲዮ መልእክት ያስተላለፉበት ሊንክ እንሆ!!

ሰላም ለኢትዮጵያ!!

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የነበረው እና አሁን ላይ በአማራ ፋኖ በጎጃም የሁለተኛ (ተፈራ ) ክፍለጦር ሰብሳቢ የነበረው ፋኖ ዮሐንስ አለማየሁ በክብር ተሰዋ። የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን የህሎና አደጋ ለመቀልበስ ያለ

ከአማራ ፋኖ በጎጃም የተሰጠ የሐዘን መግለጫ ታጋይ ይሰዋል ትግል ይቀጥላል !

January 22, 2025
ዳግማዊ ጉዱ ካሣ “ይድረስ ለእገሌ” ማለቱ ሰለቸኝና ተውኩት እንጂ ዛሬም መጻፍ የፈለግሁት የአማራን ዕልቂት ለመታደግና የኢትዮጵያን ትንሣኤ ለማብሰር እየተዋደቁ ላሉት ወገኖቼ ነው – በፋኖም ይሁን በሌላ ስም፡፡ ኢትዮጵያን ወደቀደመ ክብሯ ለመመለስ የነገድና

ጀልባዋ አትሰምጥም፤ የሚሰምጥ ግን አለ!

[ማስታወሻ ከፍል አንድ፣ በዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ ኦፍ ጃዋር አንድ ኢትዮጵያ ተብሎ በእንግልዝኛ ወጥቷል] (https://zehabesha.com/of-jawar-and-ethiopia/) ባለፈው ሰሞን፣ ጃዋር መሐመድ ከደረጀ ኃይሌ ጋር  በነገራችን ላይ ክፍል ሁለት ባደረገው ቃለ ምልልስ ላይ ተመስርቼ ገንቢ አስተያየት ጽፌ በኢንግሊዝኛው ዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ አሳትሜ ነበር። አስተያየቴ በዚህ ቃለ ምልልስ

ስለ ጃዋርና ኢትዮጵያ (ክፍል ሁለት)

January 20, 2025 ጠገናው ጎሹ የአቤ ጎበኛው አልወለድም ለወገኖቹ መብት መከበር ሲል ባደረገው ጥረት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ይሙት በቃ በፈረዱበት ጊዜ በምላሳቸው መልካም  አድርጎ ስለ መገኘት እያወሩ በድርጊት ግን ተቃራኔውን የሚያደርጉ ሁሉ

ወዮ ለመከረኛው የአገሬ ህዝብ እንጅ  ታየማ ታየ ነው

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

Go toTop