በአሁኑ ሁኔታ የአማራንና የአፋርን ነዋሪ ደህንነት መከላከል የሚቻለው በዋናነት በትግራይ ውስጥ የመከላከያ ዞን ሲኖር ነው

ከ ዚዜው ደረስ Gezew.derese@bell.net

የሰሞኑ ጭውውት የህወሀትን ተስፋፊ ሀይል ከአማራና አፋር ክልል ጠራርገን አወጣነው በብዙ ሽወች የሚቆጠሩትንም ደመሰስን ማረክን ሰለዚህም ሰራዊቱ የመጀመሪያ ዙር ተልእኮህን አጠናቋል እና ባለበት ይቁም ተብሏል የሚለው ነው፡፡

የመንግስት ባለህበት ቁም የሚለው ትእዛዝ እጅግ ያልተጠበቀና ግራ የሚያጋባ እርምጃ ስለመሆኑን ብዙዎች ይስማማሉ፡፡ በተለይም ደግሞ የትግራይ ህዝብ የጥሞና ግዜ እንዲያገኝና እንዲሁም ገበሬውም የእርሻ ጊዜው ሳያልፍ ወድ እርሻው እንዲሚለስ እድል ለመሰጠት አንድ ጎን ተኩስ ማቆም ብቻ ሳይሆን ከመላው ትግራይ በፈቃዳችን ለቀን ወጥተናል ብሎ በተናቀረ በቀናት ውስጥ እግር በእግር እየተከታተለ ህወሀት የከሰተውን ሰፊ ወረራ የሚያስታውስ ሁሉ የአሁሁን የምንግስት እርምጃ በጥራሬ ቢሚለከትው የሚገርም አይደለም፡፡

ሀዚህ ጋር ተያይዞም የሚነሱትን ጥይቄውች ውስጥ ጥቂቱ የሚከተለውን ይመስላሉ፡፡

የተፈናቀሉት፣ የአስገድዶ መደፈር ሰላባ የሆኑት ምክንያቱ ሳይገባቸው ሀብት ንብረታቸውን አንዲሁም ቤተስቦቻቸውን ያጡ የአፈርና አማራ ተወላጆች ገና ለደረስባቸው ግፍ ጊዜ አግኝተው በአግባቡ ማስብ ሳይችሉ ሀዘናቸውን በቅጡ ሳይወጡ እጅግ ብዙወቹም ተሰደው ከሚገኙበት የስደት ጣቢያም ይሁን ዘመድ ተመልሰው የደረስውን ጉዳት በአግባቡ ሳይመለከቱ በቃ በ እናነት ላይ የተካሄደው ወረራን ያካሄደው አካል ላይ የሚካሄደው እንቅሰቃሴ በዚሁ ይቆማል መባሉ ጊዜውን የጠበቀ ነውን? የሚለው የመጀመሪያ ጥያቄ ነው፡፡

ለዚህ ተጎጂ ህዝብ የሰላም ማረጋገጫው እንዲህ በ ሀዝብ ግንኙነት ሹም በኩል በሚነገር የ10 ደቂቃ መግለጫ መሆኑ ከስቃዩ ጥልቀትና ካስከተለውም ጠባሳ አንጻር ሲታይ የሚመጥነው ነውን? ይህ ህዝብ ከደረስበት ግፍ አንጻር የሚገባው የማስተማመኛ ንግግር የመንግስት መገናኛ ፐረስ ኮንፍረንስ የሁለት ጥያቄዎች ምላሽ የሚመጥነው ነውን? ለመሆኑ ለተጎጂው የስነልቦና ስብራትና ሀዘን መንግስታዊ ማበረታቻው ይህ መሆን ይኖርበታልን? ይህስ መተማመንን ሊገነባ የሚችል ለየት ያለ ማህበራዊ ይዘት ያለው ወይይት አያስፈልግም ነበር ? ፍራቻቸውን ተስፋቸውንና ምን ቢሆን ምን ቢደረግ መረጋጋት እንደሚሰማቸው፣ ማማከር በየጊዜ ሊከሰት ለሚችለውን የስሜት መዘበራረቅ ምን መደረግ እንደሚገባው ወዘተ ከተጎጂው ህብረተ ስብ ጋር መመካከህ፣ መነጋገር ተገቢ አይሆንም ነበርን?

