ጀፍሪ ፌልትማን እንደ ኸርማን ኮኸን – መስፍን አረጋ

ኸርማን ኮኸን (Herman Cohen) በትልቁ ጆርጅ ቡሽ ዘመን (1989-1993) በአሜሪቃ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ውስጥ የአፍሪቃ ጉዳዮች ኃላፊ የነበረና ወያኔን በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ለመጫን ያንበሳውን ሚና የተጫወተ ግለሰብ ነው፡፡   ይህን ያደረገው ደግሞ በለንደኑ ድርድር ላይ የኢትዮጵያን የጦር አዛዦች ‹ለሰላም ሲባል ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ባፋጣኝ ተኩስ እንዲያቆሙ›› በማሳመንና በተቃራኒ ደግሞ ወያኔ ሙሉ ኃይሉን በመጠቀም አዲሳባን በፍጥነት እንዲቆጣጠር በመወትወት ነበር፡፡

ይህ ግለሰብ የለየለት የወያኔ አፍቃሪ ነው፡፡  የወያኔ አፍቃሪ የሆነበትን ዋና ምክኒያት ደግሞ እሱ ራሱ በግልጽ ነግሮናል፡፡  የነገረን ደግሞ በባሕርዳሩ ጭፍጨፋ ማግስት በተወተው ትዊት ነበር፡፡

”Faild coup in #Ethiopia’s Amhara state was an attempt by ethnic nationalists to restore Amhara hegemony over all of Ethiopia that existed for several centuries prior to 1991.  That dream is now permanently dead.”

‹‹ባማራ ክልል ውስጥ የተካሄደው ያልተሳካው የመንግሥት ግልበጣ (ወያኔ ጦቢያን እስከተቆጣጠረበት) እስከ 1983 ዓ.ም ድረስ ለምዕተ ዓመታት ሰፍኖ የነበረውን ያማራ የበላይነት ለማስመለስ ያማራ ብሔርተኞች ያደረጉት ሙከራ ነበር፡፡  ይህ ህልማቸው ለዘለዓለም አሸለበ፡፡››

በኸርማን ኮኸን እሳቤ መሠረት ከወያኔ በፊት ኢትዮጵያ ‹‹የአማራ ኢትዮጵያ›› ስትሆን፣ ኢትዮጵያን ‹‹የኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያ››  ያደረጋት ወያኔ ነው፡፡  ይህ ደግሞ የወያኔና የኦነግ ፀራማራ ትርክት ነው፡፡  ያሁኖቹ የአሜሪቃ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪቃ ክፍል ኃላፊወች (ሱዛን ራይስ፣ ጌይል ስሚዝ፣ ሰማንታ ፓወር፣ አንቶኒ ብሊንክን፣ ጀፍሪ ፊልትማን፣ ወዘተ. ) ደግሞ የኸርማን ኮኸን ደቀመዝሙሮች ስለሆኑ፣  ወያኔንና ኦነግን የሚያፈቅሩ የአማራ ሕዝብ ቀንደኛ ጠላቶች ናቸው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአማራን ህዝብ በማጥፋት ወያኔና ተቃዋሚው በጋራ እየሰሩ ነው – ከወለጋ ከቄለም አካባቢ እና ከግንቢም ቁጥራቸው ከ2 ሺ እስከ 3 ሺ የሚደርስ የአማረኛ ተናጋሪዎች ተባረሩ

ጀፍሪ ፊልትማ ወደ አዲሳባ መለስ ቀለስ የሚለው ላንድና አንድ ዓላማ ብቻ ነው፡፡  ዓላማውም ኸርማን ኮኸን ለንደን ላይ የፈጸመውን ዓይነት ደባ፣ እሱም በተራው አዲሳባ ላይ በመፈጸም የአማራን ሕዝብ ዳግመኛ ለማዋረድ ብቻና ብቻ ነው፡፡

ስለዚህም የአማራ ሕዝብ በጀፊሪ ፊልትማን (ባጠቃላይ ደግሞ የአማራ ሕዝብ ቀንደኛ ጠላት መሆኑን በግላጭ ባስመሰከረው ባሜሪቃ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር) በኩል የሚደረግን ማናቸውንም ዓይነት ስምምነት እንደማይቀበለው ማወቅ ለሚገባው ሁሉ አንሮና አበክሮ (loud and clear) ማሳወቅ ይኖርበታል፡፡  በተጨማሪ ደግሞ በአሜሪቃ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አደራዳሪነት አማራን ወክየ እደራደራለሁ የሚል ደመቀ መኮንንም ሆነ ሌላ ማናቸውም ግለሰብ፣  የአማራ ወኪል ሳይሆን የአማራ ሕዝብ በትልቅ ወንጀል የሚፋረደው የአማራ ቀንደኛ ጠላት መሆኑን በግልጽ ሊነገረው ይገባል፡፡

