ደንቆሮ የሰማ ዕለት ያብዳል !!! የትግራይ አገረ ስብከት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ የመነጠል

የምስሉ መግለጫ,
ከህወሓት ሊቀ መንበር ደብረፂዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ጋር የተገናኙት የሃይማኖት አባቶች

ከአንድ ክ/ዘመን በፊት የተተከለዉን ከፋፋይ የአገር ክህደት ሴራ ዛሬ አንደ አዲስ ደራሽ ዉኃ ማድረግ እና ሰሞነኛ አድርጎ ማጮህ ለዓመታት እንደሰደድ ዕሳት እየተስፋፋ ያለዉን ድህነት፣ ስደት(የአገር ዉስጥ መፈናቀል) ፣ ሞት እና ርዛት የሚያስታግስ ሳይሆን የሚያለባብስ ነዉ ፡፡

ከሰሞኑ የትግራይ አገረ ስብከት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ የመነጠል አዝማሚያ እንዳለ ማራገብ የአዋጁን በጆሮ ለሚሉ ጆሮ መስጠት ከመዘናጋት በላይ ሞት ነዉ ፡፡

ከላይ ለተባለዉ ምክነያት በጦርነት በትግራይ  ለነበረዉ ጦርነት እና ላስከተለዉ ዉድመት ቤተ ክርስቲያን ድምፅ አላሰማች ማለት ምንድን ነዉ ፡፡

ለመሆኑ ህወኃት ኢህዴግ ከአስራ ዘተኝ መቶ ሰማንያ ሶስት ዓ.ም. ጀምሮ  በዕምነት ተቋማት በተለይም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ሳይቀር  መፈንቅለ ፓትራያሪክ በማድረግ የራሱን ልማታዊ ሠዉ ሲያስቀምጥ ቤ/ ክ ድምጧን አሰምታለች የሚል ማን ነዉ ፡፡

ለመሆኑ አንድ የቤተክርስቲያን አባት በህይወት እያሉ ሌላ የሾመ(ያስቀመጠ) የህወኃት / ትግሬ ስርዓት አልነበረም ወይ፡፡

ከዚያ ጊዜ አስከዚህ ሰዓት ድረስ በመላ ኢትዮጵያ በኢትዮጵያዊነት እና ማንነት ላይ በሆነ ጀምላ ማሳደድ ፣ ማፈናቀል ፣ መግደል ፤ማስገደል…..ድፍን ፴ ዓመታት ለሚከናወነዉ ቤ/ ክርስቲያን ምን የሚቆጠር አቋም ወሰደች ፡፡

በዕምነት ተቋማት ግቢ ሳይቀር ለተደረገ የጣልቃ ገብነት ወንጀል ቤ/ ክ ለአገር እና ህዝብ ከመወገን ይልቅ ለዓለማዊ አገዛዝ እንድትወግን ከላይ አስከ ታች በብቃት ሳይሆን በብሄር አምልኮት እና አገልጋይነት ተደራጂቶ እንደነበር እና ይህም እንደ ሌሎች ህዝባዊ እና መንግስታዊ መዋቅር  በብሄር ስም የተጠላለፈ አሰራር ነበር ፤ ነዉ፡፡

አበዉ  “ ዉኃን ምን ያጮኸዋል  ሲሉ  ድንጋይ  ” እንዲሉ  የኢትዮጵያ እና የህዝቧ  የዘመናት ጥቃት ፣ ዉድመት እና ሞት  ምንም ዓይነት ቁብ ያልሰጣቸዉ ዛሬ ከ1968 .ዓ.ም. ቀድሞ  ለማጥፋት የጥላቻ መንደርደሪያዉ  የዓማራ ህዝብ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ  እና ኢትዮጵያዊነት ለማዋረድ እና ለማስወገድ  ያልተፈነቀለ ድንጊያ እና ያልተቆረጠ ቅጠል አልነበረም ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  በየክልሉ የሚታየው የፖለቲካ ሕብረት መላላትና መገፋፋት ለኮሮና ቫይረስ መራቢያ መሣሪያ ነው! - አንድነት ይበልጣል

ይህ ሲሆን አንድም ቀን የዓማራ ሞት እና ስደት ፣ የኢትዮጵያ ዳር ድንበር መደፈር ፣ የኢትዮጵያ አንድነት  አደጋ ላይ መዉደቅ ያላሳሰባቸዉ ዛሬ በኃይማኖት ተቋማት ያላቸዉን የብሄር (ቋንቋ) አደረጃጀት እንደ ት.ህ.ነ.ግ.  አገር እና ህዘብ በማንነቱ ፤በርስቱ  እንዲወረር ፤ እንዲመዘበር እና እንዲሸበር ቤተ ክርስቲያን  በግላጭ ድጋፍ አላደረገችም የሚሉ ከሆነ በግልፅ ሊያወጡት ይገባል፡፡

