ትንሽም ብትሆን እውነትን ሳትቀላቅል ዋሽ ….. የሚያዉቁህ ባያምኑህም…… ነገር ግን ዋሽ ….

ያንተ በስፋት የተሰራጨ ውሸት እነርሱ በጃቸው ከያዙት እውነት በላይ ተሰሚነት ያገኛል

(እውነቱ ቢሆን)

ወያኔወች፦ አምናም ውሸት፣ ትናንትም ውሸት ፣ዛሬም ውሸት፣ ዘለአለም ውሸት፣ ውሸት  ውሸት .. አሁንም ነገም ውሸት  ብቻ ናቸው፡፡ ይህንኑ ማንነታችውን  በትክክል ለመግለጽ ይረዳ  ዘንድ በመረጃ ፎረም ላይ ከአንድ ጸሀፊ ያገኘሁትን ወያኔ ማለት ሙሉውን ውሸት መሆኑን አሳምሮ የሚገልጽ አጭር ጽሁፍ ጽሁፉን እንደወረደ ከስር አቅርቤዋለሁ፡፡

የዲጅታል ወያኔ ማኒፈስቶ፦

ዋሽ፡፡ ነገር ግን በምትዋሽበት ጊዜ ትንሽም ብትሆን እውነትን አትቀላቅል፡፡ በቃ እስከመጨረሻው ድረስ ዋሽ!  የእውነታው ድራሹ እስከማይታወቅ ድረስ በውሸትህ ጽና፡፡ ሁሉም ራሱን መጠራጠር እስከሚጀምር ድረስ ውሸትን አቀናብራት፣ ሽፋን እንድታገኝ አድርጋት፣ ሀሰተኛ ዘገባ ዘግብ፡፡ ማንም ባያምንህም በውሸትህ ጽና፦ በሷ ላይ ተመስርተህ ቀጣይ እርምጃህን ፈጽም፡፤እራስህ የፈጠርከውን ሀሰት እራስህ አሰራጨው፡፤ ከዚያም ለእርሱ የሚመጥን እርምጃ ውሰድ፡፤ ያኔ ሁሉም ሰው በግራ መጋባት ውስጥ ሁኖ ጆሮ ይሰጥሀል፡፡በተቻለ መጠን የሀሰት ማስረጃወችን አሰራጭ፡፡ ያሰራጨሀውን ሀሰተኛ መረጃ  የሚያጠናክሩ የሀሰት ምስክሮችን ከየአቅጣጫው አዘጋጅተህ አቅርብ፡፡

የሚያዉቁህ በሙሉ አያምኑህም፡፡ አይሰሙህም፡፡ እነርሱን እርሳቸው፡፡ አይናቸው እያየ ጆሯቸው እየሰማ በአደባባይ ሀሰተኛ መረጃን ልቀቅ፡፡ እነርሱ እውነቱን ስለሚያውቁ እነርሱን ለማሳመን አትጃጃል፡፡ ይልቅ በተደራሽነትህ ተጠቅመህ ቅደማቸውና ያንተ ሀሰት የእነርሱን እውነታ እንድሸፍን አድርግ፡፡ያኔ በዙሪያህ ያለው ህዝብ እውነቱን ስለሚያውቅ አንተን እና የሀሰት ፕሮፓጋንዳህን አምርሮ ከመጥላት ውጭ ምንም አያመጣም፡፡ ነገር ግን ያንተ መረጃ በመላው አለም ተቀባይ ይሆናል፡፡ ተቃዋሚወችህ እውነቱን በጃቸው ይዘው ቁመው ይቀራሉ፡፤ የማያውቅህ የሩቅ ሰው ግን አማራጭ አጥቶ ከአንተ ጎን የመሆን እድል ይኖረዋል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የጠቅላይ ሚኒስትሩ ወንበሮች – ሙሃዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት

