ኢትዮጵያ በታሪኳን እንደ ዐቢይ አሕመድ አይነት እቡይና ፍጹም አምባገነን አጋጥሟት አያውቅም! – አቻምየለህ ታምሩ

በኢትዮጵያውያን ሕይዎት እንደሚቀልደው እንደ ከሀዲው ዐቢይ አሕመድ አይነት ፍጹም ስልጣን የነበረው የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት፣ ፕሬዝደንትና ጠቅላይ ሚኒስትር አልነበረም። በነገሥታቱ ዘመን እያንዳንዱ መንግሥታዊ ውሳኔ ሲወሰን ሥርዓት ነበረው።የኢትዮጵያ ሥነ መንግሥት ፈላጭ ቆራጭ ንጉሠ ነገሥት የሚቀበል አልነበረም። ንጉሠ ነገሥቱ ስለፈለገ ብቻ የሚወስነው አንዳች አገራዊ ውሳኔ አልነበረም። ሁሉም ነገር ሥርዓት ነበረው።
በነገሥታቱ ዘመን አንድ መንግሥታዊ ውሳኔ ሲወሰን ማለፍ የነበረበትን አካሄድና የነበረን የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ከታች ጀምሮ እስከ ንጉሠ ነገሥቱ ድረስ ሥርዓቱ ምን እንደሚመስል ማወቅ የሚሻ ቢኖር ፕሮፈሰር ባይሩ ታፍላና ፕሮፈሰር ሄኔሪክ ሾለር አርመው ያሳተሙትን የኢትዮጵያ ሥርዓተ መንግሥት ያንብብ። የመጽሐፉ ርዕስ “Ser’ata Mangest: An Early Ethiopian Constitution”ይሰኛል።
በመጨረሻው የኢትዮጵያ ነጉሠ ነገሥት በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን የነበረውን መንግሥታዊ ውሳኔ አሰጣጥም ካየን አንድ ውሳኔ ሲወሰን የሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት፣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት፣ የዘውድ ምክር ቤት፣ ፍርድ ቤት፣ አማካሪዎች፣ ወዘተ በሚባሉ መዋቅሮች አልፎ ነበር አንድ ውሳኔ የሚወሰነው።
ሌላው ቢቀር የሻለቃ መንግሥቱ ኃይለ ማርያምና የሊቀመንበር መለስ ዜናዊ አገዛዞች እንኳን የሚፈልጉትን ውሳኔ ሕጋዊ የሚያደርጉበት ፓርቲ፣ ፓርላማ፣ የሚንስትሮች ምክር ቤት፣ ፍርድ ቤት፣ አማካሪዎች፣ ወዘተ ነበራቸው።
መንግሥቱ ኃይለ ማርያምም ሆነ መለስ ዜናዊ ስንት የኢትዮጵያ ልጆችን የፈጀ የጦር ወንጀለኛን በነጻ የመልቀቅን ያህል ውሳኔን ቀርቶ ማናቸውንም ተራ ጉዳዮችን እንኳን ቢሆን ከመወሰናቸው በፊት ቢያንስ በዲሞክራሲ ማዕከላዊነት በተጠረነፈው ፓርቲያቸው አስወስነው ነው ለሕዝብ ይፋ የሚያደርጉት። የሚያቀርቡትን ሀሳብም የሚቃወሙና የሚገዳደሩ የፓርቲያቸው ሰዎች ነበሩ። በደርግ ውስጥ እነ ሲሳይ ሀብቴ፣ እነ አጥናፉ አባተ፣ እነ ሞገስ ወልደ ሚካኤል፣ እነ ብርሀኑ ባይህ፣ ወዘተ የሚባሉ መንግሥቱ ኃይለ ማርያም የሚያቀርባቸውን የውሳኔ ሀሳቦች የሚቃወሙ የፓርቲ ሰዎች ነበሩ። የመንግሥቱ ኃይለ ማርያም ዘመን የመጨረሻው ውሳኔዎች የሚወሰኑት የነዚህን ሰዎች ተቃውሞና ተጠይቃዊ ሙግቶች አልፈው ነበር።