 

መስፍን አረጋ

mesfin.arega@gmail.com

1 Comment

  1. የያኔውም ኮኾን ሆነ የአሁኑ ፊልትማን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ የማስፈራሪያ በትሮች ናቸው። አሜሪካ አሁን በምታራምደው የውጭ ጉዳይ ፓሊሲ እንደ ሰካራም ሰው መንገዳገዷ ግልጽ ነው። ሃገሪቱ በሞራልም ሆነ በሃገሯ ባለ የፓለቲካ አቲካራ ነገርች እየተመናመኑ ክፉኛ አዘምብላ ለመውደቅ እንደሚቃጣት አመላካች ነገሮች አሉ። በዓለማዊው የቁስ ፍቅርና በፈጠራ ወሬ የደነዘዘው ህዝባቸውን ለምን እንዴት ብሎ የሚጠይቅ አይደለም። የዜና አውታር አቀባዪችና ዜና አናፋሾች ራሳቸው በኮርፓሬሽን የተሸመቱ በመሆናቸው ማን ወሬዬን ስፓንሰር ያረግልኛል እንጂ ስለ ዜናው ጥራትና ብቃት አይገዳቸውም። ከህዋላ የሚዘውራቸው ባለ ሃብቱ ስፓንሰር አድራጊ በመሆኑ ይህን ወሬ ብታናፍስ ዋ ስለሚባሉ ለመኖር የውሸትና የፈጠራ ወሬ ሲነዙ ኖረዋል አሁንም የበሬ ወለደ ወሬአቸው ቀጥሏል። ይህና መሰል ነገሮች በተለይም ራስ ወዳድና የጥቁር ህዝቦችን የሚጸየፈው ዶናልድ ትራምፕ የዘራው የጥላቻ ዘር በቅሎ አሁን እንሆ ሃገሪቱን ለሁለት ከፍሎ እያነታረካት ይገኛል። ጉዳዪ ይቀጥላል። ፍልሚያው በነጮች ነገር አክራሪዎችና በተቀረው ግራ ዘመም ጠንጋራና ያለ ልክ ተለታጭ የፓለቲከኞች እይታ በመሆኑ።
    ኮ/መንግስቱ ሃ/ማሪያምን በማታለል ከሃገር እንዲኮበልል ባደረጉበት ሴራ ጠ/ሚ አብይንም ለማስደንገጥና ለማባረር ያደረጉት ምንም አይነት መሻሻል ያልታከለበት ሴራቸው ዓለም ሁሉ ያየው ጉድ በመሆኑ አሜሪካ በአለም ሁሉ የተናቀችና የተጠላች ሃገር አድርጓታል። አሜሪካ ሃገር ማፍረስ፤ በኢኮኖሚ ማዕቀብ ህዝቦችን ማስራብ አልፎ ተርፎም ብቁ የሆኑ የሃገር መሪዎችን በተለያየ መንገድ መግደል የተካኑበት ተግባር ነው። እኔ ከፊልትማን ጋር መነጋገሩ ምንም ፋይዳ አይሰጥም። ፊልትማን በራሱ የማያስብ በስቴት ዲፓርትመንት አክራሪዎችን በቁሙ እንቅልፍ በሚወስደው ፕሬዝደንት የሚዘወር ራሱም ጭምር ያንቀላፋ ሰው ነው። አሁን በሱማሊያ፤ በሱዳን የምናየው በዚህም በዚያም መካረር የአሜሪካ እጅ አለበት። ኢትዮጵያና ኤርትራ ላይ የሚፈጸመውን በደል ያው በየጊዜው የምናየው ስለሆነ መደጋገም አያስፈልግም። ለአፍሪቃ ቀንድ ሰላም ነው ይሉናል አሜሪካኖች ራሳቸው በአንድ እጅ እሳት በሌላ እጅ ስንዴ ታቅፈው? አሜሪካ የጥቁር ህዝቦች ጠላት ናት። ዞር ብሎ ዝርያቸው በሰንሰለት ታስረው ወደ አሜሪካ የመጡ አፍሪቃዊያንን የቀድሞ ሰቆቃና የዛሬውን ጫና በመመርመር ይህን መረዳት ይቻላል። ጥቁሩ ህዝብ ለነጭ ያለውን እይታ መቀየር መቻል አለበት። ከጥቁር ዶክተር የነጭ ድሬሰር ይሻለኛል ከሚል አስተሳሰብ መውጣት አለብን። ሌላው ሁሉ አተካራ ከንቱ ነው።