ተቃዋሚወችህ አንተ ደረሰብኝ ያልከውን ሁሉ ባይፈጽሙትም አንተ ራስህ እነርሱን መስለህ ድርጊቱን ተውነው፡፡ ንጹሀን ተገደሉብኝ ካልክ በቃ ንጹሀን እንዲገደሉ አድርግ ወይም ማንነትህን ሰውረህ ንጹሀንን ግደል፡፡ ይህ የትግሉ መንገድ ነው፡፤ ድሉን ለማግኘት ማንኛውንም ነገር መፈጸም ግድ ይልሀል፡፤ ንጹሀን በግፍና በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉብኝ ብለህ ካሰራጨህ እና ተቃዋሚወችህ ያንን ካልፈጸሙት ይህ ነገር እንድፈጸም የራስህን ድርሻ ተወጣ፡፡ ንጹሀን በሚገኙበት ቦታ ዉጊያ ክፈት፡፡ ንጹሀን አልወጣ ካሉህ ዉጡና ተዋጉ በላቸው፡፡ እምቢ ካሉህ ማንነትህን ሰውረህ የጠላትን ገጽታ ተላብሰህ ጥቃት አድርስባቸው፡፡ ከዛ ሜድያ ላይ ውጣና ድርጊቱን በእጅጉ አውግዝ፡፡ ማውገዝ ብቻም ሳይሆን አጸፋ እወስዳለሁ ብለህ ተናገር፡፡ ዋሽ፡፡ እየዋሸህ ጽና፡፡ የዋሸሀውን ውሸት ሌላው ባያምነው አንተው እመነው እና በዛ ተመስርተህ አጸፋ መልስ ስጥ፡፡ ነገሩ ከቅም በላይ ሲሆንበት ሁሉም ይምታታበትና ያንተ ውሸት ከእነርሱ እውነት በላይ ተሰሚነት ያገኛል፡፡

ይህችን ከመረጃ ፎረም ላይ ያገነኋትን አጭር ነገር ግን የወያኔን ማንነት ቁልጭ አድርጋ የምትገልጽ አጭር ጽሁፍ ልኬያለሁ፡፡

ከሰላምታ ጋር

 

 

5 Comments

  1. ዱሮስ ቢሆን ታሪክን ላገናዘበ ሰው ውሸት ብቻ ሳይሆን ክህደትና ባንዳነት ከየት መጣና? ብቻ አብሮ መቆየት እንደመነሻ ወስዶ .. ከአህያ ጋር የዋለች ጊደር እንዲሉ… ተረኛው ኦሮሙማም ይህ ዉሸት ዳር ዳር ብሎታልና እንዳይጋባበት ያሰጋል፡፡

  2. የእነ ስብሃት ቡድን ተፈቱ እነ ጃዋርም ተፈቱ ለማ መገርሳና ድንቁ ደያስም ከስደት አዲስ አበባ ገቡ:: የመከላከያው ቁልፍ ቦታዎች በሙሉ በ አንድ ብሄር ቁጥጥር ስር እንዲሆን ስራው ተሰርቶ ሹመትም ፀድቆ አልቋል:: አክራሪው የኦሮሙማ ቡድን አንድ አጀንዳ ይዞ ስብሰባ ሊቀመጥ ነው:: አንተ ግን ጎንደር ህብረት ወሎ ህብረት እያልክ በጎጥና በአምቻ ጋብቻ ተሰባሰብ:: እመነኝ መጨረሻ ላይ የምትበላው አንተ ነህ::