ፋሽስቱ መለስ ዜናዊም ቢሆን የሚያቀርባቸውን የውሳኔ ሀሳቦች የሚጋፈጡ የፋሽስት ወያኔ አባላት የሆኑ ባልደረቦቹ ነበሩበት። ፋሽስት ወያኔ በ1993 ዓ.ም. የተከፈለው የመለስ ዜናዊን የውሳኔ ሀሰብ የሚገዳደሩ የማዕከላዊ ኮሚቴና የሥራ አስፈጻሚ አባላት በመኖራቸው ነው። ባጭሩ በፋሽስት ወያኔ ዘመን እንኳን አንድ ውሳኔ የድርጅታቸውን ሂደቶች አልፎ ነበር የሚወጣው።
በዐቢይ አሕመድ ዘመን ግን ፓርቲ፣ ፓርላማ፣ የሚንስትሮች ምክር ቤት፣ ፍርድ ቤት፣ አማካሪዎች፣ ወዘተ የሚባሉት መዋቅሮችን ለይስሙላ እንኳን አልፎ የሚወጣ ውሳኔ የለም። ገዱ አንዳርጋቸው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርነት ተነስቶ የሆነ ቦታ መጣሉን የሰማው እንደ ማናቸውም ኢትዮጵያዊ ዜናው በቴሌቭዥን ሲነገር ነው። ኢታማጆር ሹሙ አደም መሐመድ ከኢታማጆር ሹምነቱ መሻሩን የሰማው በሜዲያ ነው። ደመቀ መኮንን ገዱ አንዳርጋቸው ተክቶ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆኖ መሾሙን የሰማው እንደ ሁላችንም በሜዲያ ነው። ብርሀኑ ጁላ አደም መሐመድን ተክቶ ኤታማጆር ሹም መሆኑን የሰማው ሹመቱ በቴሌቭዥን ከተነገረ በኋላ ነው። የጦር ወንጀለኞቹን የነ ስብሀት ነጋን በነጻ መለቀቅ የጠቅላይ ሚኒስትሩን የደኅንነት አማካሪ ገዱ አንዳርጋቸውን ጨምሮ ሌሎች የብል[ጽ]ግና አመራሮች የሰሙት የዐቢይ አሕመድ ውሳኔ በቴሌቭዥን ሲነበብ ነው። እንደዚህ አይነት ፍጹም አምባገነናዊ ውሳኔዎች በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ኖረው አያውቅም።
ባጭሩ ዐቢይ አሕመድ የጦር ወንጀለኞቹን በነጻ ለመልቀቅ የወሰነው ውሳኔ በንጉሡ ዘመን በየትም በኩል አልፎ አይወጣም። ሻለቃ መንግሥቱ ኃይለ ማርያምና ሊቀመንበር መለስ ዜናዊም ቢሆኑ እንዲህ ያለውን ነገር አይነኩትም ነበር። ኢትዮጵያን ያጋጠማት በታሪኳ አይታው የማታውቀው የኢትዮጵያ ሕዝብ ባይፈቅድ እንኳን የጦር ወንጀለኞችን ጭምር በነጻ የመልቀቅ ፍጹም ሥልጣን ያለውን እቡይና ፍጹም አምባገነን ነው።
አቻምየለህ ታምሩ
ተጨማሪ ያንብቡ:  የተቃዋሚ ጎራዉ የወያኔ መዉደቂያ ደረሰ የሚለዉ ወቅታዊ አጀንዳ መሰረቱ ምን ይሆን?