ቤተ ክርስቲያን  የሁሉም ሠዉ ልጆች መጠጊያ  እና መሸሸጊያ  እናት ናት ፡፡ ቤተ ክርስቲያን  ዕጉም ስንል ገፍታናለች ፤ ድምፅ ነፍጋናለች፤ ሰንራብ አልደረሰችልንም ፤ ስንሞት እና ስንሳደድ  ልጆቸን አትንኩ አላለችም  ብሎ ቢወቅሱም የሚያምራባቸዉ  ሌሎች ከትግሬ ዉጭ ያሉ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ነበሩ ፡፡

ስለ ኢትዮጵያ ፣ ስለ ዕምነት ተቋማት ፣ ስለ ህዝብ  እና ስለ ራሱ ክብር የሚያስብ ህዝብ ለደረሰበት መከራ እና ችግር  ተጠያቂዉ መንግስት እና የዕምነት ተቋማት ሆነዉ እያለ  የህይወት እና የምስቅልቅል  ዋጋ የሚከፍለዉ ህዝብ በተለይም የቤተ ክርስቲያን ልጆች ናቸዉ ፡፡

እናም ይኸ ጩኸቴን ቀሙኝ  መንጫጫት ቀርቶ የሚበጀዉ ለህይወት ወይም ሞት  በፅኑ ዕምነት እና ዓላማ መዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡

ሲጠቃለል  አገር ለማፍረስ ከ1968 .ዓ.ም. ጀምሮ  ኢትዮጵያን በማፍረስ  ታላቋን ትግራዊ ለመቀለስ ያኔ የተተከለዉን ጋሬጣ ከ“መንቀል እና ማቃጠል  ” ዉጭ ዛሬ ስለ  ትናንቱ  ማዉራት የሚተርፈዉ  በስንፈት “ሞት  እና ዉርደት ” ማስተናገድ ይሆናል  ፡፡

ማላጂ

አንድነት ኃይል ነዉ

3 Comments

  1. ደግ ብለዋል ማላጅ ስታሊንም የተከበረ የቤተክህነት ሰው ሁኖ ትግሬዎች ሲያላግጡብን ነበር ስብሀት ነጋ ይሁን ስዩም መስፍን ጠምጥሞ ነበር ይባላል እስቲ አምላክ ፍርዱን ይስጥ።

