መልዕክት ለዘሐበሻ ድህረ ገጽ አንባባያን

ዘሐበሻ ድህረ ገጽ ሰሞኑን በብልጽግና ፓርቲ አመራሮች መካከል የተነሳውን የውስጥ ቅራኔ አስታኮ የአብይ ቡድን ተላላኪ በመሆን አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን ነጥሎ የተከፈተው ሥም ማጥፋት አካል እንደሆነ ተደርጎ በስህተት ሲጠቀስ አይተናል። አቶ ገዱን አስመልክቶ በዌብሳይታችን የተጠቀሰው አይነት ተልዕኮ ያነገበ ሥም ማጥፋት ዘመቻ አካል አይደለንም። አላደረግንም።

በቅንነት የዘሐበሻ ዌብሳይት የከፈተው ዘመቻ መስሏችሁ የወቀሳችሁን አንባቢያን ስለ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ምንም አይነት የስም ማጥፋት ዘመቻ አካል እንዳልሆንን በዚህ ማስታወሻ እንደምትረዱ ትስፋ እናደርጋለን። ዌብሳይትችን እንደ ሁልጊዜው የተለያዩ ነገሮችን እያስተናገደ ለአገር እና ሕዝብ ጥቅም እንጂ ገዢዎችን ለማስደሰት ወይም ለማስከፋት የቆመ አለመሆኑን ዛሬም ለክቡራን አንባቢያን ያሳውቃል።
አልዩ ተበጀ
የዘሐበሻ ዌብሳይት ማኔጂንግ ዳይሬክተር

https://zehabesha.com/contact/

ተጨማሪ ያንብቡ:  Hiber Radio: ሜክሲኮ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን በነጻ ቪዛ ወደ አሜሪካ እንዲገቡ አደረገች | የፕ/ት ትራምፕን ስደተኞች እንዳይገቡ የሚያግደው ውሳኔ በከፊል በአገሪቱ የፌዴራል ፍርድ ቤት ታገደ

8 Comments

  1. You are doing a great job. Do not pay attention to the destructors.

    Thank you for your wonderful services.

  2. ዘ፡ ሃበሻ የምተስሩትን ሁሉ ስለምናውቅ በዩትውብ ወሬ መደናገጥ የለባቹሁም የሚሰሩት ለገንዘብ እንጅ ለአገር ክብር አደለምና

    በርቱ ዘሐበሻ ድህረ ገጽ አዘጋቾች

  3. ይህ አስተያዬት በቀጥታ የሚያተኩረው በ03/07/2022 በሹክሹክታ ፕሮግራማችሁ ላይ ያቀረባችሁት “ሹክሹክታ” ላይ ነው፡፡

    ሄኖክ/ዘሀበሻ አንዳልጦህ የአብይ የሳንቲም ጉርሻ አሳነቀህ!!!!
    የአብይ አህመድየጭን ገረድ እስከሚመስልበት ድረስ ጅራቱን ለአብይ አህመድ በሚቆላው በብርሀኑ ነጋ በኩል የተከፈልህ የብይ አህምድ ሳንቲም አንቀህ አይደል? አፈር ድሜ ብላና ብትንሿከክ ብትንሿከክ በቆፍጣናው ገዱ ላይ ትንሿከካለህ?? አይ ውርዴት!!! አብይኮ የማያበላሸው ሰውና ድርጅት የለም!! ገዱ በተለያዩ አመታት በተለያዩ አውዶች፣ መድረኮችና ሁኔታወች ውስጥ ሆኖ የተናገራቸውን ሰፍቶ ቀጣጥሎ ማቅረቡ ሌላ ማንንም ሳይሆን እናንተን ዘሀበሻውችን አውርዷችኋል፡፡
    ለመሆኑ የአባይ ግድብ ስምምነትን በሚመለከት የዋሽንግተን ዲሲውን በአሜሪካ ተዘጋጅቶ የቀረበውን የ””ባርነት”” ስምምነት ገዱ አንዳርጋቸው በልኡኩ መሪነቱ አልፈርምም ብሎ እንዳጨነገፈባቸው ረሳችሁትን?? ገዱ ያን ጊዜ ግብጾችም አሜሪካኖችም አስፍስፈውበሴራ የተሞላው ስምምነትን ራሳቸው አርቅቀው እንዲፈረም ያቀረቡትን አገራችንን የሚጎዳና የሚያዋርድ አሳሪ ስምምነት ያከሸፈባቸው እንደዚህ ብሎ ነበር፡፡”” እኔ ከዚህ እድሜዬ በኋላ የአገሬን ክብርና የህዝቤን ጥቅም የሚያዋርድ ፊርማ አልፈርምም “”ብሎ ነው ፍርጥም እንጥላቸውን የበጠሰው፡፡ የነበሩ ሰወች ምስክሮች ናቸው፡፡ አሁን እናንተ ያንን ሰው ነው አራጁ አብይ አህመድና አማራ ጠሉ ብሀኑ ነጋ ጋር ተመሳጥራችሁ እያንሾካሾካችሁበት ያለው፡፡፡ ወራዶች ናችሁ!!
    እየተተፋችሁ ከመሄድ ለመዳን የሚያዋጣችሁ ገዱንና ሰፊውን ህዝብ በይፋ ይቅርታ ጠይቃችሁ ወደህሊናችሁ ብትመለሱ ነው፡፤ ባለቀ ጊዜ ከሀዲው አብይ አህመድ ጉያ ውስጥ ገብታችሁ አትንከላወሱ፡፤46 ሚሊዮኑ የአማራ ህዝብ እስካሁን የነበሩት አመራሮቹ ስህተቶችን የሰሩ መሆኑን ቢረዳም አሁን ነገሩ እንደዚህ እየተባባሰ ሲመጣ ቆፍጠን ብለውና ተስተካክለው ከህዝባቸው ጎን ከቆሙት እንደ ገዱ አንዳርጋቸው አይነቶቹ ጋር በአንዲንነት ይቆሟል!!! ፋኖንንም በሆድ አደሮች አያስነካም፡፡ ይዋደቅለታል፡፡አብይ ፋኖን ትጥቅ ማስፈታት በሚል ከንቱና የማይሳክ ምኞት ጥቂት ራሳቸውን ከህዝቡ ማአበል ማዳን የማይችሉ እንደነ አገኘሁ ተሻገር፣ ደመቀ መኮንን፣ ተመስገን ጥሩነህ የመሳሰሉትን ሆዳሞች ይዞ አማራን እርስ በእርሱ የማጨፋጨፍ አዲሱ ሴራው የትም አያደርሰውም፡፡ በተጣደ ድስት ላይ እሳት/ማገዶ መቆስቆስ ማለት ነው፡፡ ይህ አማራን የማገዳደል ተንኮሉ መልሶ እራሱን ይለበልበዋል፡፤ መውደቂያውንም ያፋጥንለታል!!!

