“ጊዜና ትውልድ ገና የሚያከብረው ኢትዮጵያዊ” ገዱ አንዳርጋቸው!!

ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ ( ለንደን)

የለውጥ ጉዟችንን ማዳን እንጅ ማዳከም አያስፈልግም !!

የሰው ልጅ ቢኖርም ባይኖርም በምድር ላይ አድ ግዜም ቢሆን ታሪክ ሰርቶ የራሱን እውነት ቋጥሮ ነፃ ህሌና ይዞ ለዘላለም በታሪክ ፊት ሳይሸማቀቅ ይኖራል ::

ብቻ የትም ይሁን መቼ ታሪክ ከመቃብር በላይ ነውና አፈር ሳይለብስ እንደዚህ ፀሐይ በጥዋት እንደ ጨረቃ በለሊት ደምቆ ይታያል: :

ታሪክ ይዋል ይደር እንጅ ድፍርሱ ንጋት ሲጠራ ለዛሬው ህይዉታችን ለነገው ፈራሽ ስጋችን ምስክርኑቱን ሰጥቶ እውነት ቦታዋን ትይዛለች: :

ለዛሬው ብዕሬን ያስጨበጠኝ የእንደመሩ አብዮት ማሀንዲስ የለውጡ የጀርባ አጥንት ሆነው በሁለት ጎራ የተከፈለውን የወያኔ ኢሀድግ የፓለቲካ ድርጅት አንገዳግደው ከጣሉት የመጀመሪያው ደፋር የእንደመር አብዮተኞች አንዱ” የአማራው ጄኔራ” በመባል በቅፅል ስም የሚጠሩት ገዱ አንዳርጋቸው ናቸው: :

አሁንም አቋማቸውን ግልፅ አድርገው እንዲህ አሉ: :

*** ” “በቀረችኝ የህይወት ዘመኔ ህዝቤን ለዳግም ባርነት አልዳርግም! ፋኖ ትጥቅ ይፍታ የሚለውን የብልፅግናን አካሄድ አጥብቄ እቃወማለሁ ” *** ::

ወደድንም ጠላንም ገዱ አንዳርጋቸው በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በዲሞክራሲው ግንባታም የራሳቸው አሻራ ያስቀመጡ ጠንካራ ፓለቲከኛም ቢሆኑም የለውጡን የጠ/ሚኒስትር አብይን ቡድን ደምና ስጋ ለብሶ ቆሞ እንዲሔድ ካደረጉት የለውጡ አውራዎችም ትልቁን ድርሻ በባለቤትነት ይዘዋል : :

ከአርባ አመት በላይ ከአገር ውጭ የነበሩት ጨምሮ በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች. ወደ ሐገራቸው ተመልሰው ለሰላምና ለኢትዮጵያ አንድነት ለዲሞክራሲና ለልማት የድርሻቸውን እንዲወጡ ሆደ ሰፊው ገዱ አንዳርጋቸው የዶክተር አብይን የእንደመር አብዮት ተቀብለው

” የኦሮሞ ደም የአማራ ደም ነው ” በማለት ለ27 አመት በተጠናከረ የአፈናና የግድያ ጥፍር ነቃይ ስርአት የወደቀች ሐገራቸውን በህይወት ተወራርደው ጣና ኬኛ ብሎ የመጣውን የቲም ለማን ትውልድ በሰከነ አመራር ተቀብሎ. የወያኔን ስነ ልቦናዊ ጦርነትና የነበረከት ስምኦንን አሻጥር ተቋቁመው ቲም ለማን ፓርማ ውስጥ ያነገሱ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ናቸው : :

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሕወሓት እንዴት አደብ ይግዛ?

ከዚህ ባለፈም ገዱ ጠንካራ አቋምና የኢትዮጵያን አንድነት የሚመርጡ የገዘፈ ሰብእና ያላቸው ፓለቲከኛ እንደመሆናቸው ሁሉ በአያት በቅድመ አያትቶቻችን ደምና አጥንት የተገነባችውን ሐገር በጥቂት የጎሳ መንደርተኛ ፖለቲከኞች፣ ተሸራርፋ የተገጣጠመች አድርገው የሚቃርቡትን የዘመናችን ጅላጅል ቂሎ ሞሮዎችን አጥብቀው የሚተቹ የአማራን ሕዝብ አለኝታ “ፋኖን ” ትጥቅ ለማስፈታትና አማራን. በማሸማቀቅ አንገቱን ሊያስደፉት የሚያሴሩት ዘረኞች ጋር. ትንቅንቅ በመግጠማቸው ቅልብተኞቹ የዩቲፕ አመንዝራዎች በተለመደው የሶሻል ሚዲያ ጫጫታ ከፍተውባቸዋል : :

