ዶ/ር ራሄል ባፌ እውነቱን አፈረጡት!

ብልፅግና ወያኔ የጎደለው ኢህአዴግ ነው:: አቤል ወንድሙን ወያኔን ገሎ ወያኔን መሆን ያማረው ቃኤል ነው:: ብልፅግና ኦነግና ኢህአዴግ ወያኔ ስልቻና ቀልቀሎ መሆናቸውን ከሰሜን እስከ ደቡብ፤ ከምዕራብ እስከ ምስራቅ ያሉ ኢትዮጵያውያን አሳምረው ያውቃሉ::
ጠ/ሚ አቢይ አህመድ አጭበርባሪና ውሸታም (deceptive & liar) መሆናቸውን የማያውቁት እራሣቸው ብቻ ናቸው:: ለዚህ ነው ዴሞትፎር ጠመንጃ ከግምጃ ቤት በማውጣትና በመደርደር “ሸወድኳቸው” እያሉ ጅል መንጋዎቻቸውን በጅልነት የሚያዝናኑት!
ጋሽ ፀጋዬ ገ/መድህን ‘እንቁራሪቶች አብዝተው ስለጮሁ ባህሩ ውስጥ ሌሎች እንሠሣት የሉም ማለት አይደለም’ ያለው ትዝ ይሏል!
አጨብጫቢ አክቲቪስቶችን ብቻ ሣይሆን ሆድ አደር ጋዜጠኞችን እያየን ነው::
ይሄው ነው!/ HT
ተጨማሪ ያንብቡ:  የህዝብን ሥሥ ስሜት ተጠቅመው በአቋራጭ ለመቶጀር (ቱጃር ለመሆን) የሚቅበዘበዙ የዚህ ትውልድ አባላት አደብ ግዙ ሊባሉ ይገባል!

2 Comments

  1. ራሄል ባፌ ፈረጡ እንጂ ያፈረጡት ምንም የለም። “አቤል ወንድሙን ወያኔን ገሎ ወያኔን መሆን ያማረው ቃኤል ነው” አባባላቸው ወሬ ከማሳመር ውጪ ፍሬ አልባ አባባል ነው። ሟች አቤል ነው፤ ገዳይ ቃየል ነው። በባፌ አባባል የሞተው ወያኔ ነው፤ ወያኔ ቃየል ነው፤ የገደለው ዐቢይ/ብልጽግና ነው፤ ዐቢይ አቤል ነው፤ አሁን ተመልሶ ወያኔን/ቃየልን መሆን ይመኛል። ራሄሊት የት እንዴት ይሆን “ዶ/ር” ማዕረግ ያገኙት?

  2. ሴትዮዋ የህወአት አባል በወንጀል የሚፈለጉ ተካትተዋል ማለታቸው ስህተቱ ምንድነው? ማን እንደጠቆማቸው አይታወቅም አቦይ ስብሃትም ተጠቁመው ይህ ነገር እሳት ያስነሳል በለው መቅረታቸው ይሰማል። ጋዜጠኛው ካድሬው ጠያቂ ለሆዱ ካደረ ቆይቷል። ጥያቄ ጠይቆ ማስጨረስ ሲገባው ሙግት ይዟል።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share