የኮሬ ነጌኛ: በኦሮሚያ ክልል ለሚፈፀም ከሕግ ውጭ ግድያ

በኦሮሚያ ክልል ለሚፈፀም ከሕግ ውጭ ግድያ እና እስራት አንድ ከፍተና የባለስልጣናት ሚስጥራዊ ኮሚቴ ትዕዛዝ ሲሰጥ መቆየቱን ሮይተርስ የዜና ወኪል ገለፀ

በኢትዮጵያ የከፍተኛ ባለሥልጣ


ናት የሚስጥራዊ ኮሚቴ፣ብዙ ህዝብ በሚኖርበት የኦሮሚያ ክልል፤ አማጽያንን ለመደምሰስ በሚል ከሕግ አግባብ ውጭ ግድያ እና ሕገወጥ እስራት እንዲፈፀም ትዕዛዝ ማስተላለፉን የሮይተርስ የምርመራ ግኝት አመልክቷል።

ሮይተርስ በዚህ ምርመራው ከ30 በላይ የፌደራል እና የአካባቢ ባለስልጣናትን ፣ዳኞችን፣ጠበቆችን፣በባለሥልጣናት እና በደል የሚደርስባቸውን ሰለባዎች ማነጋገሩን ጠቁሟል።
የዜና ምንጩ በሀገር ውስጥ ፖለቲካ እና የፍትህ ባለስልጣናት የተነደፉ ሰነዶችንም መገምገሙንም አስታውቋል።ከእነዚህ ቃለ መጠይቆች እና ሰነዶችም በኦሮምኛ ቋንቋ «ኮሬ ነጌኛ»ወይም የደህንነት ኮሚቴ የሚባለውን አካል አሠራርን ይፋ የሚያደርግ መረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ መገኘቱን የዜና ምንጩ ገልጿል።
እንደ ሮይተርስ የፀጥታ ኮሚቴው በኦሮምኛ ቋንቋ ፤«ኮሬ ነጌኛ» ሥራ የጀመረው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡ ከወራት በኋላ ሲሆን፤ከጎርጎሪያኑ 2018. ዓ/ም በፊት ግን ኮሚቴው አለመኖሩን ዘግቧል።
አምስት የአሁን እና የቀድሞ የመንግስት ባለስልጣናት ነገሩኝ ብሎ ሮይተርስ እንዳሰፈረው፤ ይህ ኮሚቴ ዓላማው የራስን እድል በራስ ለመወሰን ለዓመታት የዘለቀውን የኦሮሞ ነፃ አውጪ ጦር የሽምቅ ውጊያ እንዲያበቃ ማድረግ ነው።
ከሮይተርስ ከአምስቱ ምንጮች አንዱ የቀድሞ የብልፅግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ሚልኬሳ ገመቹ ሲሆኑ፤ እሳቸውን ጨምሮ አምስቱ ባለስልጣናት እንዳሉት ፤ በጎርጎሪያኑ 2019 ዓ/ም አዲስ የኦሮሞ ህዝብ አመፅ ሲቀሰቀስ ጠንከር ያለ እርምጃ በመውሰድ ይህ ኮሚቴ የመሪነት ሚና ነበረው።
የኮሬ ነጌኛ እንቅስቃሴዎችን የሚያውቁ ሰዎች በኮሚቴው ትዕዛዝ በርካታ ግድያዎች ተፈጽመዋል። በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እስር ተካሂዷል ሲል ሮይተርስ ባወጣው ዝርዝር የምርመራ ዘገባ አመልክቷል።
Dq
ተጨማሪ ያንብቡ:  የአማራው ስቃይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ በወያኔ ኦነግ የዘር ማፅዳት ዘመቻ - ተድላ አስፋው

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share