ሰሜን ወሎን ወደ“ደቡብ ትግራይ” ደቡብ ወሎን ደግሞ ወደ “ሰሜን ኦርምያ” የማጠቃለሉ ቅዠት (እውነቱ ቢሆን)

ፋኖ ብዙ ጠላት እንዳለው ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ለዚህም ነው በደሴ የተፈጸመን የወሎ ህብረትን ዘረፋ ወደ ፋኖ ላማላከክ የተሞከረው፡፡ ፍኖ የ46 ሚሊዮን የአማራ ህዝብ ሙሉ ድጋፍ አለው፡፤ ጠላቶቹ አማራን መክተው በፊቱ ሊቆሙ አይችሉም፡፤ ዳሩ ግን ምን ያደርጋል አማራው በሚፈለገውና በሚገባው ልክ፣ ፍጥነትና ደረጃ በሁሉም ዘርፎች ገና በበቂ አልተደራጀም፡፡ ለ30ና ለ40 አመታት በወያኔ ከፍተኛ ደባና ተንኮል ተሰርቶበታል፡፡ የዘር ማጥፋት ተፈጽሞበታል፡፤ ደህይቶና ኋላቀር ሆኖ ተቀብሮ ኖሯል፡፡ አሁን ደግሞ በተረኛውና ምናልባትም ከወያኔ በበለጠ አማራን በሚያሰጋው በኦሮሙማ የረቀቀ ሴራና አማራን አጠላልፎና ከፋፍሎ የመጣል አደገኛ ቁማር እየተሰራበት ይገኛል፡፡፡የሆድ አደሮቹ አማራወች የብልጽግና ፓርቲ መሪወች የሆኑት እነደመቀ መኮንንም በሁለት እግሩ መቆም ያልቻለውን ባለ አንድ እግሩን የኦሮሙማ መንግስት ያንኑ አንድ እግሩን በትከሻቸው ተሽክመው አንዳልጦት እስክሚከሰከስ ድረስ እሹሩሩ እያሉት ይገኛሉ፡፡በተጓዳኝም እነዚሁ ሆዳሞች የአማራ አለኝታ የሆነውን ፋኖን እንዳይደራጅ የቻሉትን አፈና፣ እቀባና ክልከላ <እስካስኬዳቸው ድረስ> ማድረጋቸውን ቀጥለውበታል፡፡

አማራው በትክክልና በሀቅ ቢቆጠር ብዛቱ ከ46 ሚሊዮንም ይበልጣል፡፤ይህንን እውነታ ወያኔና ኦነግ ዱሮ ገና ሳይጣሉ በፊት በጋራ በአማራ ላይ ቆምረው የሰሩት ቁማር መሆኑን የወደቀው የወያኔ መንግስትም ተረኛው የኦሮሙማ መንግስትም ሁለቱም ያውቁታል፡፤ ዘግይቶም ቢሆን መላው የአማራ ህዝብም ይህንን የተሰራበትን ሸፍጥና ደባ ጠንቅቆ ያውቀዋል፡፤ወደፊት ትክክለኛ የህዝብ ቆጠራ በመላው ኢትዮጵያ ውስጥ በሀቅ ሲደረግ ሁሉም ህዝብ ልኩንና አቅሙን ብዛቱንና ማንነቱን ለይቶ ያውቃል፡፤ ያኔ እውነቱ ፈጥጦና አግጥጦ ሲወጣ አማራው ለአመታት በሸፍጥ የተሰራበት የበጀት ድልድልና የድምጽ አሰጣጥ ቁማሮች እንዴት ይቆመርባቸው እንደነበረ ገሀድ ይወጣሉ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የኦሮሞ ህዝብ መሪ ማን ነው? “ሀገር ወዳዱ” ዓብይ ወይስ “ራስ ወዳዱ” ጃዋር?