  3. ውድ ወገኖቼ፦
    በዝርፊያና በመዋሸት ረገድ አንድ ወቅት የወያኔ ተማሪ የነበረው ኦሮሙማ በአጭር በአጭሩ የተረኝነት ጊዜው ውስጥ የወያኔን ዝርፊያንና ሴረኝነትን ያማከለ በውሸት መቀደድን በአያሌው አጥፎት ሄዷል፡፡
    ሴረኛው፣ አታላዩና መርህ የለሹ አብይ አህመድ አሊ በስውር የሚመራው ኦሮሙማ በዘረኝነት፣ በኬኛ አስተሳሰብና አሰራር እንደዚሁም በይሉኝታ ቢስነት በሚቆጭ፣ በሚያሳዝንና በሚገርም ሁኔታ የማይዋሸው ውሸት የማይሰርቀው የህዝብ ሀብትና ንብረት የለም፡፡ ኦሮሙማ ታሪክ ይሰርቃል፡፤ ገንዘብ ይሰርቃል፣ የክክሎችን ድንበር ይሰርቃል፡፤ ከወያኔ በተለዬ መልኩ አንድ ወቅት በሟቹ ወያኔ ጊዜራሱን የቻለ የራሳቸው አስተዳደር የነበራቸውን (ለምሳሌ አዲስ አበባ ከተማ ስሙ በህግ ክልል 14 ነበር) የአዲስ አበባንና ድሬዳዋ ከተሞችን ሊሰለቅጣቸው ተቃርቧል፡፡ኦሮሙማ አሁን እየሰለቀጠው ያለውን የራሱ ያልሆነውን ሁሉ ቆይቶ እንዲተፋ እንደሚደረግ ቅንታት ጥርጥር የሌለን ቢሆንም ድርጊቱ ውርደትና ክስረትን አስተናግዶ ማለፉ ለአገሪቱ ኪሳራ ነው፡፡

  4. ጽድቁ አርአያ፦
    ያልከው በሙሉ ትክክል ነው፡፤የእነ አብይ አህመድ ኦሮሙማ ከዚህም በላይ ገና ያደርጋል፡፤ አይገርምም፡፤ እንደነ ደመቀ መኮንን እና ደጉን ማፊያውን ተመስገን ጥሩንህን ይዞ አብይ ብዙ ሴራና ተንኮል በአማራው ላይ እንደሚያደርግ ሳይታለም የተፈታ ነው፡፤ ለዚህኮ ነው እኛ አማራወች አንከፋፈል፣ በፋኖ ዙሪያ እንሰባሰብና ታሪካዊ ጠላታችን የሆነውን ወያኔን እንደዚሁም ኦነግን(አብይ”ሸኔ” እያለ በስውር የሚንከባከበውን) ሁለቱንም ጠላቶቻችንን የመመከትና የመደምሰስ አቅምና ጀግንነት አለን፡፡ የሚችግረን መሳሪያና ሎጂስቲክስ ነው፡፤ ይህም ችግር ዘዴ አለው፡፡በቅድሚያ አንድ እንሁን፡፤ እንተባበር፡፡ የአማራን ክንድ ሁሉም ይፈሩታል፡፡ ነገር ግን የኛወቹ ሆዳሞች ቀድመው ስላዋረዱን አሁን እና ቀድመን እነርሱ ላይ የማያዳግም እርምጃ እንውሰድ፡፤