ተጨማሪ ያንብቡ:  ለአርቲስት ታማኝ በየነና ለሻምበል በላይነህ በእስራኤል የተደረገላቸው የጀግና አቀባበል ቪድዮ

እንዴት ነው ከአማራና አፋር ክልል ተጠራርጎ ወጥቷል የተባለው ሀይል አሁንም ሰሜን ጎንደርና ወሎ ውስጥ ቢይንስ ሶስት ወረዳ ውስጥ የሚገኘው ? እንዴት ተጠራርጎ ወጡ የተባለው ህወሀቶች በሁሉቱም ክልል በአራት አቅጣጫ ሶስት ቀን ባልሞላ ጊዜ መልሶ ለማጥቃት ብቃት ያገኙው ፣ ይህስ ከሆነ መልሶ ለማጥቃት ከምንገምተው በላይ እምቅ ሀይል ይኖረው ይሆን?

በአፋርና አማራ ክልል የተማረኩት የህወሀት ተዋጊዎች በአብዛኛው ብዙም ስልጠና ያልወስዱ ህጻናትና ከየቦታው የተለቀሙ የትግራይ ተወላጆች እንጂ ለአመታት የሰለጠነው የትግራይ ልዩ ሀይል አባላት አልነበሩም፡፡ ታዲያ ያ በሰሜ እዝ ላይ ታላቅ ጥፋትን የፈጸመ እጅግ የሰለጠነ ጦር የት ነው ያልው? ለመቼና ምንን ለመውጋት አድፍጦ ይሆን የሚሉ እጅግ ረባሽ ጥያቄዎችን እስነስቷል፡፡

ታዲያ ይህ ጉዳይ አሁን የተወሰደው ውሳኔ የአማራና የአፋር ህዝብ ለሌላ ዙር ጥቃትና ወረራ ተጋላጭ ያደርገው ይሆን? ይህ በያንዳንዱ ዜጋ መጠየቅ የሚገባው ጉዳይ ነው፡፡

ቀድም ሲል የኢትዮጵያ ሰራዊት ከትግራይ ሲወጣ “እንደጉም ተበትኗል፣ የተባለው ጦር አማራና አፋር በመዝለቅ እጅግ ስፊ ግፍና ውድመት ያደረሰ መሆኑን ሁላችንም አንረሳም፡፡ ይህ አሁን እንዳይደገም የሚከተሉትን እሰነዝራለሁ፡፡

ሰለታገስን ወይም እኛ የሞራል ከፍታ ባለው መንገድ ትግሉን ለመምራት ብንፈልግም ሀወሀት በተመሳሳይ ደረጃ ይመጣል ማለት አይደለም፡፡በሩጫ ላይ የነበረው ህወሀት የመንግስትን ተኩስ ማቆም የሚጠቀምበት፣ትንፋሹን ስብስቦ በሁሉም መልክ ራሱን ለማጠናከር ነው፡፡ይህም ሰለሆነ በምንግስት በኩል ከዚህ ቦታ አናልፍም ሰለተባለ ጦርነቱ ይቆማል ማለት እንዳልሆነ ግልጰ ሊሆን ይገባል፡፡

ህወሀት ቂመኛ ድርጅት ነው፡፡ በተለይም አማራ የሚባለውን ህብረተስብ አንገት ካላስደፋ አርፎ አይተኛም፣ ይህንንም ፣ ከጦርነቱ በፌት ለ 27 አመታት የአሁኑ ጦርነት እንደታወጀም ከነ ጌታቸው ረዳና ደብረጽዮን አንደበት በተደጋጋሚ የሰማነው ነው፡፡ ይህም ህወሀት አቅም እስካገኘ ድረስ የጦርነቱን ቀጣይነት አይቀሬ መሆነን ያሳያል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ባክኖ የቀረ  አየር ኃይል - ክንዴ ዳምጤ - ሲያትል

ህወሀት ወልቃይት ጠገዴን አጥቶ መኖር አይፈልግም ምናልባትም አይችልም፡፡ ለዚህ ሲል የትግራይን ህዝብ እንዲከፍል የማይጠይቀው ዋጋ የለም፡፡ ሰለዚህም አሁንም እነዚህን ቦታዎች መልሶ እስካልያዘ ድረስ ጦርነቱ አይቀሬ ነው፡ይህ ደግሞ በወያኔ የሚቀነቀን ብቻ ሳይሆን ባእዳን ሀገራትም የአማራ ሰራዊት ከወልቃይት ጠገዴና ራያ ይውጡ እያሉ ደጋግመው በመናገራቸው ሀወሀትን ያልተጨበጠ ተስፋ ይዞ እንዲጓዝ መሆኑን መዘንጋት አያሻም