    አሜሪካ በራሷ የቆሰለች ሃገር ናት። ከእውነት እየራቀች በሄደች ቁጥር ይህ ቁስሏ እየበረታ እየሄደ ነው። ስለሆነም የፊልትማን ወደ ኢትዮጵያ መመላለስ የላላውን ሴራ ለማጥበቅ እንጂ ለኢትዮጵያ ህዝብ ገዶት አይደለም። ወያኔና የአሜሪካ የውጭ ፓሊሲ ተመሳሳይነት አላቸው። ሁለቱም ደም ያፈሳሉ። ሁለቱም ይዘርፋሉ፡ ሁለቱም ለህዝብ ነው ይላሉ። ሌላም የሚመሳሰሉበት መንገዶች አሉ። አንባቢ ረጋ ብሎ ይፈተሽ። በቅርቡ ቫይስ የተሰኘ የጋዜጠኞች ቡድን ሱዳን በሚገኙ የስደተኞች ካምፕ በመሄድ በሰራው ዘገባ ምን ያህል የሰው ልጅ ህይወት የተመሰቃቀለ እንደሆነ ማየት ይቻላል። ሴቶች ይደፈራሉ፤ ወንዶች ይደበደባሉ፤ ከስደተኛ ካምፕ ወጥቶ ወደ ካርቱም ለመሄድ እስከ 1ሺ ዶላር ይጠይቃሉ። ከፍለውም የሚሄድ አሉ። በመንገድ ይያዛሉ። ተመልሰው ይላካሉ። ካርቱም የደረሱትም 4ሺ አካባቢ ዶላር ካመጡ ወደ ሊቢያ ይተላለፋሉ። ከዚያም የሚሞተው ሞቶ ሌላው ሲደርስ እስር ቤት ይታጎራሉ፤ ጥቂቱ ደግሞ ሌላ ክፍያ በዘመድና በሌላም መንገድ ከፍሎ ጀልባ ላይ ይወጣል፤ በጣም ጥቂቱ ከባህር እልቂት ተርፎ በደረሰበት መጠለያ ይገባል። አሁን አሁን አውሮፓ ራሱ የደረሱትን የአፍሪቃ ሰዎች መልሶ ለመላክ ዝግጅት እያረጉ ነው። ይህ ነው እንግዲህ የራስን ቤት አፍርሶ ህዝብን ጨፍጭፎ ለአረብና ለነጭ ተበደልን በማለት መጮህ የሚያስከትለው የመከራ ዶፍ። ይህ እንግዲህ በሱዳን የተለያዪ ካምፓች ወያኔ እያስታጠቀ ሰርጎ እያስገባ ከሚያስጨርሳቸው የተረፉት ናቸው። ግፍ በግፍ ላይ። የሰው አንገት የቀላው የወያኔ መንጋ አሁን ራሱ በሰው ሃገር ተቅበዝባዥና ሟች ሲሆን። ዘፈን ቢዘፈንለት፤ ቀረርቶ ቢያቅራሩ፤ እንዲህ ነበርን ቢሉ ጊዜ አሽቀንጥሮ ሲጥል የሚያነሳ የለም። ሞት ለሁሉም የማይቀር እዳ ነው። ግን በሱዳን ውስጥ ያሉ የትግራይ ተወላጆች የማይረድት ነገር እርዳታ አቅራቢው፤ አከፋፋዪ ሁሉ በስማቸው እንደሚነግድ ነው። በምንም አይነት የሂሳብ ስሌት ሰው በሰላም በሃገሩ ከመኖር የተሻለ ምንም አማራጭ ነገር የለም። ለዚህ ነው ወያኔን በማስወገድ የትግራይ ህዝብ ራሱ በመረጠውና በሚፈልገው መንገድ መኖር መቻል አለበት የምንለው። ጠበንጃ አንግቦ ነጻ ምርጫ የሚባል ነገር የለም። አሜሪካም ሆነ አውሮፓ የእኛን መገዳደል ይፈልጉታል። የጥቁር ህዝቦችን ልዕልና ማንም አይፈልግም። በዚህ ፍራቻ ነው ዛሬ ኤርትራን፤ ሱማሊያን፤ ኢትዮጵያን የሚያምሱት። ስንገዳደል ደስ ይላቸዋል። የወሬ ማሟያ እንሆናለን። እይታችን ይቀየር። ነጮችና ተግባራቸው ለየቅል ነው። መገዳደላችን ይቁም። የህዝባችን እንባ ይገታ። በቃኝ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share