የአሜሪካ ዜግንቱን ስለመመለሱ በቂ ማረጋገጫ ያላቀረበውና ወደር የለሹ እብሪተኛ ጃዋር መሀመድ “ግማሽ መንግስት እኔ ነኝ” ብሎ በይፋ ከማወጅ አልፎ ሁሉንም አይነት ግፍና ሰቆቃ በድፍን ኦሮሚያ ባለው ከ7 እስከ 8 ሚሊዮን በሚቆጠረው የአማራ ህዝብ ላይ ፈጽሟልም አስፈጽሟልም፡፡ በተረኝነትና የኬኛ ፖለቲካ ያበጠው የኦሮሙማ ቡድን እንደሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ሁሉ አገሬ ናት ብሎ በኦሮሞያ ክልል ለዘመናት የኖረውን አማራን “ነፍጠኛ ውጣ”፣ ይህ የኦሮሚያ መሬት ለአማራ አገሩ አይደለምና እዚህ መኖር አትችሉም…ወዘተ እያስባለና በተለይም አማራዎች በሆኑ እናቶች ላይ፣ እርጉዞች ላይ፣ ገበሬወች ላይ፣ በሴት ዩኒቨርሲቲ ተማሪወች ላይ …ወዘተ እጅግ ሰቅጣጭና ዘግናኝ ግፎችን፣ ጭካኔወችንና እንሰሳዊ ድርጊቶችን ፈጽሟል፤ አስፈጽሟል፡፡የኦሮሞ ክልል መሪ ተብየወቹና አንድ ጊዜ “ነፍጠኛን ሰብረነዋል” ሌላ ጊዜ ደግሞ “በማፍዘዝም በማዘዝም” እያሉ የሚመጻደቁት ባለውቅቶቹ እነሽመልስ አብዲሳም ታሪክ ይቅር የማይለው ደባ በአማራው ላይ ከመፈጸም ዛሬም፣ አልታቀቡም፡፡ ማንን ፈርተው? ምንንስ ፈርተው?? መንግስትና ህግ አለ በሚባልበት አገር ይህ መሰሉ ዘግናኝ ድርጊት በአሁኑ ዘመን በአማራው ላይ መፈጸሙን ማንም ምንጊዜም ሊረሳው የማይችል ጉዳይ ነው፡፤ ድርጊቶቹ በሙሉ ለአማራው የአእምሮ ቁስልና፣ የስብእናው ርክሰቶች ሆነው ለዘለአለም ይኖራሉ፤፡ ጃዋር ይህንን ሁሉ ሲያደርግ አብይ እያወቀ ተባባሪ በሚመስል መልኩ ምንም ሳያደርገው ቆይቶ ሳለ በስተመጨረሻው ላይ ግን ጃዋር አብይ አህመድ የተቀመጠበትን ወንበር መነቅነቅ ሲጀምር እስር ቤት ሊወረውረው በቅቷል፡፡

ወሎን ሰሜን ኦሮሚያ የማድረግ የኦሮሙማ ጥረት የተጀመረው ቀደም ብሎ ነው፡፤ ለዚሁም ይረዳ ዘንድ “የወሎ ህብረት’ የሚል ለኦሮሚያ መስፋፋትና ታላቅነት የሚሰራ ድርጅት በደሴ ተፈጠረ፡፡ አብይ አህመድ አሁንም የኢትዮጵያ መሪ ነኝ እያለና ለኦሮሙማ የበላይነትና መስፋፋት በድብቅም በገሀድም እየሰራ ባለበት ወቅት ወሎን ሰሜን ኦሮሚያ የማስደረግ የሴራ ፖለቲካውን ቀጥሎበታል፡፡ አብይም ይህንኑ አስቀጥሎ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከሰሉ ያለቀበት ባለ እጅ ሆነናል - መኳንንት ታዬ (ከሚኒሶታ)