    ከላይ እውነቱ በጽሁፉ ያቀረባቸው የወያኔ የዉሸት ባህርይወች አንድም ሳይቀር መቶ በመቶ በተረኞቹ ኦሮሙማወች እየተተገበሩ ነው፡፡ አብይን ብቻ እንመልከት፡፡ የእኢትዮጵያ መሪነት ቦታ ላይ ተቀምጦ በውስጡ የኦሮሙማ ድሪቶን የደረተው መርህ የለሹና ቀዳዳው ኮሎኔል አብይ አህመድ አሊ ከአፉ የሚወጣው ሽህ ውሸቶችና ሽህ ማታለሎች ተሰድረውና ተመዝግበው የሚገኙ ለወረደ ማንነቱ ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡ የነሽመልስ አብዲሳ እብሪት፣ የነጃዋር ጭፍጨፋና የነአዳነች አበቤ አይን ያወጣ ብልግና ሁሉም ወያኔን ያስናቁ እኛ አማራወች የተሸከምናቸው ውርደቶቻችን ናቸው፡፤
    ችግሩ የጀመረው ከ46 ሚሊዮን በላይ የህዝብ ብዛት ያለውን ታላቁን የአማራ ህዝብ በቁጥር ታናሽ አድርገው ያቀረቡ እለት ዝም በመባላቸው ነው፡፡ይህንን ሆን ተብሎ የተፈበረከ ዝቅተኛ የአማራ ህዝብ ቁጥር ወያኔ ለአላማው በውሸቱ አስኬደው ኦሮሙማም በተረኝነቱ ቀጠለበት፡፡ እንዲያው በደፈናው ሁለቱም ብዙ ተጠቀሙበት፡፡ አማራውም ብዙ ተጎዳበት፡፡አገሪቱ ሰላም ሆና ዲሞክራሲ መጥቶ ሰው በስውነቱ መብቱ ተከብሮለት ትክክለኛ የህዝብ ቁጥር ሲደረግ እውነቱ ፍንትው ብሎ ይወጣል፡፡ እስከዚያው አሁን ላለው ችግር ሁሉንም ወደጎን አድርገንና ሙያ በልብ ነው ብለን ለመትረፍ፣ ላለማለቅ፣ ለመኖር አስቸኳይ እርምጃወችን እንውሰድ፡፡ አማራ ሆይ፦ ሀያልነትህን፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ታላቅ ህዝብ መሆንህን ፣ብቸኛ መተማመኛህ ነፍጥህና ድፍረት የሞላው ልብህ መሆኑን አምነህ ተነሳ፡፡ ታሪክና አገር ሰሪነትህን ድጋሜ ማሳያ ጊዜው አሁን ስለሆነ አሁናዊ ሁኔታወችም ይህንኑ ግድ ስለሚሉ በያለህበት በጎበዝ አለቃ፣ በፋኖ እና በልዩ ሀይሎች ዙሪያ ተደራጅ፡፤ ተደራጅተህም ለሁለገብ ትግሉ ቆርጠህ ተነሳ፡፤ ምርጫህ ማሸነፍ ወይንም ማለቅ ብቻ ነውና ለማሸነፍ በሙሉ ልብ ሆነህ ተዘጋጅ፡፤ ታሪክህን እድልህን በራስህ መዳፍ ውስጥም አስገባ!!!