በእርግጥም ገዱ አንዳርጋቸው እንደሚሉት . ኢትዮጵያ፣እንደ ሐገር ለመፍጠር በሽሕ የሚቆጠሩ ዘመናት ጠይቀዋል: :

በሚሊዮን የሚቆጠሩ ህዝቦችም ደማቸውን አፍስሰው ፣ አጥንታቸውን ከስክሰውባታል: :

ኢትዮጵያዊያኖች ፣ የቋንቋን ድንበር ግድብ ዘልቀው የትውልድን ዋስትና አሻግረው አይተው አባቶቻችችን የመሰረቱልንን የጋራ ሀገር ለማቆየት አሁንም የገዱን መርህ ተከትሎ የአማራ ሕዝብ ከጎናቸው መቆምና ለገዱ አንዳርጋቸው መመከት ይገባዋል ::

ገዱ በተለያዬ ጊዜ ባቀረቧቸው ጠንካራ ሀሳቦች ውስጥ የአንድ ሐገር ልጆች እኩል እንክብካቤ እኩል ጥበቃ እኩል የጥቅም ተካፋይ.መሆን እንደሚኖርባቸው በተደጋጋሚ ሲናገሩ በመደመጤቸው በዘረኞች ጩልሌዎች እንዳይጠለፉ የአማራ አይኑን መግለጥ አለበት : : ኢትዮጵያውያኖች የዜግነታቸው መብት እኩል ሳይጠበቅና ፍትህና ርዕት ሳያገኙ. ሐገር የጋራ መሆኑ ቀርቶ የጥቂት ተረኞችና አምባ፣ ገነኖች፣ መሆኑ ማብቃት አለበት በለው. በፅኑ የሚያምኑ. ብርቱ ፓለቲከኛ በመሆናቸው ሰሞኑን. ቅጥረኛ ሸኔዎች በእሰጥ አገባ ተጠምደዋል ::

በእርግጥ ዜጎች እንደዜግነታቸው ተከብረው እንደሰው ኑረው እንደሰው በክብር ለማለፍ የሚችሉበት ሐገር ሳንዘናጋ ጠንክረን መስረቱን መጣል ያስፈልገናል. የሚሉት በሳሉ ትእግስተኛው ፣አርቆ አሳቢና፣ አስተዋዩ ፣ፓለቲከኛ ፣ገዱ አንዳርጋቸው :: የኢትዮጵያን ብሔራዊ ሉአላዊነት አላስነካም በሚል ፅኑ አቋማቸው በተለያዩ የኢትዮጵያ

ተጨማሪ ያንብቡ:  ነውረኛዋና ሰላይዋ ዝማም (ኢየሩሳሌም አርአያ)

ጠላቶች ስውር ሴራ እየተቀነባበረባቸው መሆኑን መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በአየነ ቁራኛ እየተከታተለው ይገኛል ::

ሆኖም ግን እውነት አትሞትም የሚሉት ገዱ አንዳርጋቸው ለመሰሉ፣ኩሩ ኢትዮጵያዊን ይህ ጌዜ ከባድ ቢሆንም

በህዝብ መከበርና መወደድ መታቀፍና የህዝቡን ስነ ልቦና መግዛት መቻልን ይጠይቃል: : የዘረኛ ስርአት የእድገቱ ምልክቶች አንዱ ቢሆንም በደመቀ መኮነንና በገዱ አንዳርጋቸው ላይ. አማራን የማግለል ጥላቻ. ተጀምሯል :: በዚህ ምክኒያት በሐገር ወዳዱ ኢትዮጵያዊ ገዱ አንዳርጋቸው ላይ ከአውሮፓ እስከ ሰሜን አሜሪካ. በድጅታል ወያኔዎች አማካኝነት የስም ማጥፋት ዘመቻ ቢከፍቱባቸውም ብርቱው ፖለቲከኛ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ንቅንቅ አላሉላቸውም : :

በዚህ የሀገር ሉአላዊነት አደጋ ላይ በወደቀበት አስቸጋሪ ወቅት

ሴራው ተቀነባብሮ እውነት ከሆነ ግን የአማራን ልጅ ቀኝ እጁን ቆርጦ እንደመጣል ይቆጠራል ::

ስለሆነም ገዱ አንዳርጋቸውን በተለያዩ ፌስ ቡኮችና በዩቲዩብ ጡረተኞች አማካኝነት የአማራ ተቆርቋሪ በመምሰል የተከበረ ስማቸውን ለማጠልሸት ” ታላቁ ሴራ በድጅታል ወያኔዎችና በኦነግ ሸኔ ቅጥረኞች ዘመቻው ተጀምሯል ::