እዚህ ላይ ጃዋር በሉት ዳውድ ኢብሳ፤ አብይ አህመድ በሉት መራራ ጉዲና የኦሮሙማን አመለካከትና እምነት እንደዚሁም ኦሮምያን በሌሎች ላይ በማስፋፋትና የበላይ በማድረግ አንድ ናቸው፡፡ ወያኔ እንደ ቅማንት ነጻ አውጭና አገው ነጻ አውጭ… ወዘተ እያለ እንደጠፈጠፋቸው ጸረ አማራ ስብስቦች ሁሉ ኦርሙማም በወሎ የራሱን አሻንጉሊት ለመጠፍጠፍ አልቦዘነም፡፡ይህ ስሌትም ሁሉንም የኦሮሙማ አንጃወች አንድ ያደርጋቸዋል፡፡ ከዚሁ ቅዠት አንጻር ሰሜን ወሎ ወደ “ደቡብ ትግራይ” እንደዚሁም ደቡብ ወሎ ወደ “ሰሜን ኦሮሚያ” ይጠቃለላሉ ማለት ነው፡፡በዚህም የቅዠት አካሄድ የሚያስፈራው ሁለቱም ቅዠታሞች የሰሜን – ደቡብ ድንበራችን ነው ብለው በሚያስቡት ቦታ ላይ ሲገናኙ እንዳይዋጉ ነው፡፤ መቼስ ቅዠት አይደል??

ከወያኔና ኦሮሙማ ቅዠት አንጻር ሌላው ገራሚ ነገር ባለሰፊ ታሪኩ የንጉስ ሚካኤል አገር “ወሎ” አይኖርም ማለት ነው፡፤ ለነገሩኮ ፍርጃ ሆነና ወሎ ከደርግ ስርአት በስተቀር በሶስቱም ስርአቶች ጥርስ ውስጥ የገባ ህዝብ ነው፡፡ በጣልያን ወረራ ወቅት ንጉሱ ወደ ውጭ ሲሸሹ አትሸሹም ብሎ መንገድ በመዝጋቱ በንጉሱ ጥርስ ተያዘበት፡፡ “ከወያኔ ጋርም የተባበረ ጥቅር ዉሻ ይውለድ’ ብሎ ህዝቡ ላለመተባበር በመማማሉ የደረሰበትን ሁሉ ታሪክ መዝግቦታል፡፤ አብይ አህመድም ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ወሎ ሄዶ ስብሰባ ሲመራ በህዝቡ በተለይም በአንዲት አይነ ስውር ነገር ግን እጅግ ልባም ሴትዮ ለኦሮሞ ስለሚያደርገው አድሏዊነቱና በአማራ ልዩ ሀይል ትጥቅና ስልጠና ላይ ስለተናገረው ማጣጣልና ማጥላላትን አስመልክቶ ለቀረበለት ግልጽ ጥያቄ በተለይ ጉዳዩ እንዲያ ይፋ ሆኖ በመጠየቁ አብይ ቀንድ አውጥቶ ምን እንደተናገረ የሚዘነጋ አይደለም፡፡ ቪድዮው አሁንም አለ፡፡

ወደ ጉዳያችን ስንመለስ ይህንን የኦሮሙማ ቅዠት ተሸክሞ መሳሪያ በመሆን የአማራ አንዲነት እንዲላላ አጥብቆ በመስራት ያለው ‘የወሎ ህብረት” ከወያኔ ቀጥሎ በደሴ ከተማ ዘረፋን ያካሄደ ስብስብ ነው፡፡ ስብስቡ ዘረፋውን ያካሄደው እራሱ ሆኖ እያለ ይባስ ብሎ ዘረፋውን ያካሄደው የአማራ ፋኖ ነው እያስባለ የሀሰት ዜና በመንዛት ላይ ይገኛል፡፡ የደሴ ህዝብማ ፋኖን እንዴት እንደተቀበለው፣ እንዴትስ ብሎ ፋኖን በስስት አይኑ እንደሚያየው ህዝቡ እውነታውን በአደባባይ አስመስክሯል፡፤ የደሴን ህዝብ ከወያኔ አረመኔያዊ አገዛዝና ግፍ ነጻ ያወጣውን የፋኖን አቀባበልም ታሪክ በሰነዱ የደሴ ህዝብም በልቡ መዝግበውት ይኖራሉ፡፡ እነ አብይ አህመድ በወሎ ህዝብ ላይ ጭነው እየጋለቡት ያለው “የወሎ ህብረት” የተሰኘው የውርደት ፈረሳቸውም የትም ሳያደርሳቸው በወሎ ህዝብ “ንቁ” ንቀትና አማራዊ አንዲነት ፉርሽ ሆኖ ውርደቱን ይከናነባል፡፡ ሞት ለከፋፋዮች!