  5. ቆም ብሎ ማሰብ ክቀረ ዘመናት ቆጥረናል። የሃገራችን የፓለቲካ የለውጥ መንገድ ሲጀመር ሁሌ ለስላሳ ነው። ችግሩ የሚመጣው እየቆየ ነው፡ ይህ በደርግም ሆነ በወያኔ አሁን ደግሞ በድህነት ማህል ብልጽግና ብሎ ራሱን በሰየመው ቡድን ላይም ታይቷል። ህዝባችን ኢፍታህ የተባለ ድዳ ይመስል የልቡን ሲናገር ተለቅሞ ወህኒ ይወርዳል። በአሉንና ሃይማኖቱን ሲያከበር ችግር ይጋረጥበታል። አልፎ ተርፎም ለሃገርህ፤ ለድንበርህ፤ ለዚህም ለዚያም እየተባለ ማገዶ ይሆናል። በዚህ ሁሉ ግን ሸረኞችና በሰው ደም መነገድ ልማዳቸው የሆኑ የፓለቲካ ተኩላዎች በውስጡ ይራወጣሉ። የሚበሉትን ይበላሉ፤ የተረፈውን ዘብጥያ ያወርዳሉ፤ የአዕምሮና የአካል ጉዳተኛ ሲሆኑ እነዚህን ጨለማ ቤት ለዘመናት የደበቋቸውን ተራፊ ሰዎች በምህረት ለቀናል ይሉና ብዙም ሳይቆይ ከሰቆቃቸው ብዛት ሰው ሂዶ ወደ እማይመለስበት ዓለም ይጓዛሉ። ሞት በሃበሻ ምድር ርካሽ ነው። የሰው ህይወት የፍራንክ ያህል ዋጋ ያጣበት ዘመን ላይ እንገኛለን። አንድ የወያኔ ወታደር ካደረገው እውነተኛ ታሪክ ልጥቀስ። ሴትየዋ ልጅ ወልዳ አራስ ናት። ወያኔዎችን ወደ ሰፈራቸው እየተጠጉ ሲሄድ ሰው ይሸሻል። እሷና አንዲት ጎረበት ብቻ ይቀራሉ። ከዚያ አንድ ላይ እንሁን ያንቺን ቤት ተይና ለማረስም እንዲመቸኝ እኔ ጋ ነይ ትላለች። በዚያው ቤት ውስጥ ተደብቀው የሚሆነውን ሲጠባበቁ አንድ ምሽት ላይ በሩን ገንጥለው ወያኔዎች ይገባሉ። ሲገቡ መደብ ላይ የተኛ ህጻን ያያሉ። እናት ከጎኑ ናት። ሊደፍሩ ሲሞክሩ አራስ እናትን እረ በፈጠራችሁ ትላለች። ከዚያ ዓይኑን ህጻኑ ላይ የጣለው ወያኔ ህጻኑን አንስቶ መሬት ላይ ፈጠፈጠው። እናት አልቅሳ ብታነሳ ህጻኑ ወገቡ ተሰብሯል። ወዲያው ያርፋል። እንዴት እንዲህ ትጨክናላችሁ ህጻን ላይ ስትለው “ይህ አማራ ነው አድጎ የሚወጋን” በማለት በስድብና በዝርፊያ የታጀበው ሰቆቃ በዚያ ቀን በህጻኑ ሞት ተገታ። የትግራይ ወራሪዎች አውሬ ናቸው የምንለው ለዚህ ነው። ከሰው የተፈጠሩ አይደሉም። የወያኔን እውነተኛ የክፋት ባህሪ ጠንቅቆ የተረዳው የሻቢያ ወታደር ብቻ ነው። የኢትዮጵያው ወታደር ወገኔ ሃገሬ ባላቸው በራሱ አባሎች ነው መኪና የተነዳበት። በተኛበት በጥይት ያለቀው። ሚስቶቻቸውና የሴት የኢትዪጵያ ወታደሮችን ጡት የቆረጡት። ይህ እንግዲህ ሚኒሊክ ይህን ሰራ እያለ የአኖሌን ሃውልት ያቆመልን የትግራይ መንጋ ነው።
    ሰው ደንዝዟል። በተለይ አማራውና የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታዪች ሊነቁ ይገባል። መጠራቅቅ ውስጥ ገብታቹሃል። በቅርቡ በወብላ ማሪያም ባንዲራን ተገን አርጎ በኦሮሞ ጠባብ ብሄርተኞች የተፈጠረው ሊመጣ ያለውን የክፋት ኮሮጆአቸውን ቅንጣት ክርፋት ያሳየ ነው። ገና ብዙ ይታሰባል። እስቲ እናስተውል። በማን ሃገር ነው የተዘራ አዝመራ በእሳት የሚጋየው? ወለጋ፤ በሽዋ፤ በአማራና በአፋር በኦሮሞ ጠባቦችን በጋላቢው ወያኔ የተፈጠረ ያ አይደለምን? ሴራው ጥልቅ ነው። ኦሮሞው ስሜን የቀየረብኝ አማራ ነው። ለምን እንዳጠመቀኝ እንኳን አላውቅም ብሎ የሚያላዝን የምሁር ደንቆሮ በተከማቸባት ምድር ሃገር ባንዲራ ሰላም የሚባሉት ነገሮች ሁሉ ቀልድ ናቸው። አሁን በቅርቡ ኦፌኮ ያወጣውን መግለጫ ልብ ብሎ በመስመሮች መካካል ያልተባለውን ነገር ላጤኔ እነዚህ ሰዎች ሰላም የማይሰጡ የሁልጊዜ አሻሮ ሃሳብ አፍላቂዎች መሆናቸውን አጉልቶ ያሳያል።