ኢትዮጵያ ከገዱ አንዳርጋቸው ገና ብዙ አገራዊ ለውጥን መጠበቋ አይቀሬ ቢሆንም የተቀነባበረባቸው ሴራ በቆራጥ ኢትዮጵያዊያኖች ተጋድሎ እንደሚከሽፍም ፍፁም ጥርጥር የለኝም ::

ሁላችንም ገዱ አንዳርጋቸው ነን ::

አበቃሁ በሌላ ዝግጅት እስክንገናኝ ቸር ይግጠመን: :

አለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)

 

4 Comments

  1. ብዙ የተበላሹ ነገሮች አሉ፡፤ በፊት በወያኔ አሁን ደግሞ በኦሮሙማው ቁንጮ አብይ አህመድ የሚዘወረው የኢትዮጵያ ጠላቶች አካሄድ አሁን ላይ አዲስና ለየት ያለ አቀራረብን ይዞ ብቅ ብሏል፡፤ የአሁኑ ስልታቸው ህዝባዊ ይዘት የነበራቸውን ሜድያወችና (ምሳሌ ዘሀበሻ) እንደዚሁም የህዝብ አንቂ የነበሩ (ምሳሌ ክንፉ አሰፋ) የመሳሰሉትን በአብይ አህመድ ወጥመድ አስገብቶ ሰፊ ተከታዮቻቸው የነበሩትን ሁሉ እያወናበዱ ወደኦሮሙማ ደጋፊነት ለመሳብ ከፍተኛ ስራ እየሰሩ ነው፡፡
    በተለይ ለዚህ የረቀቀ የእቡዩ የአብይ አህመድ ስታራቴጅ ዋናው ተዋናይ አማራ ጠሉና የፖለቲክ እርሾ አቡኪው ዶ/ር በርሀኑ ነጋ ነው፡፡ ከዘረፋውና ከጭፍጨፋው በተጨማሪ የእነ አብይ አህመድ ኦሮሙማ ግብ ኢትዮጵያዊነትን አጥፍቶ አገሪቱን ኦሮማዊት ማድረግ ነው፡፤ ለዚህም ግቡ አብይ አሁን ላይ ሁለት ጣምራ ጦሮችን እየወረወረ ነው፡፤ አንዱ ያሰበውን ውጤት እንደማያመጣለት ቢረዳም ሰውየው ጨካኝ ስለሆነ ፋኖን ትጥቅ ማስፈታት በሚል ሴራ አማራን በአማራ ለማጨፋጨፍ ነው፡፡ ሌላኛው ደግሞ አዲስ አበባን መሰልቀጥ ነው፡፡ አዲስ አበባን መዋጥ፣ የአድዋ ድልን ማደብዘዝ፣ የካራማራ ድልን አለመዘከር የኢትዮጵያ መሪ ነኝ (መሪ ነው አላልኩም) ከሚል ሰው የሚጠበቅ አልነበረም፡፤ የጅልና የቂል ስራ ነው የሰራው፡፡
    ክንፉ አሰፋ በዘሀበሻ ብቅ ብሎ ስይጠየቅ አዳነች አበቤን ህዝቡ መርጧታል ሲል ማረጋገጫ ሰጥቷል፡፡ዘር ከልጓም እንደሚስብ ሁሉ ሳንቲምም ለጊዜውም ቢሆን እውነትን ያስደፈጥጣል፡፤ ክንፉ ስለአድዋ ድል ሲያወሳ ተሳስቶ አንድ ጊዜ እንኳን ቢሆን የአጼ ምኒሊክን ስም አልጠቀሰም፡፡ የዘሀበሻ ሹክሹክታ ዘጋቢ ሄኖክ ደግሞ በገዱ አንዳርጋቸው ላይ በጊዜና በአውድ የማይገናኙ ንግግሮችን ለቃቅሞ ሰፍቶና ደራርቶ አቅርቦታል፡፤ ገዱ አንዳርጋቸው በኢህአደግ ዘመን በአማራ ህዝብ ትግል ላይ የሰራቸው ጥፋቶች ጠባሳው እንዳለ ቢሆንም አሁን በኦሮሙማ ዘመን ዘግይቶም ቢሆን አቋሙን አስተካክሎ ወደህዝባዊነቱ ተመልሷል፡፤ በተለይ በሁለት ጉዳዮች ላይ በጣም ወሳኝ አቋም ይዞ ማንነቱን በይፋ አስመስክሯል፡፡ ይህም ” ከዚህ እድሜዬ በኋላ” ብሎ ሁለቱንም አገርንና ህዝብን የሚጎዱ ድርጊቶችን አላደርርግም ብሎ ጠንካራ ኢትዮጵያዊነቱን አስመስክሮባቸዋል፡፤
    እምቢ ካለባቸው ክስተቶች ውስጥ አንዱ የህዳሴው ግድብ የዋሽንግተኑ በአሜሪካኖችና በግብጾች ተርቅቆ ለፊርማ የቀረበውን ስምምነት በልኡክ መሪነቱ “አልፈርምም” ማለቱ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ “ፋኖ ትጥቅ ይፍታ” የሚለውን የአብይ አህመድን ሴራ ላይ አልስማማም!! እምቢ !!ብሎ አቋሙን በይፋ አሳውቆ እምቢ ማለቱ ነው፡፤
    የሚገርመው በሁለቱም እምቢታወቹ ላይ ልጥቀስ”” ከዚህ እድሜዬ በኋላ” የሚል የማይቀለበስና የማይታጠፍ ቆፍጣና አቋሙን ገልጿል፡፡ ታዲያ ይህንን ሰው ነው ዘሀበሻ በሹክሹክታ ላይ የተንሿከከበት፡፡ ሲገርም?? እድሜ ለዶ/ር በርሀኑ ነጋ!!
    የአዲስ አበባ በኦሮሙማ የመሰለቅጥ ጉዳይ ወያኔ ወልቃይትን ውጦ እንደተፋበት ድራማው ባይከር ደስ ይል ነበር፡፤ ነገሩ ግን ተበለሻሽቷልና ከወልቃይቴዎች በላይ ትግሉ አዲስ አበቤዎችን ብዙ መስዋእትነት ሊጠይቃቸው ይችላል፡፡ በእርግጠኝነት የሚሆነው ግን ኦሮሙማ ከአዲስ አበቤ ዋጋውን አግኝቶና ተዋርዶ የዋጠውንና የሰለቀጠውን እንዲተፋ ይደረጋል፡፡