የተለያዩ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ህወሀት አሁንም በግድም ይሁን በውድ ሰራዊት እየመለመለና እያሰለጠነም ነው፣ ይህ ታዲያ ለጦርነት የሚደረገውን ዝግጅት እና የዚህም የመጀመሪያው ተጠቂ ተጎራባች ክልሎች እንደሚሆኑ ግልጽ ነው፡፡

ታዲያ ነባራዊው ሁኔታ በህወሀት ተንኳሽነት የጦርነቱን አይቀሬነት ካመላከት ፣ በዚህ በኩልስ ምን ይደርግ የሚለው እጅግ ወሳኝ ይሆናል፡፡ ለወታደራዊ ባለሙያውች ጥልቅ እስትራተጂውን ተቼ እንደ አንድ ዜጋ በኔ እይታ የሚከሉትን ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ይታየኛል፡፡

የጦር እዋቂወች እንደሚሉት፣ ስላምን ከፈለግክ ለጦርነት በበቂ ተዘጋጅ ፡፡ The original Latin of the expression “if you want peace, prepare for war” የአማራም ሆነ የአፋር ህዝብ ራሱን ለመከላከል መደራጅት ለጦርነት ብቃት ባልው ሁኔታም ዝግጁ ሆኖ ይገባል፡፡ ይህም በሰው በሰው ሀይል፣ በመሳሪያ ጥራትና ብዛት፣ በስንቅና በስላላ ተግባር ወዘት መሆን ይኖርበታል፣ ይህ የጦርነቱን

በመላው ሀገሪቱም ይህን አደጋ ግንዛቤ ውስጥ ያስገባ ሁሉን አቀፍ ዝግጅት አጠናክሮ መቀጠል ያሻል፣ መዘናጋት አያሻም፡፡

ከዚህ በተጭማሪ በዋናነት ህወሀትን ሀይል በሀገራችን ላይ ምንም አስጊ ጉዳት ወደማያደርስበት ወታደራዊና ፖለቲካዊ ደረጃ ዝቅ እንዲል የሚደረገው ጥቃት እንዲቀጥል ማድረግ እንዳለ ሆኖ፣ የሀወሀትን ጥቃት በሌሎች ክልሎች ጉዳት ማድረሱን ለመከላከል አንዱ መፍትሄ በትግራይ ክልል የመከላከያ ቀጠና (ባፈር ዞን) መመስረት አስፈላጊ ነው ፡፡ የመከላከያ ቀጠና (ቡፈር ዞን) መመስረት አስፈላጊ ህወሀት በአጎራቻች ክልሎች ላይ የማያቋርጥ ስጋትን በመደቀን ከተረጋጋ ህይወታቸን እንዳያበላሽ፣ በተለመደ ባህሪው ድንገተኛ ወረራን ለማካሄድ ሙከራ ቢያደርግ ገና ከጅምሩ ለማምከን በሱስተኛ ደረጃም በአካባቢው ለሚገኘው የትግራይ ህዝብ ሙሉ ድጋፍን በመስጠት ለሊአላውም የትግራይ ህዝብ ከ ህወሀት ተላቆ መኖር የሚኖረውን ጠቀሜታ በማሳየት ለዚህም ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ እንዲያደርገ ተጨማሪ ድጋፍን ለመስጠት ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ቋንቋ ለብልሆች የመግባቢያ መሣሪያ፤ ለደናቁርት ግን ሕዝብ መከፋፈያ - በገ/ክርስቶስ ዓባይ

የመከላከያ ቀጠና (ባፈር ዞን) መመስረትና በዚህም መሰረት ይህዝብን ድህንነት ማረጋገጥ በአለማችን የማይታወቅ ጉዳይ ሳይሆን በተለይም እንከ አሁ ድረስ እስራሴል ብጎላን ክፍተኛ ተራሮች በኩል እንዲሁም ብዙወች ፓለስትኒያኖች በሚኖሩበት መእራባዊ ድንበሯ ( ዌስት ባንክ) በኩል የመሰረተቻቸው የመከላከያ ቀጠናዎች የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የሁለተኛውን የአለም ጦርነት ተከትሎ እስታሊን በሀገሩ ዙሪያ በፈጠራቸው የመከላከያ ቀጠናዎች የተባበረውን የመራቡን ሀይል እንዳይወረው ከፍተኛ መከላከያ ሆኖት እንደኖረ ታሪክ ያሳየናል፡፡