    ሚዲያውና የመንግስት አመራር የሚያወሩልን አሸብራቂ ቃላቶች ሳይሆን ማየትና መስማት ያለብን ተግባራቸውን ነው። ቃላቸው ከሥራቸው ጋር ይሄዳለ ወይ? መልሱ የተወላገደ ነው። ተሰብስቦ ማጨብጨብ፤ ሰማይ ላይ ዳቦ አለ ብሎ ማመላከት የኖርንበት የፓለቲካ ስልት ነው። ጥያቄው ለምን ይሆን ትላንት ያነቡ አይኖች ዛሬም የሚያለቅሱት። ትላንት ፍርድ ያጡ ወገኖቻችን ዛሬም የሚገፈተሩት? የዘር ፓለቲካውን በመተው በሰውኛ ዓይን ካየነው የትግራይ እናቶች እንባ ከአማራ እናቶች እንባ ይለያል? ለወያኔ አዎን። ለእኔ ግን የሰው ልጆች ሰቆቃ ሁሉ ይሰማኛል። ሰውን በሰውኛ እንጂ ታላቋን ትግራይ ወይም ታላቋን ኢትዮጵያ እንመስርት ብዬ እንዘጥ እንዘጥ ከሚሉት የሙታን ጉባኤ ውስጥ ራሴን አላሰልፍም። 70 ዓመት ሙሉ እልፍ ሰው የረገፈበት የሶቪየት ፓለቲካ ባፍጢሙ ሲደፋ አላየንም? እንኳን የሃበሻው ወፌ ቆመች ፓለቲካ። የውጭና የውስጥ አሻጥር እንዳሻው እንደ ወራጅ ውሃ መንገድ የሚያስቀይረው? የሚያሳዝኑን ለትግራይ ቆመናል ብለው በማመን በምድር ላይ ያልተፈጸመ ሰቆቃ የሚፈጽሙት ናቸው። ከሞት እንኳን ብትተርፍ ወይም ብትተርፊ ያን ሁሉ ጭካኔ የፈጸመ ልብ ሰላም አይኖረውም። እናንተ ለትግራይ ለራሳችሁም አትጠቅሙም። የጦርነት ታሪክ የሚያሳየው ይህን እውነታ ነው።
    ማንኛውም መንግስት ሙሉ የሆነ እውነትነት የለውም። የማይዘላብድ መንግስ ማንም የለም። የጠ/ሚሩ ዲስኩር አሰልቺ ነው። ቃል መጠን አነስ ሲል ከልብ ይቀራል። ይህ ግን ሆን ተብሎ ተላላ ለሆነው ህዝብ የቀረበ የፓለቲካ ፍጆታ ነው። ማን ይሙት አሁን በአዲስ አበባ የሚነሱ እሳቶች በጥናት የተቀጣጠሉ አይመስሉም? አሁን በእምነት ዙሪያ በተለይም በመስቀል አደባባይና በወይብላ ማሪያም ታቦት ዙሪያ የተደረጉት የሃሳብና የግብግብ አልፎ ተርፎም የተኩስ እሩምታ ሚስጢር አለው እንዴ? የለውም። የገቢያ ግርግር ለሌባ ይመቻል አይነት ነው። ሃበሻው ጨርቁን አውልቋል። አንድ ነገር ልበልና ልጨርስ።
    አንድ ሚሊዪን ሃበሻ ሲባል እቃዋን ጠቅላ ቀሚሷን ለብሳ ሿ ዝንፍል እያለች ወደ ሃገር ቤት የተጓዘችው ዘመዴ አዲስ አበባ ትደርሳለች። ከቀናት በህዋላ ከተማ እንይ ብለው በየመንገድ መኪያ እያቆሙ ይንጎራደዳሉ እሷና አንድ ወንድ አንድ ላይ ሌሎች ደግሞ አልፍ አልፍ ብለው ተቆራኝተው ወሬአቸውን ያቀልጣሉ። በድንገት አንድ ህጻን ልጅ ወደ 10 ዓመት የሚሞላው ወደ እርሷ እየሮጠ መቶ አድኝኝ ይላታል እሷም አቅፋ ይዛ ከማን ስትል አራት ጠብደል ልጆች ይከቧታል። ኖ አትነኩትም ስትል አብሯት የነበረውን አንድ ይገጥመዋል በነገር። ከዚያ በፍጥነት እሷን ይከቧታል። ወዲያ ከመቅጽፈት ሁሉም ይጠፋሉ ራሷን ስትፈትሽ ሃብላ አንገቷ ላይ፤ ቦርሳዋ ውስጥ ያለ ገንዘብና ሞባይል ትሰረቃለች። ይህ የአዲስ አበባ ሌቦች ከሚጠቀሙበት የዘረፋ ስልት በጭልፋ ነው። ሌላም ብዙ ብዙ ጉድ ህግ እናስከብራለን በሚሉት ሁሉ ይፈጸማል። አታድርስ ነው። በምድሪቱ የሚያፍቅ ነገር የለም። በቃኝ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share