ተጨማሪ ያንብቡ:  የጎንደር መንፈስ ይጠራል (ክፍል - አራት) ከሥርጉተ ሥላሴ

4 Comments

  1. The OLF dieharders and remnants of Jawarism has to be completely removed from the Palace of His Majesty, Minlik the Second. Only after that, equality, fraternity and mutual respect among Ethiopians can be restored back. Unless and until these happen, no one, even the Conspirator Abiy Ahmed & his trojan horse, the Demeke group, will not be able to do the business as usual!!
    Like the sad end of the savage & brutal TPLF, days of OROMUMA are also numbered & will come soon to an end !!
    MaMa Ethiopia will flourish by the endless support & dedication of its people from all parts of the country. The highly expected genuine & solidifying federal system based on individual freedom & rights will bring the unity & territorial integrity of the nation as a whole. Long Live Ethiopia and God Bless Ethiopians!!

  2. ስም ይወጣል ከቤት ይከተላል ከጎረቤት እንዲሉ መዋስ አይገድምና እንዲያው “እውነቱ ቢሆን” የሚለውን ከየት ተዋስከው? በመሠረቱ የቃዥኸው አንተው ነህና ቅርብ እንኳን አይደለህም አማኑኤል ሆስፒታል ጎራ ብትል መድሃኒት ልታገኝ ትችል ይመስለኛል።ጀዋር መሀመድ የሰራው ወንጀል እኮ ተነግሮ ተነግሮ ወህኒ ቤት እየማቀቀ ነው ታዲይ የሱን ታሪክ በአሁን ሰዓት ማውራት የዛሬ አመት ለተወለዱ ለማያውቁት ህጻናት ለመንገር መለፋደድ አይመስልህም? አማራ እና ኦሮሞ ያገኙትን ተካፍለው ተዋልደው አብረው በልተው ጠጥተው ተፋቅረው የሚኖሩ በኢትዮጵያዊነታቸው የሚኮሩ ወገናሞች ናቸው። ሆኖም ግን እንደ አንተ እና መሰሎችህ ያለው ከፋፋይ ሆዳም አጋሰስ ጌኛ ሆድ አድረ ለመለያየት መሞከሩ ከመላላጥ በስተቀር በአንድነት ለሀገር ሰላም እና አንድነት የሚታገሉ ህዝቦች ናቸው።በሌላ መልኩ ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በወንጀለኛነት ስትመድብ ወህኒ ቤት ያለውን ጀዋር መሀመድንም በወንጀለኛነት ስትመድብ ለምንድነው ከነቤተሰቡ እስር ቤት ያለው የእንጀራ አባትህን አቦይ ስብስሃትን፤አይጥ ጉድጓድ የተደበቁትን የክርሥትና አባቶችህን ደብረ ጽዮን እና ጌታቸው ረዳን በቅዱስነታቸው ወይስ በሣጥናኤል መደብካቸው? መልሱ ለአንተ። በአንጻሩ ደግሞ “ፋኖ ብዙ ጠላት እንዳለው ሳይታለም የተፈታ ነው ” ስለአልከው የቋንቋ ተንታኝ ባልሆንም “ፋኖ” ማለት ከመንግስትም ሆነ ከወገኑ ዋጋ የማይፈልግ፤ለወገን እና ለሀገሩ ራሱን አሳልፎ የሚሰጥ፤በዱላም ሆነ በጂራፍ ጠላቱን ማርኮ ራሱን የሚያስታጥቅ የሚዋጋ እና የሚያዋጋ ፤አገር እና አካባቢ ሰላም ሲሆን አርሶም ሆነ ነግዶ ራሱን እና ቤተሰቡን የሚያስተዳድር ጀግና “ፋኖ” በመባል የተዜመለት አሁንም የሚዜምለት አሁንም ከመከላከያ፤ከልዩ ኃይል እና ከሚሊሺያው ጎን ተሰልፎ ታላቅ ጀብዱ እያስመዘገበ ያለው ነው።በመሆኑም አንተ ፋኖ የምትላቸው 46 ሚሊዮን ደጋፊ ካላቸውማ ጠቅላይ ሚስትርነቱን እና ፓርላማውን አትይዙም እንዴ? ለምን ያለቅሳሉ አንተስ ለምን እንባህ ይረግፋል? አንተ ፋኖ የምትላቸው እኮ እንደ “እውነቱ ቢሆን” ያሉ መውደቂያ ያጡ፤ በዱቢት አረቂ እና በፋጋ ጠጅ መሸታ ቤት ለመሸታ ቤት የሚንፏቀቁ፤ሲችሉ በታዛ ሺንት የሚከፍሉ ካልቻሉም ባሉበት የሚበሰብሱ ማውራ ራሶች ሲያጡ በሜዳ የሚተኩሱ ኪስ አውላቂ እና ጉሽጉሽ ደፊ ወያሌዎች ናቸው። ሰሚ የለህም