ላይ የተጠቀሱት ሁለቱም ምሳሌዎች በተለያዩ ላላዊ ምንግስታት መሀል የተካሄደውን የሚያመለክቱ በመሆኑ የኢትዮጰያ አንድ አካል ከህፕነችው ትግራይ ጋር ሙሉ በሙሉ አንድ እንዳልሆነ እገነዘባለሁ፡፡ ቁም ነገሩ ግኝ የመከላከያ ቀጠና (ባፈር ዞን) በመመስረት እርፎ ከማይተኛ ጦረኛ ሀይል ሀገርና ህዝብን እንዴት መከላከል እንደሚቻል ማሳየት ሰለሆነ ሊወራረሱ የሚችሉትን ሀሳቦች መመርመርና መተግበር ነው፡፡

በመጨረሻም ለትግራይ ችግር መፍትሄ ማግኘት የሚቻለው በወታደራዊ የበላይነት ብቻ ሳይሆን ከህወሀት ውጭ የሚገኘው ሌላው የትግራይ ሀይል ጋር ግልጽ ያለ ድፍረት የተሞላው ንግግር በማድረግ የወደፊት እጣ ፈንታንም እንድ ምእራፍ ላይ ማድረስ አስፈላጊ ይሆናል፡፡

4 Comments

  1. The TPLF forces have suffered devastating losses in Afar and Amhara and may not represent any threat to these front line regions. However, they should remain prepared for any possible TPLF attacks conventionally or using guerilla forces. Considering the human losses the TPLF has been suffering in multiple fronts, the people of Tigray will not be able and willing to offer more cannon fodder to satisfy the egos of the old and fascist leaders of the TPLF.

  2. የገባህ ነህ። ድንበር ላይ ቆመህ ኑ እና ግጠሙኝ አይባልም እንደ ሰፈር ህጻን። እንግዲህ ለእኛ ያልታየን ብዙ ጉዳይ እንዳለ ሆኖ በህቡዕም ሆነ በተናጠል ወያኔን በሃገሩ ውስጥ ማበራየት ለሚከተለው እርምጃ ጠቃሚነት አለው። የሚደረጉ ነገሮች ሁሉ ከበሮ እየተመታ መሆን የለበትም። እንዴት ሰው ከእስራኤል አይማርም። ጦርን ድንበር ላይ አስፍሮ መቀመጥ ግን ለታሰበም ሆነ ላልታሰብ ጥቃት ያጋልጣል። ሊታሰብበት ይገባል። አሁን በአማራና በአፋር ክልል ወያኔ ያደረሰውን በደል ሲዘረዝሩ እንባን ከማፍሰስ ይልቅ እንዴት ባለ መልኩ ብንደራጅና ብንታጠቅ ነው ዳግመኛ ከዚህ መሰል ጥፋት ጋር የምንጋፈጠው በማለት መዘጋጀት አስፈላጊ ነው። ይህ መሰልጠንና መታጠቅ የኦሮሞ ጨካኞችንም ለመፋለም ዋና መሳሪያ ይሆናል። በመፈናቀልና በመሮጥ ምንም ማምለጥ አይቻልም። ከመከራ ወደ መከራ መሄድ እንጂ።
    በቅድሚያ የውስጥ አርበኞችን መመንጠር አስፈላጊ ነው። ከወያኔ ጋር ተባብረው ሰው ያስገደሉ፤ የዘረፉ፤ አማራ፤ ኦሮሞ፤ ትግሬ ምንም ይሁን ማንም አይቀጡ ቅጣት በመስጠት ሌላውን ማስተማር ያስፈልጋል። አሁን የወደመው ወድሟል፤ የተዘረፈው አይመለስም፤ የሞተውም ሞቷል። ግን እንዴት ለሚቀጥለው ፊልሚያ እንዘጋጅ ነው የቅድሚያ እቅድ። እንበል አሁን የዶ/ር አብይ መንግስት ተንገዳግዶ ወያኔ ዳግም ወረራ ቢያረግ ማንንም እንደማያተርፍ የታወቀ ነው። አሜሪካና ሌሎችም አሁን ሌት ተቀን የሚሰሩት የአብይን መንግስት ለመናድ ነው። አይሆንም ከማለት ቢሆን ብሎ መዘጋጀት አስፈላጊ ነው። በቃኝ!

  3. The Tigray people should reconsider their immense and senseless sacrifices for the sake of keeping the political and economic interests and hegemony of the Adwan elite. This elite has already established their families in the west and is not affected by the war they have started and conducting. To these elite,the death and destruction in Tigray are entertainments.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share