  4. (this comment is strictly on SHUKSHUKTA aired on 03/07/2022)

    zehebesha:- You are already a sold out media to OROMUMA using Berhanu Nega’s dealership!!!
    Sad to know this. Your SHUKSHUKTA topic today on Comrade Gedu Andargachew is a betray! It is a business you dealt with OROMUMA!!!!
    Did you forget that it was Gedu Andargachew who refused to sign the agreement on Nile Dam in Washington DC prepared by the mediator Blinken & company?? Did you forget that he proudly said that “”after reaching this age, I do not have no reason to betray my country & therefore I do not sign this draft agreement”” . He proudly said it out in-front of all parties. This decisive stand of Gedu buried the Nile Dam conspiracy right there. t is undeniable that Gedu has played many wrong roles that failed the Amhara people in his long years service during EPRDF era. But no comparison to his present firm stand of saying “NO” to the killer Abiy Ahmed Ali!! Gedu is a real Amhara and our hero!!!

  5. Zehabesha website is very reliable and depenable information provided on almost every subject imaginable from Human Rights, Options, scholarly articles, Biography,, history, others, I used it as an archive site

  6. I think some people don’t know the groups of zehabesha. There are two zehabesha services; one managed by Alyou Tebeje and the other by Henok Alemayehu. Alyou’s zehabesha is this site and deals with articles and etc. whereas that of Henok’s deals solely on youtube. There is now misundetstanding. It is not Alyou who presented the case of Degu A in whatever financial dealings with Oromuma or Guraguma. So ይቺኛዋን መተንፈሻችንን ለቀቅ – በሉ ተብለው የሚታሙትን ጠበቅ ከድርጉ እንጂ በቃላቸው የቆሙትን አትጨምሩ። ለነገሩ ያልፈሱበት ምንትስ አያፍሩበትምና በዚህ ሃሜት የማደኘግጥ አይኖርም። ከተሳሳትኩ ለመታረም ፈቃደኛ ነኝ፤ በተለይ ከዘሀበሻ ድረገፅ።

  7. አሁን ማን ይሙት ሹክሹክታና የአልዩን ዘሃበሻ ምን አገናኘውና ነው የዚህን መልካም ድረገፅ ስም የምታጠፉት? ካልጠፋ ዌብሳይት? ብዙ የምንማማርበትና ወያኔዎች ሳይቀሩ የሚተነፍሱበትን ሃቀኛ ሚዲየም? ደግሞስ የአቶ ገዱን ሆነ የአቶ ለማን ውለታ እንዴት ይረሳል? ሲጀመር ሹክሹክታን ማን ስሙ አላችሁ ሃሜት መስማት ካልፈለጋችሁ በቀር? ስንት አገራችንን የሚያስጨንቅ ጉዳይ እያለ? ለምሳሌ የነ ጄ/ አበባው የ ሁለተኛው ዙር መዘግየት ያስጨንቀኛል። ለምን? ይቺ አሜሪካ የሆነ እነ አቢቹን የምታስፈራራበት ጉዳይ ቢኖር ነው ብዬ አስባለሁ። አየርመንገዳችንን ለምሳሌ በኖርዝአሜሪካና አውሮፓ እንዳይበር ማእቀብ ብታስደርግብን ድፍን መቶሚሊዮን ህዝብ ዛሬ ለዘይት እንዲህ የተራኮተ ምን እንደሚሆን አስቡት በዚህ በከፋ ዘመን። ኸረ ተው ወገን ብዙ የሚያስጨንቁ ጉዳዮች አሉና እየታሰበ ቢሆን መልካም ነው። አልዩም ሃሜትን ቁምነገር አርገህ ማስተባበያ አያስፈልግም ። ሹክሹክታን ካንተው ድረገፅ ካልለዩ ችግሩ የነሱ እንጅ ያንተ አይሆንም ። ይህው ነው!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share