7 Comments

  1. አብይ አህመድ በኢትዮጵያ የመሪነት ቦታ ላይ ተክፍሶ በውስጡ የደረተው የኦሮሙማ ድሪቶ ስለሆነ ለኢትዮጵያ ጉዳት እንጅ ጠቀሜታን የማያመጣ ችሎታ፣ አተያይና ወኔ የጎደለው ሰው በመሆኑ ይህ በጎደሎ ቀን የመጣብን ደነዝም ሴረኛም ሰው ስለሆነ ከዚህ የከፋ እልቂት ሳያመጣብን በፊት ከስልጣኑ በአስቸኳይ መወገድ አለበት፡፡

  2. አቻምየለህ፦እናመሰግናለን፡፡
    ስለተገለባባጩ ዘንዶ አብይ አህመድ አሊ ከይሲነትና ወኔቢስነት በጠቅላላ ስለግለሰቡ ማንነትና ምንነት የኢትዮጵያ ህዝብ ጠንቅቆ ያውቃል፡፤ ችግሩ የባንንዳወች ውላጅ የነበረው ወያኔ ተክሎት የሄደው የዘረኝነት መርዝ የፈጠረው ህብረት ማጣት ሆነ እንጅ አንዲትም ቀን በስስጣን ላይ ውሎ ማደር አልነበረበትም፡፡፡፡አብይ አህመድ በኢትዮጵያ የመሪነት ቦታ ላይ ተክፍሶ በውስጡ የደረተው የኦሮሙማ ድሪቶ ስለሆነ ለኢትዮጵያ ጉዳት እንጅ ጠቀሜታን የማያመጣ ችሎታ፣ አተያይና ወኔ የጎደለው ሰው በመሆኑ ይህ በጎደሎ ቀን የመጣብን ደነዝም ሴረኛም ሰው ስለሆነ ከዚህ የከፋ እልቂት ሳያመጣብን በፊት ከስልጣኑ በአስቸኳይ መወገድ አለበት፡፡

  3. አቻምየለህ፦እናመሰግናለን፡፡
    ስለተገለባባጩ ዘንዶ አብይ አህመድ አሊ ከይሲነትና ወኔቢስነት በጠቅላላ ስለግለሰቡ ማንነትና ምንነት የኢትዮጵያ ህዝብ ጠንቅቆ ያውቃል፡፤ ችግሩ የባንንዳወች ውላጅ የነበረው ወያኔ ተክሎት የሄደው የዘረኝነት መርዝ የፈጠረው ህብረት ማጣት ሆነ እንጅ አንዲትም ቀን በስስጣን ላይ ውሎ ማደር አልነበረበትም፡፡፡፡አብይ አህመድ በኢትዮጵያ የመሪነት ቦታ ላይ ተክፍሶ በውስጡ የደረተው የኦሮሙማ ድሪቶ ስለሆነ ለኢትዮጵያ ጉዳት እንጅ ጠቀሜታን የማያመጣ ችሎታ፣ አተያይና ወኔ የጎደለው ሰው በመሆኑ ይህ በጎደሎ ቀን የመጣብን ደነዝም ሴረኛም ሰው ስለሆነ ከዚህ የከፋ እልቂት ሳያመጣብን በፊት ከስልጣኑ በአስቸኳይ መወገድ አለበት፡፡