  3. ፋኖ ለአማራ ህልዉና መረጋገጥ እንጅ ስልጣን ፍለጋ ነፍጥ እናዳላነሳ ሁሉም ያውቀዋል፡፡ ይህንን እያወቁ ሆን ብለው የፈጠራ ወሬና አሉባልታ የሚያናፍሱ አያሌ የአማራ ሆድ አደር ቅጥረኞች በአማራው ውስጥ በሰፊው ተሰማርተዋል፡፡ የእነዚህ ቅጥረኞች ሚና በፊት ለወያኔ አሁን ደግሞ ለተረኛው ኦሮሙማ ፈረስ (Trojan Horse) ሆኖ እያገለገለ ካለው ከወራዳው የእነደመቀ መኮነን ጸረ-አማራ ስብስብ በምንም ስለማይተናነስ እየተለቀመ መመታት አለበት፡፡ ለምን ቢባል የቅጥረኞቹ አደረጃጀትና የተቀበሉት ጸረ- አማራ የሴራ ስምሪት አማራው በአንድ ላይ ቆሞ ለህውናውና ለአንድነቱ ለሚያደርገው ትግል አደገኛ የውስጥ መስናክል ስለሆነ ነው፡፡

  4. የወያኔም ሆነ የኦሮሙማ ጎጠኞችና መንደርተኞች ሆይ፦
    የአማራ ህዝብ ሁሉንም ጠላቶቹን ድባቅ የመምታት ታሪክ፣አቅም፣ ወኔና ችሎታ አለው፡፡ ያደርገዋልም!! በአፋርና በትግራይ ህዝብ መሀል እንደገናም በአማራና በትግራይ ህዝብ መሀል ለዘመናት የማይሽር ቂምና ጥላጫ አትርፎ የሞተው ሞቶ በህይወት የተረፈው እየተንጠባጠበ ወደ ትግራይ በመመመለስ ላይ ነው፡፡ ኦ
    ነግም እነ አብይ አህመድ ባወጡለት “ሸኔ” የሚል የዳቦ ስም እየተሞካሼ አማራ ላይ ያላቋረጠ ግፍን ፈጽሞና አሁን ላይም ከወያኔ ጋር የፈጠረው ስምምነት ለጊዜው ባያስኬደውም በእነ አብይና ሽመልስ አብዲሳ ውስጡን “አይዞህ” ባይነት ለጊዜው አሸምቆ ይገኛል፡፤ ይህ የሳሙናው አብይ አህመድና የኦሮሙማ ስብስቡ ሴራና ድብቅ የጥፋት አጀንዳ ከሆዳሞቹ በስተቀር የማይገባው አማራ የለም፡፡ አብይና ለሆዳቸው የተሰጡት እነደመቀን የመሳሰሉት የአብይ ፈረሶች ጦርነቱን እስከወያኔ መቃብርና ከምድረ ገጽ መጥፋት ድረስ እስከመጨረሻው ገፍተው ማጠናቀቅ ሲገባቸው በሰላም ጥሪ ስም፣ በድርድር ስም፣ የሚቃዡበት ህልምና የሴራ ድራማ ከንቱና የቂል ስራ ነውና ቢታሰብበት ይሻላል፡፤ ውጤት አያመጣም፡፡ ከንግዲህ በኋላ ህዝቡ የቀረው ሙጣጭ ትእግስትም የለውም ፡፤

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share