  2. የትግራይ ሃገረ ስብከት መገንጠል ማለፊያ ነው። ድሮም ቢሆን ተንኮልና ሴራ ሲዘሩ የኖሩ የወያኔ ሥራ አስፈጻሚዎች ናቸው። ሰው ደ/ጽዪንን አምኖ በእርሱ የውሸት ዲስኩር የዝንተ ዓለም ታሪክን መለወጥ የካሃዲዎች ሙያ በመሆኑ እሰየው፤ ያጽናላችሁ እንላለን። እኔ የማይገባኝ አንድ ነገር አለ። አሁን ማን ይሙት ወያኔ የሚታመን ድርጅት ነው? ከውሸት ወደ ሌላ ውሸት መሰላል የሚሰራው ወያኔ አንድም ነገር የሚታመን የለውም። ከጳጳሱና ከቀሳውስቱ አልፎ ተርፎም ከምዕመናን ይህ ጉዳይ ትክክል አይደለም በማለት የሚከራከር የለም። ቢኖሩም ታፍነው ሥጋቸው ተቆራርጦ ለአውሬ ይጣላል። ይህ ጨካኝ ቡድን ትግራይን እየሰራት የመሰላቸው ጭፍኖች ሁሉ መከራ እያዘነበባትና ወደፊትም ለመከራና ጦስ እያዘጋጃት መሆኑን መረዳት ይኖርባቸዋል፡፤
    የመገንጠልን ካባ አንግቦ በረሃ የገባው ጨካኙ ወያኔ ዛሬም ነገም ደም እያፈሰሰና እያስፈሰሰ በሩቅና በቅርብ ካሉ ጎረቤቶቹ ጋር እድሜ ልኩን ክራርና ከበሮ እያስመታ የሰውን ልጅ ማገዶ እንደሚያደርግ ያለፈበትና አሁን የሚከተለው መንገድ በግልጽ ያሳያል። ሲኦል ወርደን ቢሆን ኢትዮጵያን እናፈርሳታለን የሚል የፓለቲካ አመራር እንዴት ባለ ሂሳብ ነው የቤ/ክ መሪዎችን መካሪ የሚሆነው? ለጦርነቱ ልጅ ካልሰጣችሁ የእርዳታ እህል አይሰጣችሁም የሚለው ይህ አረመኔ ቡድን እንዴት ባለ ሞራሉ ነው መስቀል ተሳልሞ ይፍቱኝ የሚለው። ጭንቅላቱ በተንኮል ታስሮ በሰው ደም ጨቅይቶ ምንም አይነት የመስቀል ሃይል ይህን የሙታን ቡድን ወደ ጠራና ሰዋዊ እይታ ሊያመጣቸው አይችልም። አውሬዎች ናቸውና!
    የትግራይ ሙሉ በሙሉ መገንጠል እሰየው ያሰኛል እንጂ ለምን አስብሎ አያስጠይቅም። እንደ ጎረቤታቸው ኤርትራ ይገንጠሉና ይለይላቸው። ከዚያ በየክልሉ የተሸነሸነው የጎጥ ባንዲራ አውለብላቢ ሁሉ ሃገር ይሆንና አንድ አንድን ሲያላትመውና ተራብን ተጠማን ድረሱልን እንዳልን ኑሮአችን ካለፈው እያከፋን የአለም መሳለቂያ እንሆናለን። ለወያኔ የማይገባው ግን መገንጠል መገንጠልን ያስከትላል። ጦርነትን ይጭራል። ሰውን ያቆራርጣል። ልጅና አባትን፤ ሚስትና ባልን፤ እናትና አባትን ይለያያል። ለወያኔ እንዲህ ዓይነቱ ሰቆቃ የፓለቲካ ፍጆታ ነው። ደስ ነው የሚላቸው። ወያኔ ከጅምሩ ጀምሮ ለትግራይ ህዝብ አንድም ቀን አስቦ አያውቅም። ለዚህ ማስረጃው በትግራይና በሱዳን የስደተኛ ካምፕ ወድቀው የቀሩት የትግራይ ልጆች ነው።
    የሰሜን ጦርነቱን ” በመብረቃዊ ጥቃት” በደቂቃዎች ውስጥ ተቆጣጠርነው በማለት በደነፉበት በዚያው የውሸት አሸንዳ ሚዲያዎቻቸው አሁን ደግሞ ዞረው ተመልሰው “ጦርነቱን” እኛ አልጀመርነውም ይሉናል። ስለ ድርድር ሲጠየቁ ” ጦርነቱ አልቋል ከማን ጋር ነው አሁን የምንደራደረው” ያሉን የወያኔ ጄኔራሎች አሁን ደግሞ ለውጊያ ሰው አምጡ እያሉ የትግራይን ወላጆች ያሰቃያሉ። ወያኔ ከጀርመኑ ገስታፓ፤ ከጣሊያኑ ግራዚያኑ የሚከፉ ናቸው። አንድም ነገር የሚታመን የላቸውም። አይናችሁን ተጨፈኑና ላሞኛችሁ እያሉን ነው። አያሳዝንም? ታዲያ የትግራይ ሃገረ ስብከት መገንጠሉ የበረሃ እቅዳቸውን ግብ መምታት ያሳያል እንጂ ለትግራይ ህዝብ አንድም ጠቀሜታ የለውም፡፡ ቀጥሎም ዲሞክራቲክ ትግራይ ሪፐቭሊክ ተመሰረተች እንባላለን። ከዚያም ግጭቱ፤ ግድያው፤ አፈናው፤ ሰቆቃው ይቀጥላል፡፡ ጆርጅ ኦርዌል 1984 ላይ እንዳለው ባርነት ነጻነት፤ ነጻነት ባርነት ይሆናል። እባካችሁ ቶሎ ብላችሁ ተገንጠሉ። በቃኝ!

  3. አዲስ አበባ ሲዘርፍ፤ሲያዝርፍ፤ሲገድል፤ሲያስገድል የኖረ ትግሬ ይህን ጉደ ሰምቷል? ይሄኔ ንብረቱን ሺጦ መልክ መልክ አስይዟል። በአንድ ሰው እድሜ ተመሳሳይ ነገር ሊደገም ነው ማለት ነው?ሻቢያን ጠርዘው እንደላኩ እነሱም ተጠርዘው ሊላኩ ነው ማለት ነው? ጊዜ ጠብቆ ቀን ቆጥሮ ትግሬ ተለቃቅሞ ሊላቀቀን ነው ማለት ነው?

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share