  4. አቻሜለህ በኢትዮጵያ በተለያዩ ነገሥታቶች የነበረውን የፍትህ ውሳኔ ዘርዝርሃል።ሆኖም ግን በአለፉት እና በመለሰ ዜናው አመራር የነበረውን የፍትህ ሁኔታ ልለፈውና በሻለቃ መንግሥቱ ኃይለ ማርያም የፍትህ ዘመንን በጣም ስተኸዋል።ይኽውም ፓርላማ በህዝብ የሚመረጥ እንጂ በነገሥታቱ የሚሾሙም አልነበርም ከዚህ አኳያ ለመሆኑ በደርግ የ17 ዘመን ውስጥ የፓርላማ ምርጫ የተካሄደበት መቸ ነበር? የነበረው ኢሰፓክ በመኢሶን፤በሰደድ፣በወዝ ሊግ እና በኢጨአት የተመሰረተ ሲሆን ኢሠፓም በአንድ ወጥ በሰደድ የተመሰረተ ነው ታዲ ይህንን ነው ፓርላማ ብለኸ የጠራሃውን? ከላይ የጠቀስካቸው በደርግ ውስጥ ሻለቃ ሲስይ ሀብቴ እና ሻምበል ሞገስ አለማየሁም ለምሳ ሲያስቡን ቁርስ አደረግናቸው ተብሎ በሻለቃ በመንግሥቱ ኃይለማርያም ፤በሻለቃ ብርሃኑ ባይህ እና በመሳሰሉት የተፎከረባቸው በስብሰባ ላይ ያለምንም ውሳኔ በተኩስ ልውውጥ በ1969 ዓ/ም የተረሸኑ ጀኔራል ተፈሪ ባንቲም ሆኑ ኮረኔል አጥናፉ አባተ እንዲሁም ጀኔራል አማን አምዶም በሻለቃ መንግሥቱ ኃይለመርያም ዙሪያ ባሉ ምርጥ መኮንኖች የርሸና ውሳኔ የተደረገ እንጂ በየትኛው ፍርድ ቤት በየትኛው ፓርላማ ነው የተወሰነው? ለመሆኑ አቻሚለህ መረጃ ማቅረብ ትችላለህን? በተጨማሪ በ1970 ኣ/ም በጎጃም ደብረ ማርቆስ ወህኒ ቤት 82 ወጣቶች በ2 ሰዓት እንደ ደሮ በማነቅ በሦሥት ጉድጓድ በበህርዳር ወህኒ ቤት በዚያው አመት ማለትም ነሐሴ 1970 ዓ/ም 70 ወጣቶች በተመሳሳይ መልክ የጎጃም ክፍለ ሀገር የፖለቲካ ክሚሳር በነበረው ም/መቶ አለቃ እሸቱ አለሙ ትዕዛዝ እና ውሳኔ ግድያ አልተፈጽመም ? ይህንን ስልም በዚያው ቦታ ያለፍርድ ለ3 አመት የታሰርኩበት በመሆኑ ሲሆን ዛሬ መቶ አለቃ እሸቱ አለሙ በዕድሜ ልክ ተፈርዶበት ሄግ ወህኒ ቤት አለ በዚያን ወቅት በሰራው ወንጀል ማለቴ ነው ። ታዲይ አቻሜለህ አስተውለህ አገናዝበህ መጻፉ መልካም ሲሆን ከብት ባልዋለበት ኩበት ለቀማ እንዲሉ ያልዋሉበትን ሌላውን ለመውቀስ ሲባል በመልካም አመጻድቆ መጽፉ ተገቢ አይደለም።

  5. አቻምየለህ ታምሩ የአገራችንን ታሪክ ብዙም እንደማያውቅ ምስክር መጥራት አያሻንም።
    የሚያስቀው ከአራት ዐመት በፊት ትህነግ ከሥልጣን ከመባረሩ በፊት የነበረውን ታሪክ ጨርሶ መርሳቱ ነው!
    んにちは

  6. 1. በፓርላማ ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀ የህወሃትን አመራሮችን የለ ፍርድ መልቀቅ ከአሸባሪ ጋር መተባበር ስለሆነ በሽብርተኝነት የሚያስጠይቅ ወንጀል ነው።
    2.ከአስመራ ወደ ኢትዮጵያ የገባውን የኦነግ ሰራዊት አዲግራት ላይ የምሳ ግብዣ አድርገው ለተቀበሉት ለእነ ስብሃት ነጋ ውለታ መመለስ ብቻ ሳይሆን የስትራቴጂ አጋርነትን የሚያሳይ ነው። * በኦነግ እና በህወሃት የጥላቻ ርዕዮተ ዓለም ተቀርፀው በአማራና በኦርቶዶክስ ጥላቻ ካደጉ ከእነ አብይ፣ ሽመልስ፣ አዳነች፣ ታከለና ከመሳሰሉት ከዚህ ውጭ ሌላ አይጠበቅም።
    3. ዲያስፖራውን አገር እንዲገባ ጥሪ አድርጎ እነ ስብሃት ነጋን መልቀቁ በተለይ የሃገሪቱ ጠ/ሚ እሱ ራሱ ሆኖ ስሰማ ደንግጫለሁ በማለት ማላገጡ ህዝብን ስለናቀው ነው።
    4. ጂጂ ስለ አድዋ በዘፈነችው ውስጥ “የወዳደቁት መች ተነሱና” እንዳለችው ወያኔ በተኙበት ያረዳቸው የሰሜን ዕዝ አባላት ተሰባስበው መች ተቀበሩና፣ የወታደር ቤተሰቦችስ መች ተረድተው፣ ያፈራረሱት ተቋማት መች ተገንብተውና በህጉ መሰረት ተፈርዶባቸው ነው ገዳዮቹና ዘራፊዎቹ የተለቀቁት?

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share