  2. Kinfu Assefa: Sorry to say it, but I never thought that you will fall for abiy ahmed`s SUGAR. I have had a great respect for you during the struggle against woyane, but…now….you became HODAM and sold your soul and conscience for DIRTY MONEY. I hope your friend MESFIN AMAN does not follow suit.

    • ፋኖን ጎንደር ሆነህ ብታየው የተዘጋ ቤት ሰብሮ የኔ ነው ሲል :የቅማንት ቤት ጣራ ሲነቅል ግብር ሲሰበስብ ፋኖ አንድ ነገር ብቻ ይፈራል ያከብራል የትግሬን ንብረት ::

  3. እውነቱ ቢሆን እንደ ሁልጊዜው በሳል አስተያየትህ ተስማምቶናል እነ እውነቱ፤አምባቸው በቀለ ፤አለም ምን እንደሚሉ አናውቅም ።ብርሃኑ ነጋ ያልከው ኢትዮጵያዊነት አለበት ብሎ በገመተው ሁሉ ሂዶ ማርከስ የትግሉ ተቀዳሚ ተግባር አድርጎታል። እስቲ በምን ቀመር ነው አስመራ መሎቲ ቢራ ሲጠጣ ከርሞ አሜሪካ ማኪያቶ ሲያጣጣም ቆይቶ እነ አንዱ አለም አራጌ እንደ ጥጃ ሲታሰሩ ሲፈቱ በኖሩበት አገር የድርጅት ሊቀመንበር ሁኖ የወጣው? የዚህ እንቆቅልሽ አልገባ ብሎኛል በእርግጥ መደላድሉን አንዳርጋቸው ጽጌ፤ኤፍሬማ ማዴቦ፤ነአምን ዘለቀ ቢያስተካክሉትም እንደ የሸዋስን የመሰሉትን አደንዝዘው ለግርማ ሰይፉ ስልጣን ይወዳል ብለው ሽራፊ ስልጣን ስጥተውት በምን ምትሃት ከላይ ቁጭ አለ። ይህ ብርሃኑና ግምቦት 7 ኢሳት ከግብጽ መንግስት ችሮታ ይደረግላቸው እንደነበር ከዚህ በፊት ክሊፑን አይተናል።
    በበኩሌ ብርሃኑ ነጋና አረጋዊ በርሄ ለአብይም ይመለሳሉ የሚል ግምት የለኝም ባይሆነላቸውም ሃሳቡ ከነስ ዘንድ ይኖራል። ተወልደ ገ/ማርያም ከዳ የሚሉት ተረጋግጧል? ምን በወጣው ይከዳል እዛው ሁኖ ስራ ይስራ እንጅ እየስፉ መስለኝ አሁንስ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share